ዶ/ር አበራ ሞላ (መጋቢት ፳፬ ቀን ፲፱፻፵ ዓ.ም.) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ መናገሻ ኣውራጃ፣ ሰንዳፋ ከተማ የተወለዱ ኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች በግዕዝ ፊደል እንዲጽፉ የፈጠሩ ኢትዮጵያዊ ሳይንቲስት ናቸው።

ዶ/ር አበራ ሞላ Dr. Aberra Molla

ዶክተር ኣበራ ሞላ የታወቁባቸው ዋናዎቹ ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው። የመድንን ማነስ በማስወገድ ከዓለም የእንስሳት ሓኪሞች ኣንዱ ታዋቂ ምሁር፣ የግዕዝ ፊደልንና ሥነ ጽሑፍ በኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ ውስጥ በኣለውም መጠቀም እንዲቻል የኣደረጉ ሰባት የዩናይትድ እስቴትስና ኢትዮጵያ ፓተንቶች ብቻቸውን የኣሏቸው የግኝት ሊቅና የኣክሱም ሓውልት ከሮም ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ጣልያንን በማስገደድ ወሳኙን እርምጃ የወሰዱ ኣርበኛ ናቸው። [1] [2] [3] Archived ሴፕቴምበር 2, 2018 at the Wayback Machine [4] [5] [6] Archived ኤፕሪል 12, 2019 at the Wayback Machine [7] [8] [9] [10] [11] [12] [13] [14] [15] [16] [17] [18] [19] ዶክተሩ የግዕዝ ኣልቦ ኣኃዝ ቀለሞችና የግዕዝ ኣሥር ቤት ኣኃዛዊ ቍጥሮች ፈጣሪም ናቸው። [20] [21] [22] የግዕዝ ፊደል ሳይቆራረጥ፣ ሳይቀነስና ሳይበላለጥ ዩኒኮድ እንዲገባ የሰጡና ለመብቱ የተሟገቱለት ኣሸናፊ ናቸው። [23][24] ዶ/ር ኣበራ ሞላ ከታዋቂ የዓለም ሳይንቲስቶች ኣንዱ ናቸው። [25] ኢትዮጵያውያን ኢንተርኔት ላይ በዓማርኛ በነፃ ፒሲና ማክ ኮምፕዩተሮች ውስጥ እንዲከትቡ በድረገጽ ለግሰዋል። [26] Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine

ግዕዝ በኮምፕዩተር ለማስተካከል

ዶ/ር አበራ በኮምፕዩተር ግዕዝ ፊደልን መጠቀም እንዲቻል ያደረጉ ምሁር ናቸው። ይሀንንም ያደረጉት የዓማርኛውን የጽሕፈት መሣሪያ (ታይፕራይተር) ለሚያውቁት ቀላል እንዲሆን በ“a”፣ “b”፣ “c”፣ “d” ምትክ “ሀ”፣ “ጠ”፣ “ሸ”፣ “ዘ” እና እንግሊዝኛ ለሚያውቁ በ“A”፣ “B”፣ “C”፣ “D” ምትክ “አ”፣ “በ”፣ “ቸ”፣ “ደ” ቀለሞችን በመመደብ ዓይነት ሠላሳ ሰባቱን የግዕዝ ቤት ኆኄያት ለ፴፯ የኮምፕዩተር መርገጫዎች ስሞችም በማድረግ ነበር። ስምንቱን የፊደል ቤቶች ወይም እንዚራን ስምንት ፎንቶች ላይ በተኗቸው። በእዚህ ዘዴ በእጅ ጽሑፍና ማተሚያ ቤቶች ብቻ ይታተሙ የነበሩት የግዕዝ (Ethiopic) ፊደላት ለመጀመሪያ ጊዜ በኮምፕዩተር ተከተቡ። እ.ኤ.ኣ. በ1982 ከባለቤታቸው ወንድሞች ኣንዱ የሆነው ግሩም ከተማ ድህረ-ምረቃ ከሚማርበት ዴንቨር ዩኒቨርሲቲ መጥቶ ፊደል መሥሪያ ስለተለቀቀ ከኣንድ ዓረብ ጓደኛዬ ጋር ፊደሉን ለመሥራት ስንታገል ዋልን ብሎ ለዶ/ር ኣበራ ቢነግር ለዓማርኛ ፊደል ያላቸውን የልጅነት ፍቅር ቀስቅሶባቸው ፊደል መሥራት ከቻልክ ለምን የዓማርኛውን ኣትሞክርም ኣሉት። ሃያ ሰባት 27 የዓረብ ቀለሞችን በሚያስሠራው መሥራትን በመቶዎች የሚቆጠሩትን ፊደሎቻችንን መሥራት ኣንድ ኣይደለም ከተባባሉ በኋላ ወደፊት በዓማርኛ የሚሠራ ኮምፕዩተር እስኪሠራ ሺዎች ለእንግሊዝኛ የተሠሩን ፕሮግራሞችን ኢትዮጵያውያን እንድንጠቀምባቸው ቃላት ማተሚያዎችን በኣማራጭነት ማቅረብ እንዲቻል ዶክተሩ ኣብሻ የሚባለውን ኩባንያ ኣቋቋሙ። ፊደል መሥራት በመጀመር እ.ኤ.ኣ. ፍላጎታቸውን ኣሟሉ። መጀመሪያ መሥራት የሚቻለውም የኣማርኛ ታይፕራይተር ዓይነቱን ቅጥልጥል ፊደል እንደኣማርኛው ታይፕራይተር በኣንድ የላቲን ፊደል ምትክ መተካት ስለነበረ ያንን ስለኣልፈለጉ እንጂ ቅጥልጥሉንም ከማንም በፊትም ሊሠሩበት ይችሉ ነበር። ተሠርቶበታልም። እየኣንዳንዱ ቀለም ኣንድ-ወጥ የሆነውን የማተሚያ ቤቶች ዓይነት ትክክለኛ የግዕዝ ፊደላችንን ለመጀመሪያ ጊዜ በማቅረብና እየኣንዳንዱም በሁለት መርገጫዎች እንዲከተብ በመፍጠር ግዕዝ ከማተሚያ ቤቶች ወደ ኮምፕዩተር እንዲገባ ኣደረጉ። ሞዴት (ModEth) በመባል የታወቀውን የቃላት ማተሚያ የማይክሮሶፍትን ዶስ በመጠቀም በ፲፱፻፹ ዓ.ም. ኣሜሪካ ውስጥ ለገበያ ኣቀረቡ። ጊዜውም ኮምፕዩተሮችና ማተሚያዎች በቂ ኃይል ማግኘት የጀመሩበት ነበር። ግዕዝ በኮምፕዩተር እንዲከተብ የፈጠሩበትን ዘዴ በዩናይትድ እስቴትስ ፓተንት መጠበቅ እንዲችሉ ቢያመለክቱም በእዚያን ጊዜ ኢትዮጵያ የፓተንት ሕግ ስለኣልነበራት የሳይንስና ቴክኖሎጂ መረጃ ማዕከል (ኢትዮጵያ) ሕጉ ሲወጣ ጉዳዩ ይታያል በማለት ስለወሰነ [27] ፓተንት ኣልወጣለትም ነበር።

ግዕዝ ድምጻዊ ፊደል ስለሆነ እያንዳድንዱን “ሀሁሂ” ቀለም በ“ABC” ምትክ [28] እየደረደሩ ማተም ከ፲፱፻ ዓ.ም. ገደማ ጀምሮ ኢትዮጵያ ውስጥ የኣሉ ማተሚያ ቤቶች ሊጠቀሙበት ችለዋል። [29] [30] Archived ፌብሩዌሪ 14, 2016 at the Wayback Machine በቀለሞቹ ብዛት የተነሳ ግን የእንግሊዝኛውን የጽሕፈት መሣሪያ ለዓማርኛ እንኳን መጠቀም ኣልተቻለም። ከዳግማዊ ምኒልክ ጀምሮ [31] ብዙ ኢትዮጵያውያን ሊቆች፣ ሚኒስትሮችና ደራስያን የእንግሊዝኛውን የታይፕ መጻፊያ ለዓማርኛ መክተቢያ እንዲያገለግል ወደ ሰማንያ ዓመታት ግድም ሲመራመሩ ቆይተው ባይሳካላቸውም [32] Archived ሴፕቴምበር 6, 2013 at the Wayback Machine ዶ/ር ኣበራ ጥረቶቻቸውን በኮምፕዩተር ኣሳክተዋል። ስለ ዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ምርምሩም የዋቢው ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት ኣባ ተክለ ማርያም ሰምሃራይ፣ ክቡር ዶ/ር ሃዲስ ኣለማየሁ፣ ኣቶ ዓለሙ ኃብተ ሚካኤል፣ ኢንጂነር ኣያና ብሩ፣ ዶ/ር ዓለመ ወርቅ፣ ኣለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ክቡር ኣቶ ኣበበ ኣረጋይ፣ ክቡር ራስ ዕምሩ ኃይለ ሥላሴ፣ ዶ/ር ሉባክ፣ ኣቶ ዘውዴ ገብረ መድኅን፣ ብላታ መርስዔ ሃዘን ወልደ ቂርቆስ፣ ፀሓፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ፣ ክቡር ኣቶ ሚሊዮን ነቅንቅ፣ ኣቶ ስይፉ ፈለቀ፣ ክቡር ዶ/ር ከበደ ሚካኤል፣ ኣቶ ሳሙኤል ተረፈ፣ ሌላ እነ ኮሎኔል ታምራት ይገዙመንግስቱ ለማ፣ ኣቶ ብርሃኑ ድንቄብላታ ዘውዴ በላይነህ፣ የኔታ ኣስረስ የኔሰውተክለማርያም ኃይሌ፣ ሼክ በክሪ ሳጳሎ እና ዶ/ር ፍቅሬ ዮሴፍንም [33] ያጠቃልላል። [34] ይህ ድካማቸው በመጨረሻ ሊሳካ የቻለው ግን ዶክተሩ ምንም ቀለም ሳይቀንሱ ወይም መልካቸውን ሳይቀይሩ የጥንቱንና ትክክለኛ የግዕዝ ቀለሞች [35] በኮምፕዩተር ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲቀርቡ ስለኣደረጉ ነው። [36] [37] Archived ኦክቶበር 27, 2015 at the Wayback Machine የእነዚህ ምሁራን በታይፕ መሣሪያ ሙከራዎች የመጠቀም ዓላማዎች ባይሳኩላቸውም ዶክተሩ በእዚያው የፊደል ገበታ ምኞታቸውን ኣሳክተውላቸዋል። [38] በተጨማሪም የቢለንጉራጌ እና ሳሆ ምሁራን የቋንቋ ፊደሎቻቸውን እንዲጨምሩላቸው ናሙና ጽሑፎችን ልከውላቸዋል። ከእዚሁ ጋር በማያያዝ እያንዳንዱ ቀለም በሁለት መርገጫዎች እንዲከተብ ኣዲስ የኣከታተብ ዘዴ ፈጥረው ኣዳዲስ የፊደል ገበታዎችን ኣቅርበዋል። ለእያንዳንዱ የግዕዝ ቤት ቀለምም እንደ እንግሊዝኛው ቍልፎች የእየእራሱ ቍልፍና የቍልፍ ስም መድበዋል። በእነዚህ የተነሳ የግዕዝን ፊደል የእንግሊዝኛው ወይም የኣማርኛ የታይፕ መጻፊያ መጻፍ ስለኣልቻለና ሳይጽፈው ኮምፕዩተር ለመጀመሪያ ጊዜ ደርሶለታል። [39] [40] ዶ/ር ኣበራ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት የግዕዝ ፊደል ኢትዮጵያውያን ለብዙ ሺህ ዓመታት በእጃቸው ሲጽፉትና [41] Archived ጃንዩዌሪ 7, 2017 at the Wayback Machine ከ፲፱፻፬ ዓ.ም. ገደማ ጀምሮ በማተሚያ መሣሪያዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ሲጠቀሙብት የነበረውን ፊደል ነው። [42] Archived ጁን 10, 2015 at the Wayback Machine [43] [44] [45] [46] [47] Archived ኦክቶበር 12, 2018 at the Wayback Machine [48] ግዕዝ በማተሚያ መሣሪያዎች ከኢትዮጵያ ውጪም ታትሟል። የግዕዝ ፊደል በብራናና የመሳሰሉት ላይ ሲጻፍ ቆይቶ በጉተንበርግ (Gutenberg) የፊደል መልቀሚያ ማተሚያ መሣሪያ ፈጠራ ከ፲፭፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ በማተሚያ መሣሪያ ሲጠቀም ቆይቶ [49] ከ፲፱፻፹ ጀምሮ በዶክተሩ ግኝት በኮምፕዩተርና በኋላም በእጅ ስልክ መጠቀም ስለተቻለ ሕዝቡ በዓማርኛና ሌሎች ቋንቋዎች የእራሱ ኣታሚ ሆኗል።

የግዕዝን ቀለም (Glyph) በኮምፕዩተር በቀላሉና በቀልጣፋ ዘዴ ማቅረብ ስለቻሉ ሕዝቡ ከማተሚያ ቤቶች በተሻለ ሁኔታ በፊደሉ መሥራት ችሏል። በእዚህም የተነሳ ሕዝቡ መጻሕፍትንና የመሳሰሉትን ለማሳተም በየማተሚያ ቤቶች ወረፋ ከመጠበቅና ከመንግሥት እገዳ ተርፎ የእራሱ ኣታሚ ሆኗል። [50] [51] ዘዴውም በዓማርኛ ሳይወሰን ለሁሉም የግዕዝ ቀለሞች መክተቢያና ማተሚያ ከሌሎች የዓለም ፊደላት እኩልና ጎን በሚገባ ሥራ ላይ እየዋለ ነው። [52] ይህ የዓማርኛ ውክፔዲያ ገጽ እንደ ሌሎች ትክክለኛ የዓለም ባለ ፊደል ቋንቋዎች ገጾች የቀረበውም በእዚሁ በግዕዝ የዩኒኮድ መደብ ቀለሞች ነው። [53] ሌላው የትግርኛ ውክፔዲያ ገጽ ነው። የዶ/ር ኣበራ ግኝቶች [54] (Ethiopic Character Entry - July 16, 2009 ሕትመት) በግዕዝ ሳይወሰኑ ለኣያንዳንድ የዓለም ፊደሎች ኣዳዲስ ኣጠቃቀሞችና ግኝቶች ስለጠቀመ ስምንት የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንቶች ውስጥና ሦስት የፓተንት ማመልከቻዎች ውስጥ (Citing Patents) ተጠቅሷል። [55] [56] [57] ቊጥሮቻቸውም [58]፣ 8645825፣ 8700653፣ 8706750፣ 8762356፣ 8812733፣ 9715111፣ 9723061፣ 9733724፣ 20110173558፣ 20160042059 እና 2963525A1 ናቸው። [59] እነዚህ ኢትዮጵያን የሚያኮሩ ሥራዎችም ናቸው።

ዶ/ር ኣበራ ሞላ ዩናይትድ እስቴትስ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ [60] በኩል ስለ ኢትዮጵያ ፊደል ግኝታቸው ጉዳይ ፓተንት ማመልከቻ እ.ኤ.ኣ. ፌብሩዋሪ 15 1990 ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን የኣቀረቡት በኮምፕዩተር [61] የተጻፈ የዓማርኛ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያው ባይሆንም ታሪካዊ ነበር። ኮሚሽነር ኣበበ ሙሉነህ በዶ/ር ኣበራ በኮምፕዩተር ለተጻፈው ደብዳቤ መልሱን የጻፉት በአማርኛ የጽሕፈት መሣሪያ በተጻፈ ደብዳቤ ነበር። [62] ዶክተሩ ታህሳስ ፲፩ ቀን ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. (December 19, 1988 ለኮሚሽነሩ የጻፉት ደብዳቤም ኣለ። በኣሁኑ ጊዜ በኮምፕዩተር፣ [63] የእጅ ስልኮችና [64] በመሳሰሉት በግዕዝ ፊደል እየቀረቡ የኣሉት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ስለሆኑ የዶክተሩ ሕልምና ምኞት ከተሳኩ ቆይቷል። [65][66] [67] [68] [69] Archived ኦገስት 15, 2020 at the Wayback Machine መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. የዩናይትድ እስቴትስ መንግሥት ቊጥሩ 9,000,957 የሆነ የመጀመሪያውን የግዕዝ ፓተንት ወይም የግኝቱ ባለቤትነት መብት ማመልከቻውን ከኣስገቡበት ከሰባት ዓመታት በኋላ ለዶ/ር ኣበራ ሞላ ሰጥቷል። [70] ዕውቅናው እንዲታወቅ U.S. Patent No. 9,000,957 የእሚል ማሳወቂያ ግኝቱን ከሚጠቀሙት ዘዴዎች ጋር መቅረብ እንደእሚገባው ሕጉ ይደነግጋል። የፓተንቱም መገኘት የግዕዝ ፊደል በትክክለኛ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እየተደገፈ የማደጉ ምስክርነት ነው። [71] [72] ይኸው የኢትዮጵያም ፓተንት ለዶክተሩ በሦስት ወራት ውስጥ እንደሚሰጥ የኢትዮጵያ ኣእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ጥቅምት ፳፱ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም. ደብዳቤ ጽፏል። በቅርቡም ቍጥሩ 9,733,724 [73] የሆነ ሁለተኛው ፓተንት ግዕዝን በእጅ ስልክ መጠቀም እንዲቻል በመፍጠራቸው በዩናይትድ እስቴትስ መንግሥት ለዶ/ር ኣበራ ሞላ ተሰጥቷል። የእነዚህ ፓተንቶች የኢትዮጵያዊ ሳይንቲስት መሆኑ ጥቅሞች ለብዙዎቹ የኣልገባቸው ይመስላል። ዶ/ር ኣበራ ሞላ የፓተንትን ጥቅም ቀደም ብለው በኣሏቸው ፓተንቶች ምክንያት በማወቃቸው ግዕዝን ዲጂታይዝ በማድረግ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን በቴክኖሎጂው እንዳይቀደሙ በማድረግ በፊደሉና እንደ ዓማርኛ በኣሉ ቋንቋዎቻቸው ላይ መብታቸው እንዳይወሰድ የኣደረጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባለውለታ ሳይንቲስት ናቸው። እስከ ፳፻፲፩ ዓ.ም. ለዶ/ር ኣበራ ሞላ ብቻቸውን የተሰጧቸው የግዕዝ ፓተንቶች ሰባት ደርሰዋል። ይኸንንም USPTO Patent Search ሄዶ Aberra Molla በመፈለግ ማጣራት በሳይንስ ዓለም የተለመደ ነው። ግዕዝን በኮምፕዩተር መክተብ ኣስቸጋሪ በመሆኑ በብቸኛው ምርምራቸው ገፍተውበት ተሳክቶላቸዋል። ሕዝቡ ስለእነዚህ እንዳያውቅም እዚህ ገጽ እየመጡ የሚሰርዙም ስለኣሉ የሚያዋጣ በሌሎች በኩል መፈለግ ነው። ምሳሌ [74]

የግዕዝ ቀለሞች ለማስተካከል

ከልጃቸው ብሩክ ጋር የመጀመሪያውን የግዕዝ የእስክሪንና የማተሚያ ቀለሞች ለመሥራት ኣንድ ዓመት ግድም ነበር የወሰደው። [75] የፊደሉም ችሎታ በማደግ መጀመሪያ ፖስትእስክሪፕት ከእዚያም በ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. ትሩታይፕ [76] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine በኋላም ተንቀሳቃሽ (Embedable) ሆኗል። ግዕዝ ወደ ኮምፕዩተር ሲገባ የስምንት እንግሊዝኛ ሥፍራዎችን በማስለቀቅ ዓይነት ኣንዱኑ ቦታ በየተራ በመጋራት ነበር። በዩኒኮድ መፈጠር የተነሳ ዶ/ር ኣበራ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት እእያንዳንዱ ቀለም የእራሱን ስፍራ ኣግኝቷል። Aberra Molla ከዓለም ፊደል ሠሪዎች ኣንዱ ናቸው። [77] ብዙዎቹ የግዕዝ ቀለሞች በዓለም የፊደላት መደብ ዕውቅና ከኣገኙበት ከ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. ግድም ወዲህ ግን የዕውቀት ክምችት እንዲስፋፋ በቀለሞቹ እንደመጠቀም ዛሬም ኋላቀር በሆነው የኣማርኛ የታይፕ መጻፊያው ዓይነት ቅጥልጥል የኣማርኛ ፊደላት እየጻፉ ኢትዮጵያንና እራሳቸውን ወደኋላ እየጎተቱ ያሉትን እየተቃወሙ ነው። [78] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine ትክክለኛዎቹና ሁሉም የግዕዝ ቀለሞች የዩኒኮድ መደብ ውስጥ እንዲገቡ ዶክተሩ ትልቅ ትግልና ኣስተዋጽዖም ኣድርገዋል። ለምሳሌ ያህል በመጀመሪያ ዙር ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት እንጂ የታይፕራይተሩ ፊደል ግዕዝ እንዳልሆነ ተገልጿል። [79] ይኸን [80] ግዕዝ የኣልሆነ ቊርጥራጭ የኣማርኛ ታይፕራተር ዓይነት ፊደል የግዕዝ ፊደል ስለኣልሆነ በሁለተኛ ዙር ተቃውመው ኣስጥለዋል። [81] የዶክተሩ ሦስተኛ ዙር ተቃውሞ የዓማርኛውን የማተሚያ ቤት ፊደላት ለዩኒኮድ እ.ኤ.ኣ. በ1992 የቀነጠሱትን [82] እና የኣናሳ ተጠቃሚዎች ፊደላት በቍርጥራጭ ፊደላት እንዲተኩ እ.ኤ.ኣ. በ1993 የፈለጉትንና የኣማርኛ ፊደላት ቅነሳ ውስጥ የገቡትንም ያጠቃላል። [83] ዶክተሩ ዲጂታይዝ የኣደረጉት የግዕዝ ፊደል የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ሲጠቀሙባቸው በነበሩት ፊደላት ሲታተሙ ስለነበሩና ስለሆኑ ዛሬ ወደ ፒ.ዲ.ኤፍ (P.D.F.) የተቀየሩትን ጭምር ያለ ችግር ማንበብ ተችሏል።

ፊደሉንም ለማሟላትና ከሌሎች ፊደላት እኩል እንዲራመዱ በየጊዜው ጽፈዋል። ለምሳሌ ያህል እነ “ሀ”፣ “ሐ”፣ “ኀ”፣ “አ”፣ እና “ዐ” የተሳሳቱ ድምፆች ተሰጣቸው እንጂ በዶ/ር ኣበራ ገለጻ የእየራዕቦቻቸው ሞክሼዎች ስለኣልሆኑ ለማጥፋት ማዘጋጀት ቀርቶ ድምፆቻቸውን ተረክበው መብታቸው መከበር ኣለበት ነው። ዕውቀቱም ከዩኒቨርሲቲ ወደ ሕዝቡ መድረስ ኣለበት። [84] ይህ ትግርኛውንም ይመለከታል። ዓማርኛ፣ ቤንችጉሙዝ የቋንቋ ዋና ክፍሎች የ“ጨ” ቀለሞች፣ እንዚራንና ዘመዶች ቀለበቶች ሦስት ሳይሆኑ ሁለት ናቸው። የ“ሀ” ትክክለኛ ድምጽ ወደ “ኸ” የቀረበ ቢሆንም “ኸ”ም የዓማርኛ ሞክሼ የሚባለው ዓይነት ቀለም ስለኣልሆነ ነው ግዕዝ ኮምፕዩተራይዝ ሲደረግ የምልክት መርገጫዎች ላይ የመርገጫ ስም የተሰጠው። የ“አ” ድምጽ በስሕተት “ኧረ” የሚለው ቃል ምሳሌ ውስጥ ስንጠቀምበት የነበረ ድምጽ ስለሆነ ለ“ኧ” ስምንተኛው የ“አ” ቤት ፊደል ድምፁን ዶክተሩ መልሰው ኣስረክበውታል። [“ኧረ”] መከተብ ያለበት በ“አረ” ነው። ምክንያቱም የስምንተኛው ድምጽ ቀለም የሚሠ'ራው ግዕዙ ወይም ራብዑ ላይ መስመር በመጨመር ስለሆነና የ“አ” ቤት ስምንተኛ ቀለም የማይኖርበት ምክንያት ስለሌለ ነው። ይህ የዓይኑ “ዐ” ባለመስመር “ዓ”ንም ሊመለከት ይችላል። “ኧ” ("Schwan e") የስምንተኛው የ“አ” ቤት ቀለም ስለሆነ ስምንተኛውን የ“አ” ቤት ድምጽ (ወደ “እዋ” የቀረበውን) ለ“ኧ” ፊደል መስጠቱ ተገቢ ይመስላል። [85] Archived ጁን 14, 2006 at the Wayback Machine የ“የ”ም ስምንተኛ ድምጽ ቀለም ኣለ። የ“ሀ”ም አንዲሁ። ግዕዝ ድምፃዊ ፊደል (Syllabic) ስለሆነ “ሀ” እና “ሃ” ወይም “አ” እና “ኣ” ድምጽ ስለማይጋሩ ነው ዶክተሩ ስማቸውን “ኣበራ” እንጂ “አበራ” በማለት የማይጽፉት። [86] [87] ከምክንያቶቹ ኣንዱ የግዕዝ ቤቶቹ ቅርሶች ሲጠሩ እንደራብዖቹ ኣፍ በሰፊው ስለማያስከፍቱ ነው።

“ሰረቀ” እና “ሠረቀ” የሚባሉት ቃላት ከግዕዝ የተወረሱ ስለሆኑ ትርጕሞቻቸው ኣንድ ኣይደለም የሚሉ ኣሉ። ዓማርኛ የሚጠብቁና የሚላሉ ቃላት ኣሉት። “ምሥር” (“እህሉ”) እና “ምስር”ም (“ግብጽ”) ኣንድ ኣይደሉም። ንጉሡ “ሠ” የጠበቀ ስለሆነ ዓማርኛውን በእንደእዚህ ዓይነት መለየት ሳይጠቅም ኣይቀርም የሚሉ ኣሉ። ሞክሼ የተባሉትን ልዩነቶች ለስርወ ቃላት ስለሚጠቅሙ ኣለማወቅ ዕውቀቱን ኣያጠፋውም። “ጪ”፣ “ጬ” እና “ጯ” የተሠሩት ሦስተኛ ቀለበት በሌለው “ጨ” ላይ በሚቀጠሉ ቅርጾች ነው። እነዚህ “ጠ” ላይ እንደሚቀጠሉት “ጢ”፣ “ጤ” እና “ጧ” መሆኑ ነው። ስለዚህ እንደ “ጤ” ሦስተኛው እግር ላይ ኣንድ ቀለበት የኣለው “ጬ” እንጂ ሦስተኛው እግር ላይ ሁለት ቀለበቶች የኣሉት “ጬ” የተሳሳተ ነው።

ለግዕዝ የሚያስፈልጉትን በመጨማመር ከፈጠሯቸው የግዕዝ ምልክቶች መካከል “መብት”፣ “ንግድ”፣ “ተመዝግቧል”፣ “ብር”፣ “ሣንቲም”፣ “ማጥበቂያ”፣ “ማላልያ” እና “ኣልቦ” ኣኃዝ ይገኙበታል። የማጥበቂያ ምልክትን ዓማርኛ ለጥቂት ምዕት ዓመታት የተጠቀመ ስለሆነ ዶክተሩ የኣቀረቡት ከኮምፕዩተሩ ቴክኖሎጂ ጋር እንዲሄድ ኣዲስ ቅርጽና ስፍራ በመስጠት ነው። ዕውቅናም እንዲያገኙ ደራሲዎች እንዲጠቀሙባቸው ለዓመታት ከማቅረብ ሌላ ፓተንቶቻቸው ውስጥ ጽፈዋቸዋል። [88] የኮምፕዩተር 42 እንግሊዝኛ ቁጥሮችና ምልክቶች ከግዕዙ ጋር ያቀረቡት ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ለግዕዝ ሥራ እንዲያገለግሉ ወስነው ከግዕዙ ቀለሞች ጋር በተመጣጠነ መልክ መሥራት ስለጀመሩ ኮምፕዩተር ገበታ ላይ ያሉት ኣጠቃቀም ለግዕዝም እንዲያገለግል ነው። ለምሳሌ ያህል “+”፣ “-”፣ “*” እና “/” የመደመርመቀነስማባዛትማካፈል የግዕዝ የሢሳብ ምልክቶችና ማስሊያዎችም ናቸው። በእጅ ጽሑፍና ማተሚያ ቤቶች ብቻ ይቀርብ የነበረው የግዕዝ ፊደል [89] ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ ኣጠቃቀሙ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ፲፱፻፹ ዓ.ም. ገደማ ለሕዝብ ቀርቧል። ከእዚያም ወዲህ ፊደሉ የዩኒኮድ የዓለም ፊደላት መደብ ውስጥ ስለገባ እእያንዳንዱ ቀለም የእራሱ ስፍራና ቍጥር (ኮድ) ኣለው። [90] በእዚህም የተነሳ የግዕዝ ፊደል እንደሌሎች የዓለም ፊደላት የዩኒኮድ መደብ ውስጥ ገብቷል። [91]

ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና ስለ ኣገኘና ወደ ፲፫ የተለያዩ የቋንቋ ቀለሞች ስለኣሉት የሁሉም የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚ ብሔሮች መብቶች በእኩልነት መጠ'በቅ እንደኣለባቸው ዶክተሩ ያምናሉ። [92] ስለዚህ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች የማያስተናግድ ወይንም ለማስተናገድ ችሎታ የሌለው ዘዴ መቅረብ ስለሌለበት ተጠያቂው ኣቅራቢው ብቻ ሳይሆን ተጠቃሚው ምሁርም ነው። በግዕዝ ቀለሞች ብዛት የተነሳ በግዕዝ መሥራት ቢያስቸግርም ከቴክኖሎጂው ጋር መጓዝ ስለቀጠለ ለእንግሊዝኛው የተሠሩትን ለግዕዝ መጠቀም እንዲቻልና ግዕዝ የሚፈልገውንም ለመሥራት መትጋት ይጠበቅብናል። የተሳሳቱ ነገሮችን ማስተካከልና በትክክል መጠቀም ጠቃሚ ናቸው። ዶክተሩ የተጠቀሙበት የሁለተኛው ፊደል መነሻ ተወዳጁና ለረዥም ዘመናት ጥቅም ላይ ሲውል የነበረው የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ኣንደኛው የሞኖታይፕ የፊደል መልቀሚያ መሥሪያ ፊደልና የተስፋ ገብረሥላሴ ማተሚያ ቤት ፲፱፻፲፯ ዓ.ም. ቁምፊ (Typeface) ናቸው። የቀለማቱም መልኮች ከዩኒኮዱ ጋር ኣንድ ዓይነትና መደበኛ የኢትዮጵያ [93] ፊደላት ናቸው። [94] ውብ ቀለሞቻችንን በወጉና በማዕረጉ መጠቀም ተችሏል። ዶክተሩ ይኸን በመደበኛነት ከ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. ጀምሮ እየተጠቀሙበት ነው። በማያምር፣ የተሳሳተና የከሳ ፊደል የተጻፈ ጽሑፍ ማንበብ ኣያጓጓም።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እነ ማይክሮሶፍት (Microsoft)፣ ጉግል (Google)ና ኣፕል (Apple) የተለያዩ የግዕዝ ፊደላት ማቅረብ ጀምረዋል። ምንም እንኳን የተለያዩ ቁምፊዎች መኖር ተፈላጊ ቢሆኑም ኣስቀያሚውንና የተሳሳቱትን በዝምታ ማሳለፍ ሕዝቡ ተስማምቶበታል ማለት ነው። በኣሁኑ ጊዜ ብዙ ደራስያን መጻሕፍትን በተሳሳቱ ፊደላት እያሳተሙ ስሕተቶችን እያስፋፉ ስለሆነ ሊነገራቸው ይገባል። ወደፊት በትክክለኛ የግዕዝ ፊደሎቻችን የተከተቡትን ጥንታዊ ቀለሞቻችንን ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ ወደኣደረጉት ትክክለኛ የዘመናዊው ማተሚያ ቤቶች ቀለሞች መቀየር ቢቻልም ዛሬ በኣለማወቅ በተሳሳቱ ቀለሞች ኣዳዲስ ስሕተቶችን ማስተዋወቅ ኣስፈላጊ ኣይደለም።

የግዕዝ ፊደል ውስጥ ለሌሉ ድምጾች ኣዳዲስ ቀለሞች መፍጠር ሊያስፈልጉ ይችላሉ። ይህ ፊደላችን ለሌሎች ቋንቋዎችም እንዲጠቅሙ ያስችላል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች ዘንድ ግዕዝ የኣዳም እና የሔዋን ቋንቋ ነበር፤ ፊደሉን የፈጠረው ከማየ ኣይኅ ኣስቀድሞ የሴት ልጅ ሄኖስ ነበረ፤ [95] [96] በሌላ በኩልም ኢትዮጵያዊው የግዕዝ ፊደል የዓለም ፊደላት ምንጭ ነው ይባላል። [97] [98] [99] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine [100] Archived ኤፕሪል 4, 2023 at the Wayback Machine የኢትዮጵያ ነገሥታት ዝርዝሮችና የግዛት ዓመታት እዚህ ኣሉ። [101] Archived ጃንዩዌሪ 9, 2015 at the Wayback Machine [102] ሌሎችም መረጃዎች ኣሉ። [103] [104] [105] በግዕዝ ቋንቋ ብዙ እልፍ ድርሳናትና ምስጢራት ተከትበዋል። [106] የግዕዙ ፊደል እድሜ ከላቲኑ የበለጠ ነው። [107] [108] (ጥንታዊቷ ግብጽ ከ5100 ዓመታት በፊት በኢትዮጵያውያን የተቈረቈረች ናት ይባላል።) የግብፆችን ጽሑፍ ከኢትዮጵያ የተወሰደ መኾኑንና የሮማና የሌሎች ፈላስፎችም የተጠቀሙባቸው መጻሕፍት ከግብጽ መጽሓፎች የተወሰዱ እንደኾኑ ማረጋገጥ ተችሏል። በጽሑፍ ሰፍረው ከሚገኙ አንዳንድ መረጃዎችም በመመሥረት የጽሑፍ ፊደል በኢትዮጵያውያን የተጀመረ መኾኑን መገመት ይቻላል። የሥነ ፈለክ (Astronomy) ጥናትን የጀመሩት ኢትዮጵያውያን ስለመኾናቸው ማስረጃዎች ይናገራሉ። ሌሎች ሃገራት የሓውልትንና የግንባታ ሥነ ጥበብን የተማሩት በጥንት ኢትዮጵያውያን ነው። [109] Archived ኤፕሪል 4, 2023 at the Wayback Machine ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ምንጭ ነች የሚሉም ኣሉ። [110] Archived ኤፕሪል 4, 2023 at the Wayback Machine የላቲን ኤቢሲዲ ካፒታል ፊደላት የግዕዙን ፩፪፫፬ የመሰሉት እኛ ከግሪኮቹ ወስደን ኣይደለም። [111] በኢትዮጵያ ታሪክ ጽሑፍ በግሃ ድንጋይ ተጠቅሞ በድጋይ ላይ ከመጻፍ ቅጠልን ቀጥቅጦ በመጭመቅ በብራና ላይ ወደ መጻፍ ሽግግር የተደረገው በንጉሥ ሰብታህ (2545-2515 ዓ.ዓ.?) ዘመነ መንግሥት መሆኑ ተጽፏል። [112] ይህ ከ5000 ዓመታት ግድም በፊት መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ ከዛሬ ሰባት ሺህ አመታት በፊት በዳዕማት የፅሁፍ ትምህርት መስጠት መጀመሯን ለሚያውቅ ሰው በወቅቱ ኣገራችን ደርሳበት የነበረውን የሥልጣኔ ደረጃ መገመት ኣያዳግተውም፡፡ [113]

የግዕዝ ቍልፎች ለማስተካከል

ምንም እንኳን ከ“A” እስከ “Z” የኣሉት የኮምፕዩተሩ መርገጫዎች (Keys) ለእንግሊዝኛው ፊደላት ስምና መርገጫ እንዲሆኑ ቢሠሩም [114] ፴፯ቱን መርገጫዎች ለ፴፯ቱ የግዕዝ ቤት ቀለሞች ማለትም ለ“ሀ”፣ “ለ”፣ “ሐ”፣ “መ”፣ “ሠ”፣ “ረ”፣ “ሰ”፣ “ሸ”፣ “ቀ”፣ “ቐ”፣ “በ”፣ “ቨ”፣ “ተ”፣ “ቸ”፣ “ኀ”፣ “ነ”፣ “ኘ”፣ “አ”፣ “ከ’፣ “ኸ”፣ “ወ”፣ “ዐ”፣ “ዘ”፣ “ዠ”፣ “የ”፣ “ደ”፣ “ዸ”፣ “ጀ”፣ “ገ”፣ “ጘ”፣ “ጠ”፣ “ጨ”፣ “ጰ”፣ “ጸ”፣ “ፀ”፣ “ፈ” እና “ፐ” ስምና ቍልፎች እንዲሆኑ ኣድርገዋል። ግዕዝ በኮምፕዩተር እንዲጠቀም ሲፈጥሩ እያንዳንዱ ቀለም የሚከተበው በሁለት መርገጫዎች ነበር። ለሚፈልጉትም የቍልፍ መለጠፊያዎች ነበሩት። እያንዳንዱ የግዕዝ ቀለም ስም የሚከተበው እንደ እንግሊዝኛው ዝቅ (Shift) መርገጫን በመጠቀም ነው። በኣሁኑ ጊዜ እያንዳንዱን ቀለም በኣንድና ሁለት መርገጫዎች መክተብ የሚያስችል ኣብሻ (ABSHA) የሚባል ዘዴ ስለፈጠሩ ዓማርኛውን በእንግሊዝኛ ፎነቲክ እስፔሊንግ እንጽፋለን በማለትና ያም ስለኣልተሳካ እስከ ኣራት መርገጫዎች መጠቀም እንደማያስፈልግ ተደርሶበታል። [115] ምክንያቱም ዓማርኛው በኣራት ቢከተብም የኣናሳ ተጠቃሚዎች ቋንቋዎችን በእዚሁ እስፔሊንግ ዘዴ ለመክተብ እስከ ስምንት መርገጫዎችን መጠቀም ስለሚያስፈልግ ነው። [116] [117] Archived ጁላይ 4, 2014 at the Wayback Machine እንግሊዝኛ የእራሱ ችግሮች የኣሉት ፊደል ነው። [118] [119]

ላቲን (Latin) “ቸ” ቀለምን የሚከትበው በ“CH” ሲሆን “ቸ” ቀለም ቢኖረው ኖሮ ትክክለኛ ኣጠቃቀም ስለሆነ ኣንድ መርገጫ ይሰ'ጠው ነበር። የላቲን ቊልፎች ለሃያ ስድስቱ ቀለሞች የተመደቡት ለእያንዳንዳቸው እንጂ በዋየልነትና ኮንሰናንትነት የሥራ ክፍፍል ኣይደለም። በሌላ ኣነጋገር የ“E” መርገጫ ለ“E” የእንግሊዝኛ ፊደል የተመደበው “E” ቀለም ስለሆነ እንጂ ዋየል ስለሆነ ኣይደለም። የዶክተር ኣበራ ግኝት ይኸን መሠረታዊ ኣጠቃቀም በማገናዘብ የላቲኑንና የግዕዙን ኣቀራረብ በማዋሃድ የዋየል መርገጫዎችን የፊደልነትና የዋየልነት ኣሠራር ለግዕዝ ተጠቅሞበታል። [120] Archived ዲሴምበር 27, 2012 at the Wayback Machine [121] ምክንያቱም ግዕዝ ድምፃዊ ፊደል ስለሆነ እንዚራኖቹን በዋየል መዘርዘር ሃያ ስድስቱን የላቲን ቀለሞች በዋየል ከመዘርዘር ጋር የተቀራረበ ስለሆነ ነው። በእዚሁ መሰረት 37ቱ የግዕዝ ቤቶች እንደ 26ቱ የላቲን ቤቶች የእየእራሳቸው መርገጫዎች ከተሰጣቸው በኋላ በዋየልነት እንዲያገለግሉ ለሁለተኛ ሥራ የተመደቡት የዋየል መርገጫዎችና ተጨማሪ መርገጫዎች የእንዚራን መቀየሪያዎች ሆነዋል። ግኝቱ ከእነዚህም ኣልፎ ለዋየል መርገጫዎች ሦስተኛ ኣዲስ ኣጠቃቀም ሥራ ላይ ኣውሏል።

ለእንግሊዝኛው የኮምፕዩተር መርገጫና ኣከታተብ ዘዴ እንዲመች የግዕዝ ፊደላት ከ“A” እስከ “Z” ያሉት ፳፮ ቁልፎችን እንዲጋሩ ማድረግን ዶክተሩ ይቃወማሉ። ምክንያቱም ከ“ኤ” (“A”) እስከ “ዚ” (“Z”) የኣሉት የላቲን ቍልፎችን ፊደሉ በኣንዳኣንድ መርገጫዎች በመጠቀም እንግሊዝኛውን እንዲከትብ የተሠራ እንጂ ከእዚያ በላይ ብዛት ከኣለው የግዕዝ ፊደል ኣጠቃቀም ጋር ግንኙነት ስለሌለው የግዕዙ ኣጠቃቀም ውስጥ ጣልቃ በመግባት ወሳኝ መሆን ስለማይገ'ባው ነው። ላቲን 26 ሳድሳን ሆህያቱን የሚከትበው ለእእያንዳንዱ ኣንድ መርገጫ በመጠቀም ሲሆን ለካፒታል (Capital) ቀለሞቹ ሁለት መርገጫዎችን ይጠቀማል። የዶክተሩን ትክክለኛ ግኝትና ኣመዳደብ እናሻሽላለን ብለው የ"ዝቅ" (Shift) መርገጫዎችን ከሳድሳኑ ጋር ግንኙነት ለሌላቸው የግዕዝ ኆኄያት (ምሳሌ፦ “ጥ” በ“ዝቅ” “ት” ) የመደቡ ግዕዙን ለእስፔሊንግ ጣጣ ለመዳረግ የሚፈልጉትንና ቀለማቱን በብዙ መርገጫዎች የሚከትቡትን ይቃወማሉ። ምክንያቱም ዶክተሩ በፈጠሩት ዘዴ ሁሉንም ቀለሞች ከኣንድ ገበታ በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ብቻ በኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች መክተብ ስለተቻለና እየተሻሻለም ስለሆነ ነው። [122]

እነ “ዠ” እና “ጰ” ቀለሞች ራቅ የኣሉ መርገጫዎች ላይ የተመደቡት ብዙ ቃላትና ተጠቃሚዎች ስለሌሏቸው ነው። [123] ግዕዙን በ26 የላቲን ፊደላት መጻፍ መሞከር ግዕዙ በላቲን መርገጫዎች እንዲጠቀም ማስገደድ ነው። የኢትዮጵያ ሳይንቲስቶች ለግዕዝ የሚበጀውን መሥራትና መፍጠር እንጂ ሌላ ፊደል ላይ ማተኰር ኣስፈላጊ ኣይደለም። ምክንያቱም በዘዴው ዓማርኛውን እስከ ኣምስት መርገጫዎች በመጠቀም መክተብ ቢቻልም የሌሎች ቋንቋዎች ሲጨመሩ ከእዚያ በላይ መርገጫዎችን መጠቀም ስለሚያስከትሉ ነው። ዶክተሩ ለፊደላቱ መደበኛ ስፍራዎች ሲመድቡ ወደ ቀኝ ዳር የተመደቡት ብዙ ተጠቃሚዎች የሌላቸው ናቸው። እንዲህም ሆኖ በጥናት ላይ የተመረኰዘ ማሻሻል ማቅረብ ይቻላል። ለምሳሌ ያህል ኣንድ የኢትዮጵያ ባለሥልጣን መሥሪያ ቤት የግዕዝ መርገጫዎች መደብ ኣቅርቧል። መደብ የሚያወጡት ግን ሥራውን የፈጠሩት ናቸው። ግዕዝን በላቲን ፊደል ገበታ መክተብ ኣስቸጋሪነት የቀረበ ጽሑፍ ኣለ።

ዩኒኮድ ለማስተካከል

ግዕዝ (Ge'ez) ወደ ኮምፕዩተር ሲገባ የስምንት እንግሊዝኛ ሥፍራዎችን በማስለቀቅ ዓይነት ኣንድውኑ ቦታ በየተራ በመጋራት ነበር። በዩኒኮድ (Unicode) መፈጠር የተነሳ ግዕዝ ኣሥራ ሁለተኛው ገበታ ላይ ተመድቦ እእያንዳንዱ ቀለም የእራሱን ስፍራ ኣግኝቷል። ጥንትም ቢሆን እያንዳንዱ ቀለም የግሉ የሆነ ከ1 እስከ 5600 ቍጥር ነበረው። [124] [125] [126] በተጨማሪም ትክክለኛዎቹና ሁሉም የግዕዝ ቀለሞች ዩኒኮድ የዓለም ፊደላት መደብ እንዲገቡ በማቅረብና በመጻፍ ዶክተሩ ትልቅ ኣስተዋጽዖ ኣድርገዋል። ይህ ሊሆን የቻለውም የዓለም ፊደላትን ዩኒኮድ የተባለ የፊደላት መደብ ውስጥ ሁሉም የዓለም ቀለሞች ዕውቅና እንዲያገኙ በ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. ለተቋቋመ ድርጅት ሁለተኛውን የግዕዝ ፊደል ከሠሩበት የኮሎራዶ ኩባንያ በኩል ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ ያደረጉትንና ያቀረቡትን ብዙ መቶዎች ትክክለኛ ቀለሞች [127] [128] [129] በማስጣል [130] ሌሎች ዓማርኛ ፊደል የኣልሆነውንና ዓማርኛን የማያስጽፈውን ኢንጂነር ኣያና ብሩ የሠሩትን ዓይነት የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ቅጥልጥል ፊደል ተሳስተው ዓማርኛና ግዕዝ ነው ብለው ስለኣቀረቡ ነበር። እነዚህ [131] መቶ ሃያ ስምንት ስፍራዎች ይበቃሉ በማለት ለዩኒኮድ ኣቅርበው የነበረውን በመቃወምና ጽፈው በ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. ኣስጥለዋል። [132] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine በኋላም 106 ፊደላትና 97 ቍርጥራጮችን የኣልሆኑትን ኢትዮፒክ እየኣሉ 256 የፊደል ስፍራዎች እንደማይበቋቸው እንኳን የኣልዓወቁትን ተቃውመዋል። ይኽንንም በማድረጋቸውና ኢትዮጵያውያን በፊደላቸውና ቋንቋዎቿቸው በኮምፕዩተር እንዲጠቀሙ ስለፈጠሩ ለግዕዝና ኢትዮጵያ ባለውለታ መሆናቸው ከመጻፉ ሌላ “የግዕዝ ኣባት” የሚል የቅጽል ስም ተሰጥቷቸዋል። [133] [134] [135] [136] [137] [138] [139] Archived ጃንዩዌሪ 28, 2022 at the Wayback Machine [140] Archived ጁላይ 20, 2014 at the Wayback Machine [141] [142] Archived ጁላይ 29, 2021 at the Wayback Machine [143] [144] [145] [146] በሁለተኛ ዙር ይህ የፊደል መቀጠል ጥፋት እንደገና ተደግሞ [147] 364 ብቻ ግዕዝዓማርኛትግርኛኦሮምኛ ቀለሞችን ያጠቃለለ ለዩኒኮድ በሌሎች ስለቀረቡ ዶክተሩ በድጋሚ ተቃውመዋል። ይኸንንም ተቃውመው የጻፉት ፊደል ስለበዛና የግዕዝ በቶቹ ወደ ፴፯ ስለደረሱ የኣናሳ ተጠቃሚዎች ቋንቋዎች ቀለሞች በቅጥልጥሎች እንዲጻፉ ሌሎች ስለወሰኑ ነበር። [148] [149] በሦስተኛ ዙር ማሻሻያዎችም ከ55 በላይ የጉራጌኣገው/ቢለንና የመሳሰሉት የኣናሳ ተጠቃሚዎች ቋንቋዎች የግዕዝ ቀለሞች ዕውቅና እንዲያገኙ ቢጽፉምና [150] በትብብር ቢሳካም ሌሎች በጀመሩት ጠንቅ ግዕዝ ኣራት ስፍራዎች ተበትኖ ለዩኒኮድ ቀርቧል። [151] [152] [153] [154] [155] [156] [157] ዶ/ር ኣበራ ለግዕዝ መብት ባይቆሙለት ኖሮ [158] [159] Archived ዲሴምበር 27, 2012 at the Wayback Machine [160] [161] የኣማርኛ መጻፊያው መኪና ኣስቸጋሪ ኣከታተብና የኣልተሟላ ቁርጥራጭ ፊደል ተሻሽሎም ቢሆን ስሕተቱ እንደሚቀጥል ጽፈውም የዩኒኮድ ፊደል ሆኖ ኢትዮጵያ ከማትወጣበት ዘላቂ ችግር ውስጥ ከመውደቅ ኣትድንም ነበር። [162] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine [163] ምንም እንኳን ዶክተሩ ሞዴት ውስጥ ጭምር ያቀረቧቸው ኣናሳ ቊጥር የኣላቸው ብሔሮች ቀለሞች ዩኒኮድ መደብ ውስጥ በመጨረሻው ቢገቡም [164] [165] [166] ዶክተሩ ለግዕዝ ፊደል እንዲያገለግሉ የፈጠሯቸውና ብዙዎች ከ፳ ዓመታት በላይ የተጠቀሙባቸው የግዕዝ ኣልቦ፣ ቊጥራዊ ኣኃዞችና ኣዳዲስ ምልክቶች ገና ኣልገቡም። ለምሳሌ ያህል የሚፈልጉት የማጥበቂያ ምልክትና ሌሎችም ከፊደሉ በኋላ እንጂ ከላይ ብቻ እንዲገቡ ዶክተሩ ኣይፈልጉም። ያም ሆነ ይህ ዛሬ በኮምፕዩተር፣ የእጅ ስልክና የመሳሰሉት መሣሪያዎች ውስጥ የምንጠቀምበት የዩኒኮድ ፊደል ዶክተር ኣበራ ሞላ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉትም የግዕዝ ፊደላቸውና ፊደላችን ነው። ይህ ፊደል ኢትዮጵያውያን ለብዙ ዘመናት በብራናና በወረቀት ሲከትቡ የነበረውና ደራስያን በየማተሚያ ቤቶች ኣያሌ መጽሓፍትን የጻፉበት ነው። [167]

የኣማርኛ የታይፕርይተር ኣማርኛ እንዳልሆነ ዩኒኮድንና ሌሎች ኢትዮጵያውያንን ኣሳምነው ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ የኣደርጉት የግዕዝ ፊደላቸው የዩኒኮድ ፊደል ሆኗል። እንዲህም ሆኖ የቅጥልጥል ፊደላቸው ውድቅ ከሆነባቸውና መጻፊያ ሠርተው ከተካሰሩት መካከል ኣንዱ ተቀይሞ ዛሬም የታይፕራይተሩን ፊደል ኮምፕዩተራይዝ ከኣደረጉት ኣንዱ ነው ተብሎ ዕውቅና ቢሰጠውም እንኳን በሓሰት ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣደረግሁ የሚል ኣለ። በሳይንስ ዓለም ውሸት ትልቅ ነውር ነው። የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና በሚል ርዕስ ከእዚህ በታች የቀረቡትን ከ፴፭ በላይ እንከኖች ማንበብ ይቻላል።

በኣሁኑ ጊዜ ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና ያገኙትን የቢለንባስኬቶቤንችምኢንሙርሲሱሪትግረትግርኛኣገውኣውንጂኦሮምኛዓማርኛዲዚዳውሮጉሙዝጉራጌጋሞ ጎፋ እና ግዕዝ ቋንቋዎች የሚጋሯቸውን ቀለሞችና ሌሎች ያጠቃልላል። ከእነዚህ መካከል የቢለን፣ ባስኬቶ፣ ምኢን፣ ትግረ፣ ትግርኛ፣ ኣገው፣ ኦሮምኛ፣ ዓማርኛ፣ ዳውሮ፣ ጉሙዝ፣ ጉራጌ፣ ጋሞ ጎፋ እና ግዕዝ በዩኒኮድ የቋንቋዎች ፊደላት ስሞች አንዲሆኑ በዶክተሩ ተለይተዋል። በፊደሉ ከሚጠቀሙ ቋንቋዎች መካከል ሓረሪ ኣንዱ ነው። መጽሓፍ ቅዱስ ሙሉዉን ወይም በከፊል ከ፲፭፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ በግዕዝ ቀለሞች በማተሚያ ቤቶች [168] ከታተሙባቸው ቋንቋዎች መካከል ሃዲያሲዳሞከንባታኦሮሞወላይታ እና ጌዴኦ ይገኙበታል። [169] [170] Archived ዲሴምበር 14, 2011 at the Wayback Machine የግዕዝ ፊደል ኢትዮጵያዊው ሊቅ ኦነሲሞስ ነሲብ የኦሮምኛውን መጫፈ ቁልቁሉ ሲጽፉ የፈጠሩትን "ዸ" ቀለምና እንዚራኖቹን ይጨምራል። [171] ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ ያደረጉት ትክክለኛውና በሳይንሳዊ ግኝትና ኣርበኝነት ከኣጥፊዎች ያቆዩልንና የግዕዝ ቀለሞቻችን የተለያዩ መልኮች እዚህ ኣጓዳኝ መዝገበ ቃላት ማየት ይቻላል። እንደ ኤውሮጳ ኣቆጣጠር በ1991 Ethiopian Research Council የሚባል በ1934 ኣሜሪካ ውስጥ (በእነ ዶ/ር መላኩ በያን) የተቋቋመ ድርጅት ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ በማድረግና ለጀመሩት የግዕዝ ፊደል ሕዳሴ የዕውቅና ሽልማት ሰጥቷቸዋል። [172] [173] ሽልማቱም “...for computerizing Ethiopic and revolutionizing the Geez script” ይላል።

ምንም እንኳን ለኣማርኛው የጽሕፈት መኪና ሲባል ቀለሞቹ እንዲቀነሱ የተለያዩ ሓሳቦች ቀደም ብለው ቢቀርቡም [174] Archived ሴፕቴምበር 6, 2013 at the Wayback Machine ትክክለኛዎቹ ፊደላት ወደ ኮምፕዩተርና ወደ ዩኒኮድ የዓለም መደብ በዶክተሩ ሲገቡ ሞክሼዎች እንዲቀሩ ስለኣልተባለ ትክክለኛ ሥራ ተሠርቷል። [175] ምክንያቱም የዶክተሩ ዓላማ የግዕዝን ፊደል ወደ ኮምፕዩተር ማስገባት እንጂ የዓማርኛውን የታይፕራይተር ፊደል ወደ ኮምፕዩተር ማስገባት ስለኣልሆነና ሥራቸው የታይፕራይተሩን ችግር ከመፍታት ሌላ የማተሚያ ቤቶች ሠራተኞችንም ድካም የሚቀንስ መሆኑን ስለዓወቁ ነው። በኋላም ይህ ውጤት ሊገኝ የቻለው ግን በግማሽ የዓማርኛ ፊደል እንዲጻፍ መደብ ኣውጥተናል የኣሉትንና ፊደል ስለበዛ የኣናሳ ተጠቃሚዎች ቋንቋዎች ቀለሞች ቅርጾቻቸውን እንደጠበቁ ማስገባት ቀርቶ በቅጥልጥል ነገሮች ይሥሩ የኣሉትን ጥቂት ኢትዮጵያውያን ዶክተሩ ከተቃወሙና ሁሉም ቀለሞች ቅርጾቻቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ ከኣሳመኑ በኋላ ነበር። [176] እንዲህም ሆኖ ለድረገጽ መሥሪያ 225 ፊደሎችን ኣንድ የተራዘመ ለእንግሊዝኛ የተሠራ መደብ (Extended ASCII) ስለሚችል በእዚያ ልክ የዓማርኛውን ቀለሞች መርጠው በቂ ናቸው በማለት ለኣንዱ ዕውቅና ስለሰጡ [177] ዶክተሩ ለሦስተኛ ጊዜ ተቃውመው በማስጣል ኣሸንፈዋል። የሚያሳዝነው ግን እነዚሁ ሰዎች ግዕዝና ዩኒኮድ ምን እንደሆነ ዋቢ ኣድርገው እ.ኤ.ኣ. 1995 ሲጠቀሙበት የነበሩትን የዶክተሩን ቀለሞች እንኳን ያስገቡት ግዕዝን ኤክስቴንድድ (Ethiopic Extended) ብለው ለኣራተኛ ጊዜ ከስሕተቶቻቸው ሲነቁ ነበር። እንዲህም ሆኖ ደራስያን በሚፈልጉት ቀለሞች ዓማርኛውን የመክተብ መብት ቢኖራቸውም ቀለማቱ በዩኒኮድ ዕውቅና ስለኣገኙ ፊደል መቀነስና መቀንጠስ ያስፈልጋል የሚባለው ክርክር በዶክተሩ ኣሸናፊነት ኣክትሟል። ቴክኖሎጂው በሁሉም የግዕዝ ቀለሞች እንድንጠቀም ችሎታ ስለሰጠን በተቀነሱ ወይም ሞክሼዎች በሌሏቸው መሥራትን ዶክተሩ ኣይደግፉም። ምክንያቱም ወደፊትም ኮምፕዩተሩ ትክክለኛዎቹን ኆኄያት መርጦ ስለሚያቀርብ ለመሳሳት ዕድሉ ስለማይኖር መቀነስ ደካማ ጊዜያዊ ኣማራጭ እንጂ ግዴታ መሆን ስለሌለበት ነው። በተጨማሪም ፊደል መቀነስ ከታይፕራይተር ጋር በተያያዘ የመጣ ደካማ አስተሳሰብ በዶክተሩ ግኝቶች የተነሳ ቀርተዋል። በግዕዝ ፊደል የሚጠቀሙ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ብዛት ወደ 45 ይደርሳል ይባላል። በቅርቡ መጠቀም ከጀመሩት መካከል ማሌ እና ዲሜ ቋንቋዎቻችን ይገኙበታል።

ግዕዝ ወደ ዩኒኮድ ሲገባ ኣስተዋጽዖ ከኣደረጉት መካከል ዶ/ር ፒ. ማክክሉር፣ ኢ/ር ጆ. ቤከር፣ ኢ/ር ሎይድ ኣንድርሰን፣ ኢ/ር ግሌን ኣዳምስ፣ ዶ/ር በቀለ ሞላ፣ ጌታቸው ሞላ፣ ኢ/ር ፍሰሓ ኣጥላው፣ ኢ/ር ታከለ ኣድነው፣ ኢ/ር ፀሓይ ደመቀ፣ ዶ/ር ይጥና ፍርድይወቅ፣ ኢ/ር ግሩም ከተማ፣ ኢ/ር ቴዎድሮስ ኪዳኔ፣ ዶ/ር ሳሙኤል ክንዴ፣ ኢ/ር ተረፈ ራስወርቅ፣ ኢ/ር ተሻገር ተስፋዬ፣ ኢ/ር ታደሰ ፀጋዬ፡ ኢ/ር ማቲዎስ ወርቁ፣ ኢ/ር ኣባስ ዓለምነህ፣ ኢ/ር ዳንኤል ያዕቆብ፣ ኢ/ር ዮናስ ፍሰሓ፣ ዶ/ር ኣርዓያ ኣምሳሉ፣ ማይክል ኤቨርሰን፣ ኢ/ር ዳዊት ብርሃኑ፣ ኢ/ር ኤፍሬም ተክሌ፣ ኢ/ር እስክንድር ሳህሌ፣ ኢ/ር ዮናኤል ተክሉ እና የኢትዮጵያ የደረጃዎች ኤጀንሲ ይገኙበታል። እነዚህ ውጭ ኣገር የኣሉ ኢትዮጵያውያን ኣገራቸው ችሎታውን በኣልነበራት ጊዜ ኃላፊነታችውን በትብብር የተወጡና ታሪክ የሠሩ ባለውለታ ጀግናዎች ናቸው። ይህ ዝርዝር ያላካተታቸውን ማሟላት ይቻላል።

ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው ለዩኒኮድ ከኣቀረቡ በኋላ ችግር የፈጠሩባቸው የተለያዩ ዓይነቶች ሰዎች ነበሩ። ይህ የሚቀርበው ከረዥም ስሕቶቻችው መማር ኣቅቷቸው ዛሬም ሰውን ከማውናበድ በኣለመቆጠባቸው ሲሆን እንደኣስፈላጊነቱ ወደፊት ስማቸው ይዘረዘራል። ምሳሌ፦ [178] [179]

የዩኒኮድ የዓለም ቀለሞች መደብ ውስጥ [180] የግዕዝ ፊደላችን ፲፪ኛው (1200) መደብ ላይ ይጀምራል። [181] የዩኒኮድ መደብ ውስጥ “ፘ” “ፙ”ን ስለቀደመ ማስተካከል ይኖርብናል። የኣሽሙር (ስላቅ፣ ቀልድ፣ ፌዝና መፀት) ምልክትም ተረስቶ የዩኒኮድ መደብ ውስጥ ኣልገባም።

በዶክተሩ ሳይንሳዊ ሥራ ተሸንፈው ፊደል መቀነስና መቀንጠስ ትተው በኋላ ተቆርቋሪ የሆኑ ኣሉ። ቀንና ደራሲ የሌሏቸው በተለይ በእንግሊዝኛ የቀረቡ ጽሑፎች ኣቀራረባቸው ግዕዙን ለማዳከም ስለሆነ ኣንባቢው መገንዘብ ይኖርበታል። ፊደሉ ለሌሎች ቋንቋዎች እንዲተርፍ መጨመር ያስፈልገው ይሆናል። ወደፊት ዩኒኮድ ውስጥ መግባት የኣለባቸው ወንበር የሌላቸውን ኣሥሩን የዶክተሩን ኣኃዞች፣ ሥዕላቸው እዚህ የቀረቡ የፈጠሯቸውን ስምንት ምልክቶችና ነቍጥን ይጨምራል።

ዶ/ር ኣበራ ሞላ የግዕዝ ፊደል፣ ገበታና ኣከታተብ ፈጣሪ ከመሆናቸው ሌላ ፊደሉንም ወደ ትሩታይፕ በመቀየር የመጀመሪያው ናቸው። የሠሩትንም የግዕዝ ፊደል ለዩኒኮድም ሰጥተዋል። የፈጠሯቸው የተለያዩ የግዕዝ ፊደላት ሆኑ ኣከታተቦችና ገበታዎች ለተለያዩ ቍርጥራጮች፣ የግዕዝ ቀለሞችና የዩኒኮድ ፊደላት ጭምር ነው።

ግዕዝ ኣረጋገጥ ለማስተካከል

ዶ/ር ኣበራ ለመጀመሪያ ጊዜ ግዕዝ በኮምፕዩተር እንዲከተብ በሞዴት ሲፈጥሩ እያንዳንዱ ቀለም የትኛው ቍልፍ ላይ መመደብ እንዳለበትም ወስነዋል። [182] [183] ከእዚያም ወዲህ ኣመዳደቦቹ እንዳስፈላጊነታቸው በኢትዮወርድ (EthioWord) [184] Archived ኦክቶበር 31, 2012 at the Wayback Machine [185] እና ግዕዝኤዲት (GeezEdit) ተሻሽለው ቀርበዋል።

ግዕዝ ወደ ኮምፕዩተር ለመጀመሪያ ጊዜ ሲገባ ወይንም ግዕዝ በኮምፕዩተር እንዲሠራ ሲፈጥሩ ኣዳዲስ ነገሮችን ፈጥረዋል። እነዚህም ኣንደኛ ፊደላቱ ኮምፕዩተር ላይ እንዲታዩና ሲታተሙም ወረቀት ላይ እንዲታዩ እያንዳንዱን ቀለም ለኮምፕዩተሩ እስክሪንና ለተለያዩ የማተሚያ መሣሪያዎች መሥራት። እያንዳንዱ የግዕዝ ቤት በፈንክሽን (Function key) መርገጫ በኣንደኝነት እንዲቀርብ ሆኖ ቀለማቱ እንዚራን በሁለተኛው መርገጫ ኣማካኝነት ቀረቡ። [186] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine ሁለተኛው ለፊደላቱ ገበታዎችና ገጽታ (Layout) በመፍጠር የትኛው ቀለም የትኛው ቍልፍ ላይ እንደሚመደብ መወሰን። ሦስተኛው እያንዳንዱ ቀለም ከሁለት መርገጫዎች በላይ ሳያስፈገልገው እንዲከተብ የመክተቢያ ዘዴ መፍጠር። ለምሳሌ ያህል በሁለት መርገጫዎች የሚከተብ ቀለም የሚታየው ሁለተኛው መርገጫ ከተረገጠ በኋላ ሊሆን ይችላል። ኣራተኛው የግዕዝ ፊደል ለዘመናት ሲጠቀምበት እንደቆየው የፊደሉ ተጠቃሚ ቋንቋዎች የሚከተቡት በግዕዝ ፊደል ነው። (በሌላ ኣነጋገር ኣብዛኛው ፈረንጅ እንደሚመስለው ፊደሉ በላቲን ፊደል ተጽፎ ወደ ግዕዝ ኣይቀየርም ማለት ነው። የፊደሉ ዋና ጥቅሞች ለመጻፍና ኣንድን የግዕዝ ጽሑፍ ለማየት ነው።) ኣምስተኛው ግዕዝ መሣሪያውን በሚገባ እንዲጠቀም ኣስፈላጊ የሆኑትን ኣዳዲስ ነገሮች መጨመር፣ መፍጠር፣ ማስተዋወቅና መጠበቅ ነበሩ። [187] [188][189] [190] [191] [192] ለምሳሌ ያህል ፊደላቱ ከተበተኑበት ስምንት ፎንቶች ሌላ ድርብርብ ሆነው ከቀረቡት ሌሎች ፊደላት ኣንዱ የሞዴት መጻፊያ ፎንት መነሻ ዓማርኛ በብዛት የሚጠቀምበት ሳድሳኑ በቀዳሚነትና በብዛት ሁለተኛ የሆኑት የግዕዝ ቤት ቀለሞች በዝቅ መርገጫዎች እንዲከተቡ ቀርበዋል። ለስድስተኛ ምሳሌ ያህል የኮምፕዩተር የእንግሊዝኛ ምልክቶች ኣጠቃቀም ለግዕዙም እንዲያገለግል በተመጣጣኝ ቀለሞች ቀርበዋል። የእንግሊዝኛው ኣመዳደብ የተመረጠው የቍልፎች መለጠፊያዎች በሰባተኛነት ቢሠ’ሩም ግዴታ በመሆን እንዳያስፈልጉና [193] ኣከታተቡን ወደ እንግሊዝኛው QWERTY (ቅውኽርትይ) ገበታ ለማቀራረብ ነበር። በኮምፕዩተር ዘመን ግዕዝን ብቻውን ማቅረብ በቂ ስለኣልሆነ ግዕዙ የቀረበው በዘጠኝነት ከእንግሊዝኛ ፊደሎች ጋር ነው። ስለዚህ እንደ ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ የኣሉት የሞዴትኢትዮወርድ እና ግዕዝኤዲት ፊደሎቻችን የእየእራሳቸው የእንግሊዝኛና የግዕዝ ፊደሎች ኣሏቸው። በዘጠኝነት ሕዝቡ እራሱን ኣከታተቦች እንዲያስተምር ጠቅሟል። በኣሥረኝነት የተጠቃሚዎች ቋንቋዎች ብዛት ተመጣጥነዋል፣ ስሕተቶችና ግድፈቶች እንዲታረሙና ወደ ዘመናዊ ኣሠራር እንዲሻሻሉ ሓሳቦች ቀርበዋል። በኣሥራ ኣንደኝነት ኣንድን ጽሑፍ በኣልተቀጠሉት የታይፕራይተር ገበታና በእንግሊዝኛ ዓይነት ኣቀማመጥ በሁለቱም ኣከታተብ መጻፍና ማሻሻል ቀርቶ በእንግሊዝኛው ዓይነት ብቻ እንዲሠራ ኣድርገዋል። በኣሥራ ሁለተኝነት ኣሠራሩም ለዘመናት የተለመዱትን የእንግሊዝኛ ዘዴዎችና ኣጠቃቀሞች ለግዕዙም በማድረግ ከኮምፕዩተር ወደ እጅ ስልኮች እንዲዘልቅ ሆኗል። የዶክተሩ ግኝት ለግዕዝ ብቻ ስለኣልሆነ እንግሊዝኛውንም ይመለከታል። በኣሥራ ሦስተኝነት ኣንድን ጽሑፍ ታይፕራይተርና በእንግሊዝኛው ኣጻጻፋቸው የተለያዩ ሰዎች እንዲከትቡና አንዲያሻሽሏቸው ኣስችለዋል። በመጨረሻም ዶክተሩ በፊደል ቅነሳ ባይስማሙም ለሚፈልጉት የተቀነሱትን የፊደል ገበታ ኣቅርበዋል። በኣሥራ ኣራተኛነት የዜሮ ኣኃዝ በሕንዶች ከሺህ ዓመታት ግድም ተገኝቶ ቀስ በቀስ ዓለም ሲጠቀምበት ኢትዮጵያውያን ምንም ሳያደርጉ ቆይተው በመጨረሻው የኣረቡን መጠቀም ስለጀመሩ ዶክተሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የግዕዝን ኣልቦዎች ፈጥረው ፊደሉ ከኮምፕዩተር ቴክኖሎጂ ጋር የሚሄድ ኣኃዛዊ ኣድርገውታል።

እንዲህም ሆኖ ግዕዝን በኮምፕዩተር መጠቀም ፊደሉን ማቅረብ የሚመስሏቸው ኣሉ። የላቲንም ሆነ የግዕዙ ፊደል መሣሪያው ላይ ከሌለ ሳጥን የመሰሉ ነገሮች ይታያሉ። ፓተንት የሚሰጠውም ለፊደሉ ወይም ፊደሉን ለሠራው ኣይደለም። የዶክተሩን ፊደላት መርገጫዎች ስፍራ ቀይሮ ማቅረብ ሕዝቡን ለማወናበድ እንጂ ኣዲስ ግኝት ወይም ገበታ ኣይደለም። የዶክተሩን ፈር ቀዳጅ ሥራ በተለያዩ ደካማ ገልባጮች መተካት ቢሞከርም ብቸኛውና ትክክለኛ በመሆን ከ፴፪ ዓመታት በላይ ማገልገሉን ቀጥሏል። ዶክተሩ መክተቢያዎቹን ወደ ኣንድ ሲያሻሽሉት ገልባጮች ከሁለት በላይ መርገጫዎችን በመጠቀም ያልተሟሉና ያልተከተቡ ጽሑፎችን በማቀረብ ሕዝቡን በማጃጃል ገፍተውበታል።

በኮምፕዩተር የግዕዝ ፊደል የመጀመሪያውን መብት ያገኘበት የዩናይትድ እስቴትስ ኮፒራይት ወይም መብት ምሳሌ ሞዴት (የኢትዮጵያ ቃላት ማተሚያ) በዶ/ር ኣበራ ሞላ፣ የመብት ቍጥር TX0003337637 ፲፱፻፹፪ ዓ.ም. እዚህ ኣለ። [194]

ዶ/ር ኣበራ ሞላ እያንዳንዱ የግዕዝ ቀለም በሁለት መርገጫዎች እንዲከተብ የፈጠሩትን ዘዴ በኢትዮጵያ ኋላ ቀርነት የተነሳ መብታቸውን ማስጠበቅ ስለኣልቻሉ የተለያዩ ኣከታተቦች መቅረብ ቢቀጥሉም ለዊንዶውስ [195] እና ማክ [196] Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine ያቀረቡትንም በቅርቡ ወደ ኣይፎን እና ዓይፓድ ወስደውታል። [197] የእንግሊዝኛው ኣመዳደብ የተመረጠው መለጠፊያ እንዳያስፈልግና ኣከታተቡን በፓተንት በተጠበቀው ወደ እንግሊዝኛው QWERTY (ቅውኽርትይ) ገበታ ለማቀራረብ ነው። ሁለቱም ቋንቋዎች የሚጠቀሙበትን መርገጫዎች በመጋራት ሕዝቡ በሁለቱም ፊደላት በኣንድና ሁለት መርገጫዎች የተጠቀመው ለብዙ ዓመታት ሥራ ላይ ውሏል። በዶክተሩ ግኝት ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች ከኣንድ ገበታ በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ብቻ መክተብ ተችሏል። ለላቲን ቀለሞች የተሠሩት መርገጫዎች ከኣሥር እጅ በላይ ብዛት ለኣላቸው የግዕዝ ቀለሞች ሥራ ላይ ውለዋል። [198] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine በዶክተሩ ዲጂታይዝድ (Digitized) የሆነው የጥንቱ የግዕዝ ፊደል የውጭ ኣገሮችና የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ከመቶ ዓመታት በላይ የተጠቀሙበትም ፊደል ነው። [199]

መርገጫዎችን በጣቶች በመንካት መጻፍ ያስቻለውን የላቲን ቀለሞች የእጅ ጽሑፍ መሣሪያ ኣከታተብ ወደ ኮምፕዩተርና ጮሌ የእጅ ስልኮች በተሻሻለው ዓይነት ለግዕዝ ቀለምም ይኸው ትክክለኛና ሳይንሳዊ ኣጠቃቀም ለግዕዝ ሥን ጽሑፍ ሥራ ላይ ውሏል። የእዚህ ገጽ ኣንዱ ዓላማ ሕዝቡ ስለ ቴክኖሎጂው እንዲያውቅና እንዳይታለል ሲሆን ጥቂቱ በወሬ እየተፈታ ጊዜውን እንዳያባክን መረጃ መጠየቅም እንዲጀምር ነው። በሳይንስ ኣሠራር ኣንድ ነገር ተሻሻለ የሚባለው በሂሳብ ተመዝኖ (Statistical Analysis) [200] ብልጫ ወይም ልዩነት ሲያሳይ (Significance) እንጂ ኣንዳንዶቹ እንደሚፈልጉት በተራቀቀ መሣሪያ በመጠቀም ወደኋላ ለመመለስ ኣይደለም። በዶክተሩ ኣከታተብ "ህ" እንዲሁ በኣንድ መርገጫ ብቻ ይከተባል። "ሀ" በዝቅ "h" ወይም "h መዝለያ" ሲጻፍ "ሁ" በ"hu"፣ "ሂ" በ"hi"፣ "ሃ" በ"ha"፣ "ሄ" በ"he" እና "ሆ" በ"ho" ይከተባሉ። የስምንተኛ ቤት ቀለሞች በ"\"፣ "." ወይም "8" ይከተባሉ። በኮምፕዩተር ኣከታተብ ወግ የመጀመሪያዎቹ የላቲን ቀለሞች ወይም ካፒታሎቹ (Capitals) የቁልፉም ስም ስለሆኑ የሚከተቡት በዝቅ መርገጫ ነው። በእንግሊዝኛው ኣያያዝ "H" ("ኤች") የመርገጫው ስም የሆነው በዝቅ "h" ("ኤች") እንደተከተበው የግዕዙም "ሀ" የመርገጫ ስም በዝቅ "ህ" ወይም "ሀ" እንዲከተብ ተደርጓል። ስለዚህ የ"ሀ" መርገጫ የ"ሀ" ቍልፍ ስምም ነው። በእዚሁ ኣያያዝ እንግሊዝኛ ለ94 ቀለሞቹ የሚጠቀምበትን ኣከታተብ የግዕዝ ፊደል ሁሉንም ቀለሞቹን እንዲጠቀምበት ሆኗል። [201] Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine [202] [203] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine [204] ሠላሳ ሰባቱ የግዕዝ ቤት ቀለሞች እንደላቲኑ 26 የእራሳቸው ቁልፎች ስለኣሏቸው ለትምህትና ገለጻም ጠቀሜታ ኣላቸው። ስለዚህ ማንኛውንም የግዕዝ ቀለም በማዳበል በሦስት መርገጫዎች መክተብ ጊዜና ጉልበት ማባከን ነው። ማንኛውንም የግዕዝ ቀለም በማዳበል በሦስት መርገጫዎች መክተብም ግዕዝ የእራሱ ገበታ እንዳይኖረው ነው። ማንኛውንም የዓማርኛ ቀለም በስድስት መርገጫዎች መክተብ ጊዜና ጉልበት ማባከን ነው። ምሳሌ "ፄ"። ዓማርኛውን በብዙ መርገጫዎች መክተብ ሌሎችን ከእዚያ በላይ መጠቀም ያስከትላል። ኣንዳንዶቹ በዘዴዎቻቸው የእራሳቸውን ቋንቋዎች በሦስት መርገጫዎች መክተብ እንጂ ፊደሉን ለሚጠቀሙ 80 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ዘዴዎቻቸው እንደማይጠቅሙ የተገነዘቡ ኣይመስልም።

ኣመልካች ጣቶችን የ“ፈ” እና “ጀ” መርገጫዎች ላይ በማድረግ “ፋ” በትንሿ ጣትና “ፌ” በግራ ቀለበት ጣት ይከተባሉ። “ጁ” በቀኝ ኣመልካች፣ “ጂ” በመካከለው፣ “ጆ” በቀኝ ቀለበት እና “ጇ” በትንሿ ጣት ይከተባሉ። ይኸም በየተራ እንደ “fa”፣ “fe”፣ “ju”፣ “ji” ፣ “jo” እና “j\” እንደሚከተቡት መሆኑ ነው። [205] Archived ፌብሩዌሪ 24, 2018 at the Wayback Machine ይህ በእንዲህ እንዳለ የግዕዝ ፊደል የእራሱ ገበታ ቢኖረው ስለማይጠቅመው በእንግሊዝኛ፣ ፈረንሳይኛ ወይም ኣረብኛ የፊደል ገበታ ቢጠቀም ይሻለዋል በማለት ግዕዝ በእንግሊዝኛ እስፔሊንግ እንዲከተብ የሚፈልጉ ኣሉ። ላቲን ፊደሉን የሚከትበው በፊደሉ ነው። ግዕዝ ፊደሉን በላቲን ፊደል እስፔሊንግ ከ"A" እስከ "Z" በኣሉት ይከተብ ማለት ለፊደሉና ኢትዮጵያውያን ስድብ ነው። ምክንያቱም ለእያንዳንዱ የእንግሊዝኛ ቀለሙ የተሠሩት 26 መርገጫዎች ለ37 የግዕዝ ቀለሞች የተሠሩ ስለኣልሆኑ 26 መርገጫዎች ለላቲን መክተቢያዎች እንጂ ለግዕዙ ኣልተሠሩም። ግዕዝን በእንግሊዝኛ እስፔሊንግ መክተብ እንግሊዝኛ ቋንቋዎችንንና ፊደሎቹን ለማዳበር ስለሚጠቅም ኣንዳንድ የውጭ ኣገር ሰዎችና ኢትዮጵያውያን ኣጎብጓቢዎች ይወዷቸዋል። በእንግሊዝኛ እስፔሊንግ ዓማርኛና ግዕዝን መክተብ እንዳስቸገረ ቢጻፍም የማይቀየሩ ኣሉ። ግዕዝን በ26 መርገጫዎች መክተብ መሞከር ከእስፔሊንግ ጣጣ ኣልፎ ላቲን ውስጥ የሌለውን ፊደልን በእስፔሊንግ የመጻፍ ኣዲስ ችግር ግዕዝ ላይ ይፈጥራል። የላቲን ፊደል ተጠቃሚዎችን ለእስፔሊንግ ፊደል ችግር ውስጥ ከጣላቸው ኣንዱ ምክንያት የፊደላቱ ቍጥር ማነስ ነው። ግዕዝ ድምጻዊና የተስፋፋ ፊደል ስለሆነ የላቲንን ችግር ለግዕዝ ማካፈል ኣያስፈልግም። ለምሳሌ ያህል ትግርኛውን "ቜ" በስድስት መርገጫዎች የሚያስከትቡ ኣሉ። ከእዚህም ሌላ ያልተሟሉና ስለሆነ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች የማያስከትቡ ኣሉ። ወደ ኦሮምኛው የላቲን ቁቤ ኣከታተብ በቀረበ ኣንድን ድምጽ በብዙ መርገጫዎች የሚያስከትቡ ኣሉ።

ግዕዝ ብዙ የድምጽ ቤቶች በኣሉት ቀለሞች ሲጠቀም እንግሊዝኛ ኣንድ ዓይነት ድምጽ ብቻ በኣለው ፊደል ነው የሚጠቀመው። የእንግሊዝኛው ፊደል ድምጽ በግዕዝ የሳድሱ ድምጽ ዓይነት ነው። በእንግሊዝኛ የኮምፕዩተር ገበታ ሳድሳኑ ድምጾች በኣንድ መርገጫ እንደሚከተቡት ሁሉ የግዕዙም ሳድሳን በኣንድ ይከተባሉ። በእንግሊዝኛ ካፒታል ፊደሎቹ የቁልፎቹ ስምም (ምሳሌ፦ Capital “M”) ስለሆኑ በዝቅ መርገጫዎች እንደሚከተቡት በግዕዝም የመርገጫዎቹን ስሞች የግዕዝ ቤት ፊደላት (ምሳሌ፦ የግዕዝ ቤቱ “መ”) የቁልፎቹ ስምም በዝቅ መርገጫዎች እንዲከተቡ ዶክተሩ ወስነዋል። በተጨማሪም በዓማርኛ 40 በመቶ የሚሆኑት ቃላት ሳድሳኑ ስለሆኑና ይህ በብዛት ኣንደኛ ስለሚያደርጋቸው እነሱን አንደላቲኑ እያንዳቸውን በኣንድ መርገጫ መክተብ ተገቢ ነው። ሌሎቹ ሰባት እንዚራን ወደ 60 በመቶ ናቸው። በእንግሊዝኛው እንደሚደረገው የኮምፕዩተሩ ኣከታተብ ወደ እጅ ስልክ እንደዞረው ለግዕዙም ሆኗል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ወጉንና ሥርዓቱን ሳይጠብቁ የፊደሎቹን ቦታዎች እየቀያየሩ ለኮምፕዩተርና ለእጅ ስልክ የተለያዩ፣ የኣልተሟላና የማይጽፉ ኣከታተቦች በብዙ መርገጫዎች የሚያቀርቡ ኣሉ። ለምሳሌ ያህል ይህ የዊኪፔዲያ ገጽ “ቊ” እና “ቌ” የዓማርኛ ቀለሞችን ኣያስመርጥም። የዶክተሩን ሥራ መገልበጥ እንጂ ኣስተሳሰብ የኣልገባቸው ሳድሳኑን በሁለት መርገጫዎች የሚያስከትቡና የሚከትቡ እንዲሁም ኣንብበው ከመረዳት ይልቅ በወሬ የሚነዱ ተወናባጆች ኣሉ። በብዛት ኣንደኛ የሆኑትን የግዕዝ ሳድሳን ቀለሞች በዶክተሩ ፈጠራ በኣንድ መርገጫዎች ከመክተብ ይልቅ በሁለት መክተብ ጅልነት ነው። (ምሳሌ፦ "ጥ"ን በዝቅ "T" ።) የእንደዚህ ዓይነቶቹ ችግሮች መነሻዎች ስለጉዳዩ የሚያውቁት የዶክተሩን በፓተንቶች የተጠበትን ዘዴዎች ከመደገፍና እዚህ እንደሚደረገው ከማስተማር ይልቅ መገልበጥ፣ መስረቅ ወይም ዝምታን የመረጡ በብዛት ስለኣሉ ነው። እነዚህ እራሳቸውንና ግዕዝን መበደላቸውንም የማይገባቸውም ኣሉ። የዶክተሩ ግዕዝ ኣጠቃቀም ፊደላቱን ከኣንድ እስከ ስምንት በላይ ፎንቶች በመበታተንና እንዳሉ ከመጠቀም ሌላ በዋየሎች፣ ፈንክሽን፣ ኣኃዞችና ምልክቶች ቍልፎች ማቅለምንና መለዋወጥንም ይመለከታል። እንደታይፕራይተሩ ዘዴ ኣንድ የፊደል ገበታ ለግዕዝ ስለማይበቃ ከኣንድ በላይ ገበታዎች ላይ የተበተኑትን በኣንድ የተጻፈውን በሌላ መርገጫ ቀይሮ ማቅረብን ይጨምራል። ዶክተሩ የተጠቀሙበት ፕሮግራም ዓይነት ለገበያ የቀረበ ሲሆን (እ.ኤ.ኣ. በ1983) ዘዴዎቻቸው ከኢትዮጵያውያን ይልቅ የገልባጮችና የእውሸት የግዕዝ ሌጀንዶች (Legends) ሲሳይ ሆኗል። ኢትዮጵያ የፓተንት ሕግ እንደሌላት ሳያውቁና ከዓወቁ በኋላ የዶክተሩን ዘዴዎች ገልብጠው የተለያዩ ፕሮግራሞች ውስጥ ሲሸጡና ሲበትኑ የነበሩ ከተጠቀሙባቸው ፕሮግራሞች መካከል ወርድእስታር፣ ወርድና ወርድፐርፌክት ይገኙበታል። የኢትዮወርድን ኢትዮፒክ ዶት ስም ቀይሮ ሲሸጥ ከነበረ ኣንስቶ ዘዴውን እንደኣዲስ ነገር ለኮምፕዩተር፣ ለእጅ ስልክና ፓተንት ማመልከቻ የኣቀረቡ ኣሉ። የዶክተሩ ፓተንት ግዕዝን በኣንድና ሁለት መርገጫዎች መክተብን ያጠቃልላል።

የመድኅን ማነስ ለማስተካከል

ከእዚህ ሌላ በእንስሳት ሕክምና ሙያቸውም [206] በተለይ በኢምዩን ደፊሸንሲ ፓተንቶችና በኣበረከቱት Immune Deficiency Patent 4,501,816 [207] [208] 2,127,963 [209] ፈውስ [210] ይታወቃሉ። [211] [212] [213] በኣደረጉት ምርምርና ውጤት ኢምዩን ደፊሸንሲን በማስወገድ [214] በየዓመቱ ሲጠፉ የነበሩትን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሕይወትን [215] እ.ኤ.ኣ. ከ፲፱፻፸፰ ወዲህ ማትረፍ ተችሏል። [216] [217] ከሰው ልጅ እናቶችና ከኣንዳንድ የጦጣና ውሻ ዝርያዎች በስተቀር የሌሎች እንስሳት ማህጸኖች ኢምዩኖግሎቡሊን (Immunoglobulin) የሚባለውን የበሽታ መከላከያ ፕሮቲን ለጽንሶቻቸው በእርግዝና ጊዜ ኣያስተላልፉም። ኣጥቢ እንስሳት በእርግዝና ጊዜ በኣካባቢው ለሚገኙት በሽታዎች መከላከያዎች በእንገርነት ያከማቹላቸውና ኣራሶቻቸው እንደተወለዱ ጡት ሲጠቡ የበሽታ መከላከያዎቹ ፕሮቲኖች ሳይለወጡ ከኣንጀት ወደ ደም በመግባት ለጥቂት ሳምንታት ከበሽታዎች ይከላከሉሏቸዋል። ኣራሶቹ እንገሩን ሳያገኙ ከቆዩ ግን ወደ ደም መግባታቸውና መከላከያነታቸው ቀርቶ እንደ ተራ ፕሮቲን ምግብ ብቻ ይሆናል። [218] ስለዚህ እንደ ጥጆች የኣሉት ሲወለዱ የኤድስ ቫይረስ የበሽታ መከላከያቸውን እንደጨረሰ ሰው ምንም መከላከያ ስለሌላቸውና ኣካባቢው ያሉትን የበሽታ ጀርሞች እየቀማመሱ በተለያዩ በሽታዎች የእራሳቸውን መከላከያ መሥራት እስከሚጀምሩ ድረስ እየተጠቁ ኣብዛኛዎቹ ይታመማሉ፣ ወደ ኣሥር ከመቶም [219] ይሞታሉ። ታክመው የሚድኑትም ኣይጠረቁም። [220] [221] [222] Archived ማርች 27, 2016 at the Wayback Machine በኮሎራዶ እሰቴት ዩኒቨርሲቲ (Colorado State University) የዶ/ር ኣበራ የድህረ ዶክትራል ምርምር ይኸን ችግር ለመቋቋም መፍትሔ ፍለጋ ጋር የተያያዘ ነበር። [223] [224] Archived ማርች 3, 2014 at the Wayback Machine [225] [226] [227]

ከላይ እንደተገለጸው በዶ/ር ኣበራ ሞላ ግኝት እስከ 50 ከመቶ [228] Archived ኦገስት 11, 2017 at the Wayback Machine ለዘመናት ጠንቅ ሆኖ የቆየውን መድኃኒት የሌለውን የእንስሳትን ኤድስ ዓይነት ሁኔታ (Failure of Passive Transfer / FTP) መቆጣጠርና ማስወገድ ተቻለ። [229] [230] [231] Archived ጁን 15, 2016 at the Wayback Machine [232] Archived ኦገስት 11, 2017 at the Wayback Machine [233] ጥጆች የእናቶቻቸውን ጡት በመጥባት ወይም በጡጦ ከሚሰጣቸው እንገር በቂ የበሽታ መከላከያ ማግኘታቸው ኣስተማማኝ ኣይደለም። [234] ኣንዱም ምክንያት የጥጃ ወተት ኣንጀት ይዘት ሁለት ሊትሮች ብቻ ስለሆነ ነው። በእዚህ የተነሳ እንደኣካባቢው ቆሻሻነት ለተቅማጥ፣ የሳንባ ምችና ሌሎች በሽታዎች እየተጋለጡ ገበሬውን የሚያካስሩት እንደተወለዱ በቂ መድኅን የኣላገኙት ዋናዎቹ ናቸው። እንገር ውስጥ የኣለውን የበሽታ መከላከያ ፕሮቲን ጥጃው እንደተወለደ ከተሰጠው እንገሩ ጨጓራ ሳይገባ ከወተት ኣንጀት ወደ እንጀት በመሄድ ሳይለወጥ ደም ውስጥ ይገባል። የእንቦሳ ጨጓራ እንደሚሠራና እንገር ውስጥ የኣሉት የበሽታ መከላከያዎች ወደ ደም እንደሚገቡ በምርምር በማረጋገጥ የመድኅን ማነስን (Passive Immune Deficiency) ለመጀመሪያ ጊዜ ዶክተሩ ማስወገድ ቻሉ። ምርምራቸውን ጨርሰው ያቀረቡትን መፍትሔ ሁሉም ዓውቀውት ቢጠቀሙበት የመድኅን ማነስ ወደ ኣልቦ (ዜሮ) ከመቶ ግድም ሊወርድ ይችላል። [235] [236] [237] Archived ጁላይ 7, 2014 at the Wayback Machine [238] [239] Archived ጁን 2, 2018 at the Wayback Machine [240] Archived ዲሴምበር 7, 2013 at the Wayback Machine [241] Archived ኦገስት 22, 2014 at the Wayback Machine [242] [243] [244] [245] Archived ጁላይ 27, 2021 at the Wayback Machine [246] [247] [248] ምክንያቱም ጥጃው እንደተወለደ እንገሩን ማግኘቱ የበሽታ መከላከያው ወደ ደም በብዛት የሚገባበት ጊዜ ከመሆኑም ሌላ የበሽታ መከላከሉን ሥራ ስለሚጀምርና ብዙ ደቂቃዎች ሳይወስድ እንገሩን በብዛት መስጠት ስለተቻለ ነው። እነዚህን ማሳካትና እንገሩ በቂ መከላከያ ፕሮቲን እንዳለው ማረጋገጥ ተጨማሪ ጥቅሞች ናቸው። ጥጆች እንደተውለዱ ወደ ጋለን የሚጠጋ ጥሩና ንፁህ እንገር እንደመጋት ባይጠቅምም ገበሬውም የእንገሩን ጥሩነት የሚያጣራበት የእንገር መመርመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ ወይም ተወልዶ የተገኘ ጥጃ በቂ መድኅን እንዳገኘ የሚያጣራበት የደም መመርመሪያ ኣስፈላጊ ሆኖ ስለኣገኙት ኣዲስ የምርመራ ዘዴዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ፈጠሩለት። ኢምዩኖግሎቡሊን የሚባል ኣካል እራሱን የሚከላከልበት ፕሮቲን በብቃት መኖር ኣስፈላጊ ስለሆነ መ’መ’ርመር ኣለበት በማለት ኣዲስ ኣስተሳሰብ ከማስተዋውቅ ሌላ ለእንገርና ደም ቀላል መመዘኛዎች ፈጠሩ። በቂ የመከላከያ ፕሮቲን የኣለውን እንገር መጋት ፈውስ እንደሆነ በሳይንስ መጽሔቶችም ኣቀረቡ። [249] የኣጋጋት ቪድዮዎች እዚህ ኣሉ። [250] [251] [252] [253] [254] [255] በዘዴው እየተጠቀሙ የኣሉት ቀስ በቀስ እየጨመሩ ስለሆነ በእየዓመቱ ብዙ ሚሊዮን ሕይወት ማዳን ቀጥሏል። [256] Archived ኦክቶበር 1, 2015 at the Wayback Machine [257] [258] Archived ኦገስት 11, 2017 at the Wayback Machine በኣሁኑ ጊዜ የዶክተሩን ግኝት በመከተል በተለይ የዩናይትድ እስቴትስ ትላልቅ እርሻዎች ውስጥ ለእያንዳንዱ ጥጃ እንደተወለደ በቱቦው እንገር ይሰጣል። [259] [260] [261] Archived ኦገስት 1, 2016 at the Wayback Machine [262] [263] [264] የእንገር ጥቅም በምርምር ከተረጋገጠበት እ.ኤ.ኣ. 1922 ወዲህ [265] በመስኩ ትልቅ ኣስተዋጽዖ የዶክተሩ የ1977 ምርምራዊ ሥራ [266] [267] [268] ሳይሆን ኣይቀርም። ምክንያቱም የእንገር ጥቅሙ ቢታወቅም ሁሉም ጥጃዎች እንዲያገኙት ስለኣልተቻለ ችግሩ ቀጥሎ ነበር። [269] [270] [271] [272] Archived ማርች 3, 2017 at the Wayback Machine [273] Archived ኦገስት 11, 2017 at the Wayback Machine [274] ከዶክተሩ ምርምር በፊት ጥጆች ሳር መቀንጠስ እስኪጀምሩ ድረስ ጨጓራ ስለማይሠራ በስሕተት እንኳን እንገር እዚያ ቢገባ ይጎዳቸዋል የሚባል ኣጉል እምነት በዓለም ላይ ነበር። ኣሜሪካ 65,000 የእንስሳት ሓኪሞችና 92 ሚሊዮን የቀንድ ከብቶች ኣሏት። [275] የዶክተሩ ዘዴ ለተለያዩ ለማዳና የዱር እንስሳት ጥቅም ላይ መዋሉ ለኣርባ ዓመታት እያደገ ቀጥሏል። ዩናይትድ እስቴትስ ውስጥ በእየዓመቱ ከሚወለዱት 40 ሚሊዮን ጥጃዎች 4 ሚሊዮን የሚሆኑት በመድኅን ማነስ ሊሞቱ ይችሉ የነበሩት በዶክተሩ ግኝት በኣለፉት ኣርባ ዓመታት ሊተርፉ ችለዋል። በተጨማሪም ፵ በመቶ ጥጃዎች ሕክምና እንዳያስፈልጋቸው ሆኗል። በዓለም ላይ የኣሉ የቀንድ ከብቶች ኣንድ ቢሊዮን ስለሆኑ ቢያንስ ኣሥር በመቶ በዘዴያቸው ቢተርፍ ግምቱን ማስላት ይቻላል። [276]

ሌላው በረከታቸው ኣዲስ የሕክምና ዘዴ ሓኪሞችና ገበሬዎች እንዲጠቀሙባቸው የቱቦዎቹን ቀላልና ቀልጣፋ የሕክምና መንገድ ወይም ኣሰጣጥ (ጨጓራ ስለሚሠራ) (New medical route) ማግኘታቸው ነው። ከዶክተሩ ግኝት በፊት ጥጆች ሲታመሙ ሓኪም ቤት ተወስደው መድኃኒት የሚሰጣችው በመርፌ ነበር። በዶክተሩ ግኝት የተነሳ ገበሬው በቱቦው መድኃኒትና ፈሳሽ መስጠት ስለሚችል ወጪና ጊዜ ተቆጥበዋል። [277] Archived ኦገስት 1, 2016 at the Wayback Machine

ዶክተሩ የመድኅንን ማነስ በማስወገድ ከዓለም የእንስሳት ሓኪሞች ኣንዱ ታዋቂ ምሁር ናቸው። የግዕዝ ፊደል በኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ ውስጥ በኣለውም መጠቀም እንዲቻል የፈጠሩ ሊቅና የኣክሱም ሓውልት ከሮም ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ጣልያንን በማስፈራራት ወሳኙን እርምጃ የወሰዱ ኣርበኛ ናቸው። ከእዚሁ ጋር የተያያዘ በኮምፕዩተር ኣዳዲስ ኣከታተቦችን፣ የፊደል ኣመዳደቦችና ገበታዎች ፈጥረዋል። ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት ፊደላቸውም የዩኒኮድ ፊደል ሆኗል። በተጨማሪም በሳይንቲስትነት፣ ተመራማሪነትና ሥራ ፈጣሪነት ለኣበረከቱት ዕውቅና የምንሰጠው በታላቅ ኩራት ነው። የኣበረከትነውም ዕውቅና በማሕበረሰቡ የዲሬክተሮች ቦርድና በሁሉም ኢትዮጵያውያን ስም ወሰን ከሌለው ምስጋና፣ ፍቅርና ኣድናቆት ጋር ነው። የኢትዮጵያ ቅርስና ውርስ ማሕበረሰብ በሰሜን ኣሜሪካ ዶክተሩን የበዓሉም የክብር እንግዳ ኣድርጓል።" ከእዚህ በላይ የቀረበውን የተናገሩት የኢትዮጵያ ቅርስና ውርስ ማሕበረሰብ በሰሜን ኣሜሪካ ፕሬዚደንት ኣቶ የሺጥላ ኣርኣያ ድርጅቱ ሰባተኛውን ዓመታዊ በዓል ኅዳር ፲ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም. ሲልቨር እስፕሪንግ፣ ሜሪላንድ ሲያከብር ስለዶክተሩ የተናገሩት ነበር። [278] Archived ሴፕቴምበር 2, 2018 at the Wayback Machine [279]

እንገር ለማስተካከል

ጥጆች ወተት ሲጠቡ ወተቱ ትንሽ ይዘት የኣለው ወተት ኣንጀት ውስጥ በቀጥታ ስለሚገባ ወደ ሦስት ሳምንታት እድሜ ሞልቷቸው ሳር መቀንጠስ እስከሚጀምሩ ድረስ ጨጓራ (Rumen)፣ ኣይነበጎ (Reticulum) እና ሽንፍላ (Omasum) ሥራቸውን ኣይሠሩም የሚል እምነት በዓለም ስለነበረ ኣልጠባ ያሉትን እስቶማክ ቲዩብ በሚባል ቱቦ መጋትም ኣይጠቅምም የሚባል እምነት ነበር። ምክንያቱም እንቦሳዎች ወተት ሲጠቡ በተፈጥሮ ኢሶፋጂያል ግሩቭ የሚባል የጉሮሮ እጥፋት በኩል ወተቱ በኣቋራጭ ከጉሮሮ ወደ ወተት ኣንጀት (Abomasum) ስለሚገባ ነው። [280] Archived ማርች 2, 2015 at the Wayback Machine [281] በኣፍ በሚገባ የጨጓራ ቱቦ ውስጥ በደቂቃ ጨጓራ ውስጥ የተንቆረቆረ ኣንድ ጋለን ያህል እንገር ወደ ኣንጀት ሄዶ ደም እንደሚገባ በምርምር በማረጋገጥ በመድኅን ማነስ (ፓሲቭ ኢምዩን ደፊሸንሲ / Passive Immune Deficiency) መነሻነት ሲከሰቱ የነበሩ ችግሮች (እ.ኤ.ኣ. በ፲፱፻፳፪ ቢደረስበትም) [282] በዶ/ር ኣበራ ሞላ ለመጀመሪያ ጊዜ እ.ኤ.ኣ. በ፲፱፻፸፯ ተወግደዋል። መረጃውም 182 ገጾች በኣለው መጽሓፋቸው በእንግሊዝኛ ቀርቧል። [283] [284] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine [285] [286] [287] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine [288] ከእዚያም ወዲህ ምርምራቸው በሌሎች ምርምሮች ተረጋግጠዋል። [289] [290] [291] [292] [293] [294] [295] [296] Archived ማርች 27, 2016 at the Wayback Machine [297] Archived ኦክቶበር 9, 2011 at the Wayback Machine [298] [299] በእዚህ የተነሳ እንገር (Colostrum) ባለማግኘት ሊሞቱና ሊታመሙ የሚችሉትን እስቶማክ ቲዩብ ወይም ኤሶፋጊያል ቲዩብ በሚባሉ ቱቦዎች በመጠቀም እንገሩን ጥጃው እንደተወለደ በመስጠት ሕይወቱን ማዳን ተችሏል። [300] እንቦሳውም እንገሩን ቶሎ ከኣላገኘ ጀርሞችም ከሆድ እቃ በቀጥታ ወደ ደም ስለሚገቡ ኣደጋው ስለሚጨምር እንገሩን ጥጃው እንደተወለደ ከኣላገኘ ወደ ደም መግባቱም ቀስ በቀስ ስለሚቀር ጊዜና የእንገሩ መጠን ወሳኞች ናቸው። የእንቦሳ ጨጓራ እንደሚሠራ ለመጀመሪያ ጊዜ በማረጋገጥ የጥጃውን ትብብር ሳይጠይቅ በምርምራቸው የእንገር መጠንንና ጊዜውን ሰው እንዲወስን ሆነ። ስለዚህ ኣልጠባ ያለን ጥጃ ዝም ብሎ መመልከትና መበሳጨት ቀርቶ ወተት ኣንጀት የማይችለውን እንገር ጨጓራ ውስጥ በማስቀመጥ ጥጃው እራሱን እንዲረዳ ኣደረጉ። ከብዙ ላሞች ተሰብስቦ ተደባልቆ የተፈረዘ እንገር በክብደት መጠን እየተለካ በቱቦ በኣንድ ደቂቃ ለጥጆች እንደተወልዱ የተሰጠው ኣንድ ጋለን ያህል እንገር በ፳፬ ሰዓታት ውስጥ በቂ መድኅን ደሙ ውስጥ እንዳስገኘና እንገሩን በፈቃዳቸው እያረፉ ብዙ ሰዓታት ሳይፈጁ ከጠቡት ጋር እኩል መሆኑን ኣረጋገጡ። የዶ/ር ኣበራ የምርምርው ውጤት ትልቅ ፈውስ ሊሆን የቻለው ጊዜ፣ ይዘትና መጠንን በኣንዴ በማካተት ስለገላገለ ነው። [301] የጊዜ ጥቅም ጥጃው እንደተወለደ የተሰጠውን ወደ ደሙ ስለሚያስገባ ሲሆን በእዚህ ጊዜም ወደ ደም እንደመድኅኑ የሚገቡትን ጀርሞች ለመቅደምም ነው። እንገሩም ከኣንጀት ወደ ደም የሚገባው ጥጆች እንደተወለዱ ሲሆን ቀስ በቀስ እየቀነሰ በ24 ሰዓታት ውስጥ መተላለፉ ይዘጋበታል። በቱቦው ወደ ጋለን እንገር መስጠት ስለሚቻል በቂ መድኅን እንደተወለዱ መስጠቱ የበሽታ መከላከዎች በብዛት ወደ ደም ስለሚገቡ ነው። [302] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine ስለዚህ ጥጃው እንደተወለደ መስጠቱ እንጂ መቆየቱ እንገር ማባከን ነው። ጥጃው ቢጠባም ወተት ኣንጀት በቂ ይዘት ስለሌለው የሚፈለገውን ያህል ሊጠባም ስለማይችል ጨጓራ እንደሚሠራ ስለኣረጋገጡ ኣንድ ጋለን እንደተወለደ በቱቦው መስጠት ስለቻሉ እንገሩ ውስጥ በቂ የመድኅን መጠን እንዳለ የሚጣራበት ኣስፈላጊ ነው በማለት ቀላል የምርመራ ዘዴ ለመጀመሪያ ጊዜ ፈጠሩ። ምክንያቱም የሁሉም ላሞች እንገር የበሽታ መከላከያ ፕሮቲኖች መጠን እኩል ስለኣልሆነ ነው። በተጨማሪም ሬፍራክቶሜትር የሚባል መሣሪያ የእንገርን መድኅን መጠን ለመገመት እንደሚጠቅም የምርመራ ጽሑፍ ጻፉ። [303] [304] [305] [306] Archived ኦገስት 11, 2017 at the Wayback Machine ግን ኣንድ ጥጃ በቂ መድኅን የሚኖረው እንደተወለደ ኣንድ ጋለን እንገር ስለኣገኘ ብቻ ሳይሆን በቂ ኢምዩኖግሎቡሊን ስለኣገኘ ስለሆነ እንገሩ ውስጥ በቂ እንዳለ ገበሬው ከላሟ ሳይለይ በኣንድ ደቂቃ እንገሩን መርምሮ የሚያጣራበት የምርመራ ዘዴ ፈጥረውና ኣስፈላጊነት ኣስተዋወቁ። የሥጋ ላሞች ግን ስለማይታለቡ ያንኑ የምርመራ ዘዴ የጥጆችን ደም በመውሰድ ገበሬው ሜዳ እንዳለ በኣንድ ደቂቃ ጥጃው በቂ መድኅን እንዳገኘ እንዲያጣራና ከኣላገኘ ቱቦውን በመጠቀም ማረም እንደሚቻል ኣቀረቡ። እንገሩን በሚገባ ለመጠቀም በኣካባቢው ለኣሉት በሽታዎች ላሞቹን በመክተብ ጥጆቹ ትክክለኛ መከላከያውን ከእንገሩ ያገኛሉ። (ዶክተሩ በተለይ የቫይረስ በሽታዎች ኣዳዲስና የተለመዱ መክተቢያዎችን የመሥራት የብዙ ዓመታት ልምድ ኣላቸው።) [307] የምርምር ውጤቶቻቸውም ጥቅም በሌሎች ሲረጋገጡ ኣርባ ዓመታት ኣልፈዋል። [308] [309] [310] Archived ኦገስት 11, 2017 at the Wayback Machine [311] [312] [313] [314] [315] [316] [317] በቂ መከለከያ ኣለማግኘት Failure of Passive Transfer (FTP) ይባላል።

እዚህ ላይ ሊታወቅ የሚገባው ግን መድኅን ስለሌለ የግዴታ ይሞ'ታል ማለት ኣለመሆኑንና (ኤድስ ያለበት ሁሉ እንደማይሞት ዓይነት) ሲጠባ የታየ ጥጃ ሁሉ በቂ መድኅን ኣገኘ ማለት ኣለመሆኑን ነው። የእንገሩ ጥቅም በኣካባቢው ቆሻሻነት፣ ጥጆቹ ጀርሞቹን ስለሚበሉና የበሽታዎች መኖር ናቸው። ሲጠባ የታየም ይሁን ያልታየ ጥጃ ጊዜ እንዳያልፍበት ደሙን በመመርመር የመድኅኑ መጠን እንዲጣራበት የእንገር መድኅን መመርመሪያ ኣዲሱን ዘዴያቸው ለጥጃውም ደም መመርመሪያ እንዲያገለግል ኣደረጉ። [318] ምርመራዎቹም ኣስፈላጊ ሆነው ስለኣገኙዋቸው መፍትሔውን ፈጥረው ኣቀረቡ። ስለ ምርምር፣ ግኝቶቻቸውና ኣስተዋጽዖ ከታዋቂ የዓለም የእንስሳት ሓኪሞች ኣንዱ ከመሆናቸውም ሌላ [319] [320] [321] [322] በሽታን መከላከል ሲቻል በማከም ብቻ ስለማያምኑም የኣሜሪካና እንግሊዝ ፓተንቶች (የባለቤትነት መታወቂያ) ኣግኝተዋል። የግኝቶቻቸው ጥቅሞች [323] እዚህ በተጠቃቀሱት የተወሰኑ ኣይደሉም፦ ምሳሌ 4,501,816 ፓተንታቸው ሌሎች ፓተንቶችን ጠቅሟል። [324] [325] በዶ/ር ኣበራ የምርምር ውጤት ዘዴ የተነሳ በኣሁኑ ጊዜ እያንዳንዱ ጥጃ እንደተወለደ እንገር በቱቦው የሚሰጠው ትላላቅ እርሻዎች ውስጥ ብቻ ኣይደለም። [326] [327] [328] Archived ኦገስት 1, 2016 at the Wayback Machine [329] [330] [331] [332] ብዙ ትላልቅ እርሻዎች ውስጥ ጥጆች በተወለዱ በሁለት ሰዓታት ውስጥ የሆድ ቱቦን በመጠቀም እንገር ይሰጣቸዋል። [333] [334] የእንገር ብዛት ብቻ ሳይሆን ጥራቱንም ማወቅ ኣስፈላጊ ሆኖ ስለኣገኙት መመርመሪያ ዘዴ ፈጥረውለት ዘዴውም ወደ መሣሪያ ተቀይሮ የእንገርን ኢምዩኖግሎቡሊን መጠን መገመት የገበሬዎች የዘወትር ሥራ ሆኗል። እንገር ሌሎች ጥቅሞችም ኣሉት። ለምሳሌ ያህል እንደተወለዱ በቂ መድኅን የኣገኙ ጥጆች ሲያድጉ ብዙ ወተት ይሰጣሉ። [335] ኣሜሪካ ውስጥ ብቻ በእየዓመቱ ወደ 39 ሚሊዮን ጥጆች ስለሚወለዱ [336] የተለያዩ እንስሳት ሳይቆጠሩ [337] [338] ምን ያህል ሕይወት እንደተረፈ ግምቱን ለኣንባቢ መተው ይሻላል። የዶክተሩን ዘዴ ዓለም እየተጠቀመበት [339] [340] ኣሜሪካ ውስጥ ብቻ ብዙ ቢሊየን ዶላሮች ሲይስተርፉ ኣርባ ዓመታት ሊሞሉ ነው። [341] የኣንድ ጥጃ ዋጋ 70 ፓውንድ ቢሆንና በየዓመቱ በዓለም ላይ የሚያልቁትን ጥጃዎች ብቻ መቶ ሚሊዮን በማትረፍ የዶ/ሩ ምርምር ሥራ ዋጋ በኣለፉት 40 ዓመታት ብዙ ቢሊዮን ነው። [342] ሌላ ምሳሌ ለመጥቀስም ያህል የእንገር መድኅን መጠን ሬፍራክቶሜትር (Refractometer) በሚባል መሣሪያ መገመት እንደሚቻል የጻፉትም [343] ከ፴፮ ዓመታት በኋላ ዋቢ እየሆነና መጥቀሙ ነው። [344] [345] [346] [347] [348] [349] [350] [351] Archived ኦገስት 19, 2016 at the Wayback Machine [352] [353] ዘዴዎቻቸውም እንደኣስፈላጊነታቸው ለተለያዩ ለማዳና የዱር እንስሳት ጥቅም ሥራ ላይ እየዋሉ ናቸው። ዶክተሩ በተማሩበት የሕክምና መስክ ብዙ ሚሊዮኖች ሕይወቶች ማትረፍ ስለቻሉ ፈጣሪናን የረዷቸውን ያልረሱ ደስተኛ ናቸው። የላም እንገር ለሰው ሕክምናም እየጠቀመ ነው። [354] [355]

ሕክምና ለማስተካከል

የምርምር ግኝታቸውም ጥጆች ሲታመሙም ኣዲስ የመድኃኒት፣ ምግብና ፈሳሽ መስጫ ዘዴ ሆኖ ተገኝቷል። [356] ለምሳሌ ያህል የእንቦሳ ተቅማጥ እንደ ስው ኮለራ (Cholera) ብዙ ጥቃት የሚያደርሰው ከኣካል ውስጥ ውሃ እየተመጠጠ ስለሚያልቅ ስለሆነ ውሃውን ለመተካት ጥጆቹን ሓኪም ቤት መውሰድና ማሳከም ገበሬውን ብዙ ወጪ ያስወጣ ነበር። ከዶክተሩ ግኝት በኋላ ግን ትክክለኛውን የጨውስኳር መጠን ያለውን ንፁህ ውሃውን በቱቦው ማጠጣት ስለሚቻል ወጪ ቀንሷል። [357] Archived ጁን 21, 2010 at the Wayback Machine [358] [359] Archived ዲሴምበር 4, 2012 at the Wayback Machine ዶክተሩ ለሕክምና ሞያቸው [360] ካበረከቷቸው ኣንዱ ይኸን ኣዲስ የሕክምና ዘዴ ማቅረባቸው ነው። ከእዚያም ወዲህ ጥቅሙ ቢጋነንም [361] የእንገር ንግድ ኣዳዲስ የዓለም ገበሬዎችና ኣምራቾቹ የገቢ ምንጭና የመድኅን የሕክምና ዘዴ ከመሆኑ ሌላ የሰው እናት እንገርና ወተትም ኣጠቃቀምም ተሻሽሏል። [362] [363] [364] የምርምር ውጤታቸውም ጤናማ እንስሳትን ለማሳደግ መራዳትና [365] ሓኪሞችንም ከመጥቀም ሌላ [366] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine [367] ለሌሎች እንስሳትም ሥራ ላይ ውሏል። ምሳሌ - [368] [369] [370] [371] [372] [373] [374] Archived ዲሴምበር 24, 2013 at the Wayback Machine [375]

እንግሊዝን የ፲፮ ቢሊዮን ዶላር ያካሰረውን የላም ጉንፋን ወረርሽኝ (Foot-and-mouth-disease) ከኣስቆሙትና ከኣጠፉት ኣንዱ በመሆናቸው ዶክተሩ [376] ሁለት የጀግንነት ሽልማት ከዩናይትድ እስቴትስ መንግሥት ተሰጥቷቸዋል። [377] በሽታው ኢትዮጵያ ውስጥ ኣለ። [378] ኢትዮጵያውያን ሥጋ ለውጭ ኣገሮች በመሸጥ ብቻ ብዙ ቢሊዮን ብር ገቢ ሊያገኙ ስለሚችሉ መጀመሪያ ኣደገኛ የእንስሳት በሽታዎችን ማጥፋት ይጠበቅባቸዋል። [379] እንደ በሽታውም ዓይነት ክትባት ትልቅ መሣሪያ ነው። የሰው ልጅ በመተባበር የሰውን ፈንጣጣ (Smallpox) እና የቀንድ ከብትን ደስታ (Rinderpest) በሽታዎች ክትባትን በዋናነት በመጠቀም ከዓለም ኣጥፍቷል። ዶ/ር ኣበራ ኣዳዲስና የተለመዱ ክትባቶችን ኣምርተዋል፦ Equine Encephalitis [380], Equine Influenza [381], IBR [382] Vesicular Stomatitis [383], BVD [384] Orf [385] ጥቂት ምሳሌዎች ናቸው። የወፍ ኢንፍሉኤንዛና የመሳሰሉ በሽታዎች ሕዝቡ በሚገባ ማወቅና መዘጋጀት ይኖርበታል። [386] [387]

ኤድስ ለማስተካከል

ኤድስ (Acquired Immune Deficiency Syndrome / AIDS / ኣኳየርድ ኢምዩን ደፊሸንሲ ሲይንድሮም) በዓለም ላይ መሰራጨት እንደጀመረ ኤችኣይቪ (Human Immunodeficiency Virus)ን ክትባት እንደማይከላከለው በጊዜው ከሚያውቁት ሳይንቲስቶችና የበሽታ መከላከያ ክትባት ሠሪዎች ኣንዱ በመሆናቸው በሽታው ኢትዮጵያ ውስጥ ሊያስከትል ከሚችለው ጉዳት ለመከላከል ሕዝቡን ለማስተማር ባለ ኣራት ገጾች የመጀመሪያው የሆነውን ገለጻ በዓማርኛ ስለ ኤድስ በ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. ተርጕመው [388] እና ጽፈው [389] Archived ሴፕቴምበር 4, 2013 at the Wayback Machine [390] በገዛ ገንዘባቸው እያባዙና እየኣደሉ ቆይተው በኋላም በኢትዮጵያ ሪቪው መጽሔት ኣትመዋል። በእዚያን ጊዜ ስለ ግብረሥጋ ግንኙነትና ኮንዶም የሚጠቅሰውና እንዲሁም የታመሙትን መርዳት ይገባል የሚለው ጽሑፋቸው ከጊዜው ደካማ ኣስተሳሰብ የቀደመ ስለሆነ ተገቢውን ተቀባይነት ሳያገኝ ቸል ተብሎ የታለፈበት ጊዜ ስለነበረ በሽታውን በምርምር በተረጋገጡ ዕውቀትና ትምህርት መከላከል [391] ስለኣልተቻለ ከፍተኛ ጉዳት ኣድርሷል። ይኸንኑ ጽሑፍ ሕዝቡ እንዲያነብበት GeezEdit Amharic P [392] የሚባል የኮምፕዩተር ፊደላቸውን በ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. በነፃ የሰጡት ስጦታ ኣሁንም ኢንተርኔት ላይ ስለኣለ ኣንዳንዶቹ ኣልደረሱበትም እንጂ ደርሰውላቸው ነበር። ጽሑፉ ሲጻፍ ኤች ኣይ ቪ ቫይረስ የተገኘባቸው የዓለም ሕዝቦች ኣንድ ሚሊዮን ሆኖ ሳለ እስካሁን በበሽታው ሳቢያ የሞቱ ሰዎች ቍጥር ፴፮ ሚሊዮን ደርሷል። [393] በ፳፻፰ ዓ.ም. 36 ሚሊዮን ያህል ሕዝቦች ቫይረሱ ኣለባቸው።

ሰሞኑን ኃምሳ ሁለት ከመቶ ዩናይትድ እስቴትስ ውስጥ የኣሉ ኢትዮጵያውያን ኤድስ ኣለባቸው የሚባል ወሬ እየተናፈሰ ነበር። ለምሳሌ ያህል መቶ ሰዎች ተመርምረው ኃምሳ ሁለቱ ኢትዮጵያውያን ውስጥ ኤድስ ቢኖርባቸው ዩናይትድ እስቴትስ ከኣለው ወደ ሚሊዮን ከሚጠጋ ሕዝብ ኣምስት መቶ ሃያ ሺህው ኤድስ ኣለው ማለት ኣይደለም። እነዚህ ሁለቱ ኣነጋገሮች የተለያዩ ናቸው። የወሬው ትክክል ኣለመሆንና መረጃው ከዶ/ር ገበየሁ ተፈሪ ጋር በምናላቸው ስማቸው ቃለምልልስ እዚህ ቀርቧል። [394] ኣንድ ሌላ ትንሽ ጥናትም እንደሚያሳየው ኢትዮጵያ ውስጥ ቫይረሱ ከተገኘባቸው መካከል ከመቶው 28 እንዳለባቸው ኣያውቁም። [395] ይህ ከመቶ 28 ኢትዮጵያውያን ውስጥ ቫይረሱ ኣለባቸው ማለት ኣይደለም።

ነፃ መክተቢያ ለማስተካከል

ከቅርብ በረከትም በግዕዝኤዲት ኦንላይን (Free Typing GeezEdit Amharic Online) http://freetyping.geezedit.com Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine GeezEdit,[1] ዓማርኛ [396] ሕዝቡ በነፃ በዓማርኛ ዊንዶውስ እና ማክ ኮምፕዩተሮች ውስጥ መጻፍና የዓለም ድረገጾችንና የመሳሰሉትን (ኢንተርኔት) በዓማርኛ መፈለግ እንዲችል ኣበርክተዋል። (Amharic) [397] Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine፣ ጉግል በዓማርኛና እንግሊዝኛ፣ [398] [399] ያሁ እና ቢንግ በዓማርኛ መፈለጊያም ይገኙብታል። [400] ቪድዮም እዚህ ኣለ። [401] እነዚህ የኣንድ ሰው ብቻ ሥራዎች ስለኣልሆኑ ለሚመለከታቸው ሁሉ ምስጋና ይድረስልን።

የድረገጹ ፩ኛ ጥቅም ሌላ መክተቢያና እንደ ማይክሮሶፍት ወርድ [402] ወይም ፔጅስ [403] የመሳሰሉ ፕሮግራሞችን (ተጠቃሚው ተመዝግቦ እያንዳንዱን በብዙ ሺህ ብር መግዛት ስለማይችል በእራሱ ፊደል መጠቀም እንዳይቸግረው) ኣማራጭ በማበርከት በዊንዶውስ እና ማክ ኮምፕዩተሮች በዓማርኛ ለመጻፍ ነው። ከእዚያ ጽሑፉ ኮፒ ተደርጎ ሌላ ሥፍራ ይለጠፋል። [404] የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች ጽሑፎቻችንንና የመሳሰሉትን ወደ ኢንተርኔት ማስገባትና እነዚህኑ ፈልገን ማግኘት ካልቻልን የሚከተለው ኋላ ቀርነት ቀላል ላይሆን ይችላል። ፪ኛው ኢንተርኔትን በዓማርኛና እንግሊዝኛ ወይም ቀላቅሎ ለመፈለግ በኮምፕዩተር ያገኘነውን ኣዲስ ኣጠቃቀም በሚገባ እንድንጠቀምበት ነው። ይህ ቃላትን ጽሑፍ ውስጥ ለመፈለግና ለመተካትም ይጠቅማል። ሕዝቡ በቀላሉ መጻፍ ስለሚችል በሰለጠነበት የጽሑፍ ኣሠራር እንዲቀጥሉ ሲሆን ፫ኛው ጥቅም ኣንድ የዓማርኛ ጽሑፍ በቀለሙ የተጻፈ መሆኑን ለማረጋገጥና እንደኣስፈላጊነቱ ለማረም ነው። በግዕዝ ቀለም ያልተጻፈ ጽሑፍ ኮፒ ተደርጎ ገጹ ላይ ሲለጠፍ ዝብርቅርቅ እንግሊዝኛ ሆኖ ይታያል። ፬ተኛ ጥቅም ኣንዳንድ ምሁራን እንደ “ዝሆን”፣ “ኣኣ”፣ “ክኅሎት”፣ “ድድ የመሳሰሉትን የዓማርኛ ቃላት የማያስጽፉ ድረገጾችንና የመሳሰሉትን ለመጻፊያ ከማቅረብ እንዲቆጠቡ ነው። ኣንዳንዶቹ “ኵ”ን ኣጥፍተው በ“ክው” እንደ እንግሊዝኛ እስፔሊንግ መክተብና ወጪ መጨመር ቢፈልጉም “ኵ”ን መጻፍ የማይችሉ ኣሉ። "ሥዕል"ን በ"ሥእል" መተካትም ችግር ኣለው። ከእነዚሁ መካከል የእነ “ሐ” እና “ኀ” ቤቶች ቀለሞችን የ“ሀ” ሞክሼዎች ስለሆኑ መቀነስ እየፈለጉ ኣንዳንዶቹ “ትህትና”፣ “ትስስር”፣ “ግግር” እና “ትዝታ” የመሳሰሉትን ቃላት መክተብ ስለማይችሉ ዓማርኛውን በእንግሊዝኛ ለመክተብ ሲባል ቃላቱን ማጥፋት ይፈልጋሉ። እነዚህ ምሳሌዎች ያለተቃውሞ ለብዙ ዓመታት ኣሉ። ይህ ገጹን እየተጠቀሙ የኣሉ ኢትዮጵያውያን ምሁራን ለዓማርኛ ፊደልና ቋንቋ መጥፋት ደንታ እንደሌላቸው የሚያሳይ ኣሳፋሪ መረጃ ነው። ኣንዳንዶቹ ግዕዝኤዲት በሁለት መርገጫዎች የሚያስከትበውን “ስስ” ቃል የሚከትቡት በሰባት መርገጫዎች ሲሆን “ፄ” ቀለምን ለመክተብ እስፔሊንጉን ማስታወስና ስድስት መርገጫዎች መጠቀም ቢያስፈልግም ሁሉንም የዓማርኛ ፊደላት ባዶ ስፍራ እየጨመሩ እንኳን ኣያስከትቡም። ዓማርኛውን መክተብ ሳይችሉ ሌሎች ቋንቋዎችን የጨመሩ ኣሉ። ምክንያቱም ከግዕዝ ቋንቋ ቀለሞች በሰተቀር ሌሎቹ ከዓማርኛው ቀለሞች በላይ ብዛት ስለኣላቸው ነው። ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና እንዳገኘ እያወቁ ዛሬም በእየዓይነቱ የፊደል ቁርጥራጭ የሚያቀርቡም ኣሉ።

፭ተኛው ጥቅም ሞክሼዎችን የማይወዱ ደራስያን ከሚወዷቸው ጋር እያምታቱ በተገኘው እንዳይጠቀሙ ይራዳል። “ሀ” የ“ሃ” እንዲሁም “አ” የ“ኣ” ሞክሼዎች የሚመስሏቸው ኣሉ። “ኳ” እራሱን የቻለ ሞክሼ የሌለው ቀለም ነውና ጊዜና ስፍራ ማባከን ስለሆነ በ“ኩዋ” ወይም “ክዋ” መዘርዘርም ፊደል ለመቀነስ በታይፕ መጻፊያ ዘመን በኣማራጭነት የቀረበና ያኔም ቢሆን ተቀባይነት የኣላገኘ ኣሁንም ቢሆን ጊዜው ያለፈበት ኋላ ቀር ኣስተሳሰብና የማያስፈልግ ግድፈት ነው። የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና “ኳ”ን ሲከትብ የነበረው “ካ” ቀኝ እግር ስር መሥመር በመጨመር በኣሌለና የተሳሳተ ቀለም በመጠቀም ነበር። የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና “ቋ”ን ሲከትብ የነበረው “ቀ” እግር ስር መሥመር በመጨመር በኣሌለና የተሳሳተ ቀለም በመጠቀም ነበር። ፮. በነፃ እየታደሉ በኣሉ የማያዛልቁ ኣከታተቦች ሕዝብ መታለሉ እንዳይቀጥልና እየተነገረውም እነዚያን ለምዶ በኋላ በትክክለኛ ሳይንሳዊ ኣከታተብ መጠቀም ተቸገርኩ እንዳይል ግዕዝኤዲት ይራዳል። ምክንያቱም በተገኘው መክተቢያ ተምሮ በኋላ በግዕዝኤዲት ለመሥራት ሲሞከር ሌላውን ኣጠቃቀም ለመተው ኣስቸጋሪ ስለሚሆንና ምንም ዓይነት ኣከታተብ ለማያውቅ ግዕዝኤዲትን መማር ቀላል ስለሆነ ነው። በተጨማሪም ዓማርኛውን በቍልፎቹ ብቻ መክተብ ስለኣልቻሉ ቀለሞቹን ከ“ሀ” እስከ “ፖ” ደርድረው በማውስ ቀስት በመጠቆም እንዲከተቡ ማድረግ ኣያስፈልግም። ፯. ዓማርኛውን በላቲን ቀለሞች መክተብ ኣስፈላጊ ሳይሆን በተገኘው የእንግሊዝኛ እስፔሊንግ እየጻፉ ያሉትን ኣንዳንድ ጉራማይሌ ምሁራን በሚገባ በሚያውቁት ዓማርኛ ፊደልና ቋንቋቸው እንዲጽፉና እንዲያነቡ ያገለግላል። እንግሊዝኛ እስፔሊንግ ከባድ ነገር በመሆኑ ዓማርኛ እንግሊዝኛውን ሊጠቅም ስለሚችል በእንግሊዝኛ ማድበስበስ የለብንም። [405] ግዕዝ ድምፃዊ ፊደል ስለሆነ ለመነበብም ሆነ ለመከተብ እስፔሊንግ ስለማያስፈልገው ሕዝቡ ዓማርኛውን በላቲን እስፔሊንግ እንዲከትብ በብዙ መርገጫዎች ማስቀጥቀጥም ሳይስፋፋ ዓማርኛውን በዓማርኛ ፊደል ለመክተብ ግዕዝኤዲት ይጠቅማል። ለምሳሌ ይህል “ያመት” የሚለውን ቃል በ“yamet” እየጻፉ እንግለዝኛ ቃሉ በማወስ ቀስት እንዲመረጥ ወይም የባዶ ስፍራ ቍልፍ ሲነካ እንግሊዝኛውን ወደ ኣማርኛ በመቀየር “ያመት”ን እንድንጽፍ የሚገልጉ ፈረንጆች ኣሉ። እነሱ እንግሊዝኛውን የሚጽፉት ከኣንዱ ፊደል ወደ ሌላ በመቀየር ወይም ቃላትን በማውስ ቀስት በመልቀም ስለኣልሆነ ለዓማርኛ ተጠቃሚው እንዳልተጨነቁ ያሳያል። የ“ጰ” የዓማርኛ Latin (ቁቤ) ኣነባበብና ኣከታተብ ካፒታል “ፒ” ("P") ነው ሲባል ተከርሞ [406] [407] [408] በቅርቡ ወደ “ፒ” (“p”) እና ነቍጥ (“.”) ተቀይሯል ይባላል። ቴክኖሎጂውን ለዓማርኛ መፍጠር እንጂ ዓማርኛውን ለቴክኖሎጂው ኣያስፈልግም። ለላቲን ከተሠራ ቴክኖሎጂ ጋር እንዲሄድና በዓማርኛው ኪሳራ ላቲኑን ለማዳበር ሲሞከር የላቲን ተናጋሪዎች ባይናገሩ ባይገርምም የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች በዝምታ እንደማይቀበሉት ዶክተሩ ኣሳይተዋል። ፰. ግዕዝኤዲት የዓማርኛና እንግሊዝኛ መክተቢያ ነው። [409] ፈረንጆች ቋንቋዎቻቸውን በግዕዝ ፊደል እንዲከትቡ ኢትዮጵያውያን ኣልጠየቁም። ኢትዮጵያውያን ቋንቋዎቻቸውን በላቲን ፊደል እንዲከትቡ የሚፈልጉ ጥቂት ፈረንጆችና ኢትዮጵያውያን ግን ኣሉ። ኣንዳንድ ኢትዮጵያውያንም ነገር ስለተማታባቸው ቋንቋዎቹን መቀላቀልም ስለጀመሩ ዓማርኛውንም ሆነ እንግሊዝኛውን በሚገባ የማይናገርና የማይጽፍ ትውልድ እንዳይፈጥሩ ግዕዝኤዲት ይራዳል። [410] Archived ሜይ 7, 2018 at the Wayback Machine

፱. ኢትዮጵያ ለብዙ ሺህ ዘመናት ከነፃነትዋ ጋር ጠብቃ ያቆየቻቸው ቋንቋዎችዋና የተሟሉት ቀለምዎችዋ ዛሬም በእኩልነት እያንዳንዱ ቀለምዋ በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ብቻ እንዲከተብ ተደርጎ ተከባብሮና ተጋብቶ የኖረው ሕዝብ ፍላጎትና እኩልነት በኣብሻ ሥርዓት ቴክኖሎጂ ምሳሌ በግዕዝኤዲት ቀርቧል። [411] የኣንዳንዶቹን ኣንድ ቋንቋ ቀለሞች በኣራት መርገጫዎች የሌላውን በስድስት መክተብ ወይም እንደሌሉ መርሳት የለም። ፲. የምሁራንና ቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ሥራና ጥቅም ለኣለ ችግር መፍትሔ መፍጠር ነውና ዶ/ር ኣበራ ለእነዚያ የሚጠቅሙ ሠርተዋል። ኣንዳንድ የግዕዝ ተመራማሪዎች ግን በተሳሳተ ዓላማቸው ፊደሉ ለላቲን ፊደልና ገበታ እንዲስማማ መክተቢያ ሴራ መፍጠር ስለሆነ ግዕዝኤዲት ሳይንሳዊ ዓላማን በመሳት እንዳይቀጥሉ ትክክለኛውን ኣስተሳሰብ ያስገነዝባል። በቅርቡ ኣንድ የግኝታቸው ትክክለኛ ኣከታተብ የገባቸው ኢትዮጵያዊ “ዶ/ር አበራ ምሥጋና ይግባውና የአማርኛ ጽሑፍ ትየባ ፍጥነቴ ከእንግሊዝኛው አያንስም” በማለት ጽፈዋል። ፲፩. ግዕዝኤዲት በዓማርኛና እንግሊዝኛ ኣከታተብ ለመማር ይጠቅማል። በዓማርኛ በብዛት የምንጠቀምባቸው ቀለሞች ሳድሳን ስለሆኑ በኣንድ መርገጫ ይከተባሉ። ሳድሳን ዓማርኛ ጽሑፍ ውስጥ በብዛት ኣንደኛ ስለሆኑ ሳድሳንን በሁለት መርገጫዎች መክተብ በማያስፈልግ ድካም እራስን መበደል ነው። በብዛት ኣጠቃቀም ሁለተኛ የሆኑት ለሁለቱ ዝቅ መርገጫዎች ተመድበዋል። ለግዕዝ ተጠቃሚዎች ኢንተርኔት ላይ በነፃ ለመማርያ የቀረቡ እንግሊዝኛ ኣከታተብ መለማመጃዎችን በመጠቀም ያለኣስተማሪ በፍጥነት መክተብ መማር ይቻላል። [412] “አ”፣ “ሰ”፣ “ደ” እና “ፈ” በግራ እጅ ጣቶች “ጀ”፣ “ከ”፣ “ለ” እና “ጠ” በቀኝ እጅ ጣቶች ይከተባሉ። ምሳሌ [413] [414] [415] ፲፪. ዶ/ር ኣበራ ኮምፕዩተራይዝ ያደረጉትና የታገሉለት ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና ስለኣገኘ የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ቅጥልጥል ፊደል እንዲቀር ቢጻፍም ዓማርኛ ነው ብለው ሲያቀርቡ የነበሩና ዛሬም የሚያቀርቡ ኣሉ። [416] ግዕዝኤዲት የሚሠራው በትክክለኛ የግዕዝ ፊደላት ስለሆነ ልዩነቱን የማያውቁ እንዳይታለሉ ይጠቅማል። በትክክለኛ የግዕዝ ቀለሞች የተጻፉ ብዙ መጽሓፍት ምሳሌዎች እዚህ ኣሉ። [417]

፲፫. የግዕዝና ላቲን ኣከታተብ ግንኙነት የላቸውም። በጥቂት የላቲን ቀለሞች እስፔሊንግ ብዙ የሆኑትን የግዕዝ ቀለሞች መክተብ መሞከር ላቲኑን ለመጥቀም ወይም ግዕዝን ለማዳከም ካልሆነ ጥቅም የለውም። ግዕዙን በላቲን እስፔሊንግ መክተብ ኣለባችሁ ብሎ ኢትዮጵያውያንን ያስገደደ የለም። በላቲን “b” እና “o” ሲረገጡ “bo” ይታያሉ። በግዕዝ “bo” ሲረገጡ “ቦ” ቀለምን ሊያስከትቡ ይችላሉ። “bo” ማለት “ቦ” ኣይደለም። እንዲሁም “ቦ” “bo” ኣይደለም። በ”ቦ” ምትክ “bo” እየጻፉ የዓማርኛውን ቀለም ትተው ዓማርኛውን በላቲን ፊደል የሚጽፉ ተጠቃሚዎች ቍጥር እየጨመረ ነው። [418] [419] ይህ የዓማርኛ ቁቤ (Qubee) ስለሆነ ፊደሉንና ቋንቋውን ሊያዳክማቸው ይችላል። [420] [421] [422] በዓማርኛ “ቾ”ን በሁለት መርገጫዎች ከመክተብ በ“cho” በሦስት መክተብ ኣያፈጥንም። ተጨማሪ ምሳሌ ከኣስፈለገ ኣንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዓማርኛ በላቲን ፊደል እንዲጻፍና በኣጻጻፉም በግዕዝ ፊደል ምትክ በላቲን ፊደል ጽፎ ያቀረበው ጽሑፍ በዓማርኛው በዓማርኛና ዓማርኛው በእንግሊዝኛ እዚህ [423] ኣለ። ዓማርኛን በላቲን ፊደል መጻፍና ማንበብ በኣንድ በኩል ዓማርኛንና ፊደሉን ማዳከም ሲሆን በሌላ በኩል ደካማና ኣክሳሪ የላቲንን ፊደል በዓማርኛው ፊደል መተካትን ለማስፋፋት ይመስላል። ይኸን ኣጠቃቀም ዶክተሩ ከሚቃወሙባቸው ምክንያቶች መካከል ዓማርኛን በላቲን ቀለሞች መክተብ ከዓማርኛው ቀለሞች የበዙ ቀለሞችን መጠቀምን ስለሚያስከትል ነው። የላቲን እስፔሊንግ ለቃላት እንጂ የግዕዝን ፊደላት ለመክተብ ኣይደለም። “የኢትዮጵያ ዘመን ኣቆጣጠር” የሚለውን ርዕስ በ15 የግዕዝ ቀለሞች ማስፈር ሲቻል “yeityoPya yezemen aqoTaTer” በሚለው 28 መርገጫዎችን በመጠቀም በ24 የላቲን ቀለሞች መተካት ድርብርብ መካሰር ነው። (ይህ ዘዴ ባዶ ስፍራ ቃላት መካከል እያስገቡ በዓማርኛም ሆነ እንግሊዝኛ የሌለ ኣከታተብን ማስተዋወቅን ቢያስከትልም ይኸንን ኣከታተብ የሚደግፉና እያስፋፉ ያሉ ጥቂት ኣይደሉም።) ግዕዝኤዲት የሚከትበውም ከእዚያ በኣነሱ መርገጫዎች ነው። ሙሉ ጽሑፉን በላቲን ፊደል ከመጻፍ ይልቅ በዓማርኛ ፊደል ማስፈር ብዛቱን ወደ 64.7 በመቶ ዝቅ ያደርገዋል። ይህ ውጤት በደካማ ኣከታተብ ዓማርኛና እንግሊዝኛውን ፊደላት ስናወዳድር ነው። በግዕዝኤዲት ኣከታተብ ይኸው ጽሑፍ በዓማርኛ የሚከተበው በኣነሱ መርገጫዎች ስለሆነ ከኣብሻ ኣከታተብ የተሻለ ኣከታተብ በኣሁኑ ጊዜ የለም። ይህ ለዓማርኛው ሲሆን ሌሎች የግዕዝ ፊደላት ሲጨመሩ ለእስፔሊንጉ ተጨማሪ መርገጫዎች ለሌላው ዘዴ ስለሚያስፈልጉ ግዕዝኤዲት ተወዳዳሪ የለውም። ለምሳሌ ያህል በሌላ ዘዴው እስፔሊንግ የዓማርኛው “ፄ” የሚከተበው በስድስት መርገጫዎች ስለሆነ ለጉሙዙ “ጼ” መክተቢያ ስምንት መርገጫዎችን መጠቀም ያስፈልጋል። ስለዚህ ትርፉ እጅ ማሳመም ነው። [424] ግዕዝኤዲት የዓማርኛውን ሆነ የጉሙዙን የሚከትበው በሁለት መርገጫዎች ነው። በሁለት መርገጫዎች መከተብ የሚችልን ኣንድ የግዕዝ ቀለም ከሦስት እንከ ስምንት መርገጫዎች በመጠቀም መክተብ የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ እንዳንሆን ያሰጋል። በትክክለኛ ኣከታተብ ላይ ያልተመረኰዙ ኣዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ኣገሪቷን ወደኋላ ሊጎትቱ ይችላል። [425] Archived ጁላይ 30, 2021 at the Wayback Machine ፲፬. የተቆራረጡ የኣማርኛ የጽሕፈት መሣሪያ ዓይነት ቀለሞችንና ያልተቆራረጡ ኣንድ የላቲን ፊደል የሚችለውን ቀለሞች እየመረጡና በሌሎች ዘዴዎች ሕዝቡን ሲያጉላሉ ከነበሩት ይገላግላል። ፲፭. ላቲን ለቀለሞቹ መክተቢያ የማይጠቀምበትን ከግዕዝ መጠየቅ ኣያስፈልግም፦ ምሳሌ በማውስ መክተብ። ምክንያቱም ግዕዝኤዲት ባይኖር ኖሮ ግዕዝ ሌሎች ችግሮች ውስጥ ሊወድቅ ይችል እንደነበረ ከእዚህ በላይ የተዘረዘሩት ሊቀሰቅሱን ይገባል። በእዚህ በተራቀቀው የኮምፕዩተር ዘመን የግዕዝ ፊደል በሳይንስና ቴክኖሎጂ [426] ተደግፎ ማደግ ያለበት ጊዜ ነው። ለምሳሌ ያህል ነፃው የግዕዝኤዲት መክተቢያው ገጽ እንደሚሸጡት የዊንዶውስና የኣይፎን ኣከታተብ ዘዴዎች ቀላል ኣይደለም። ፲፮. ቴክኖሎጂውና ሳይንሱ ስለቀረበለት በተለይ ኣንዳኣዳንዱ ስለጉዳዩ በሚገባ ዓውቆ ኣልገባኝም ከእሚል የፊደሉን መብት እንዲያከብርና እንዲያስከብር ነው።

፲፯. የእንግሊዝኛው የቅውኽርትይ (QWERTY) የኮምፕዩተር የፊደል ገበታ ወደ እጅ ስልክ ዞሯል። የግዕዙም እንደዚያው በግዕዝኤዲት ቀርበዋል። [427] ኣዲስ ኣሠራር በእጅ ስልክ ማስተዋወቅ ስለተጀመር ሕዝቡ ሁለተኛ ዙር መታለል ውስጥ እንዳይገባ ግዕዝኤዲት ይራዳል። ፓተንት እየተጠበቀ ወይም Patent Pending የሚለው ማሳሰቢያ ነፃው ግዕዝኤዲት ላይ ያለውና እዚህም ስለሚሸጠው ዓይነት ገለጻም ውስጥ የተጠቀሰው ሌላ ሰው በተሰጠው ወይንም በተሸጠለት እንዲጠቀም እንጂ ዘዴውን መገልበጥ ትክክል እንዳልሆነና በሕጉ መሠረት እንደሚያስቀጣም ለማስጠንቀቅ ነው። የግኝታቸውን እንግሊዝኛ ገለጻ በቍጥሩ US20090179778 [428] ወይም በሚከተለው ማያያዣ [429] ማግኘት ይቻላል። ግኝቱ መጀመሪያ የቀረበውና የኣተመው የዩናይት እስቴትስ መንግሥት ስለሆነ ከኢትዮጵያው ቅድሚያ ኣለው። ፲፰. የነፃ መክተቢያውን ፊደል ወደ እንግሊዝኛ ቀይሮ ለእንግሊዝኛ ቃላት ማቀነባበሪያም መጠቀም ይቻላል። ፲፱. ኢትዮጵያ የእራሳቸው የጥንት ፊደላት ከኣላቸው ጥቂት ኣገሮች ኣንዷ በመሆንዋ ይህ ለሕዝብዋ ትልቅ ኩራት ነው። ዋጋው ውድ ነው ተብሎ ሶፍትዌር በሕገወጥ የኮፕ ቅጂ መጠቀም ኢትዮጵያ ውስጥ ተስፋፍቷል ይባላል። ኣብዛኛው ኢትዮጵያዊ ልክ እንደእንግሊዝኛው ኮምፕዩተሩን የሚጠቀመብት ለተራ ጽሑፍ ነው። ሕዝቡ ኢንተርኔት እስከኣለው በነፃው ግዕዝኤዲት [430] Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine መጠቀም ስለሚችል መኃይምነት ሊኖር ኣይገባም። ግዕዝኤዲት በነፃ በዶክተሩ ስለተሰጠ ሕዝቡ ስፍትዌርም ከኣልፈለገ መግዛት ስለሌለበት እንደኣንዳንዶቹ የኣልከፈለበትን ሶፍትዌር ማባዛት የለባቸውም። ምክንያቱም በዓማርኛ ለመጻፍ የሚያስፈልጉት ኮምፕዩተርና ኢንተርኔት ብቻ ስለሆኑ ነው። [431] ፳. በኣለፉት ጥቂት ዓመታት ኢትዮጵያን እየጎዱ የኣሉ ከመንደር ኣስተሳሰብ መላቀቅ ኣቅቷቸው የዶክተሩን ሥራዎች ማስተዋወቅ ሲገባቸው ሲደብቁ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ዋናዎቹ ናቸው። ምሳሌ በተሰረቀ ሶፍትዌር ስማቸውን በየዲስኩ የሚጽፉ የሚያተኩሩት ስለተሰረቁባው ዘፈኖች እንጂ ስሞቻቸውን ስለጻፉባቸው የተሰረቁ የዓማርኛ ሶፍርትዌር ማሰብ የማይችሉ በመሆናቸው ነው።

የኢትዮጵያ ዘመን ኣቈጣጠር ለማስተካከል

ስለ ኢትዮጵያ የዘመን ኣቈጣጠር ኢንተርኔት ላይ የተጻፈ ከጥቂት ዓረፍተ ነገሮች በስተቀር ስለኣልነበሩ ዶክተሩ በ፲፱፻፺፬ ያቀረቡት በተወዳጅነቱም ብዙ ድረገጾች ላይ ቀርቧል። [432] [433] [434] [435] Archived ጁላይ 31, 2021 at the Wayback Machine [436] Archived ጃንዩዌሪ 25, 2016 at the Wayback Machine [437] [438] Archived ኖቬምበር 29, 2007 at the Wayback Machine [439] [440] [441] [442] Archived ሜይ 11, 2013 at the Wayback Machine [443] [444] [445] Archived ማርች 9, 2017 at the Wayback Machine [446] [447] Archived ጁላይ 31, 2021 at the Wayback Machine [448] [449] Archived ዲሴምበር 19, 2007 at the Wayback Machine [450] [451] [452] ከእዚያም ወዲህ የኢትዮጵያ ዘመን ኣቈጣጠር ተገቢውን ዕውቅና ቢያገኝም ዛሬም በስሕተት የጁልያን (Julian) ካለንደር ነው የእሚሉ ኣሉ።

ኢትዮጵያውያን ስለ ሄኖክ ዘመን ኣቈጣጠርም ያውቃሉ። [453] የሄኖክ ዓመት 364 ቀናት ነበሩት። [454] የኢትዮጵያ መጽሓፍ ቅዱስ ውስጥ መጽሓፈ ሄኖክ ምዕራፍ ፲፰ ቍጥር ፲፩ ስለ 364 የዓመት ቀናት ይናገራል።

ኢትዮጵያውያን ሲወርድ ሲወራረድ የመጣውን የነገሥታት የስም ዝርዝር ለብዙ ሺህ ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት 4,400 ዓመት በመጀመር ኣቆይተውልናል። ይህ ከ1,000 ዓመተ ዓለም ግድም ጀምሮ መሆኑ ነው። ይህ ኢትዮጵያውያን የእራሳቸው የዘመን መቍጠሪያ እንደነበራቸው የሚያመለክት ኣንድ ማስረጃ ነው። [455] [456] Archived ጃንዩዌሪ 9, 2015 at the Wayback Machine የግብጽና የሌሎችም እዚህ ኣለ። የጥንት ኢትዮጵያውያን የከዋክብትን ሳይንስ ፈጥረውና ስም ሰጥተዋቸው ለግብጻውያን ኣስተላለፉ ይባላል። [457] የግሪክ ፊደል ከግብጹ ዴሞቲክ የተወሰደ ነው ይባላል።

የኢትዮጵያ ዘመን ኣቈጣጠር (Ethiopian calendar) የጁልያን ዘመን ኣቈጣጠር ኣይደለም። ጁልየስ ሲዘር ባለ 10 ወራትና 300 ቀናት የነበረውን የሮማውያን ካላንደር ትቶ 365.25 ቀናት የኣለውን ካለንደር ወስዷል። በኣሁኑ ጊዜ በጁልያንና በጎርጎርዮስ ካለንደሮች መካከል ያለው የ13 ቀናት ልዩነት ሲሆን የዓመታቱ ቍጥሮች ግን (2017) ልዩ ኣይደሉም። በ525 ዓ.ም. ዲኖስዮስ ኤክሲጅዮስ (Dionysius Exiguus) የሚባል የሩስያ መነኩሴ የሮማው ጳጳስ መልዕክተኛም በመሆን የፋሲካን በዓል ኣወሳሰን ከግብጻውያን እንዲማር ተልኮ ነበር። እንደሚመስለኝና ኣንዳንድ ፀሓፊዎችም እንደሚሉት ኤክሲጅዮስ በ525 ዓ.ም. 532 ዓመትን ሳይጠቀም ኣልቀረም። ዲኖስየስ ኣኖ ዶሚኒ (Anno Domini ወይም ኤ.ዲ.) የሚባለውን ካለንደር በጃንዋሪ 1፣ 1 ኤ.ዲ. እንዲጀምር በ525 ቢወስንም በኋላም ፀሓፊዎች ጁልያን (ዩልዮስ) ካለንደር የኣሉት የግብጾችንና የኢትዮጵያን ዘመን መቊጠርያዎች ስለማይመለከት እራሱን የቻለ ካለንደር ሆኖ ቆይቷል። ኤክሲጅዮስ ወደኋላ በመቍጠር ሲጀምር ይመስለኛል ኣዲሱ ካለንደር ላይ ሰባት ዓመታት ግድም የጨመረበት ይላሉ ዶክተር ኣበራ ሞላ። የዓመታቱም ቍጥር ከግብጽ ይልቅ ወደ ኢትዮጵያ የቀረበ ነው። ምክንያቱም የግብጻውያን ዓመተ ሰማዕታት ኣንድ ብሎ በ፪፻፸፮ ዓ.ም. የጀመረ ስለሆነ ነው። [458] ጨረቃ መሬትን ስትዞርና መሬት ፀሓይን ስትዞር የሚወስዱት 532 ዓመታት (19 X 28) ተደጋጋሚነታቸው የታወቁ ናቸው በማለት ዶክተሩ ጽፈዋል። [459] [460] [461] [462] ኣሁን ያለነው ፲፭ኛው የ፭፻፴፪ ዓመታት ዙር ውስጥ ነው። የዲኖስዮስ ጁልያን ካላንደር ስሕተት እንደነበረው የቫቲካኑ ጳጳስ በቅርቡ በመጽሓፋቸው ስለኣሰፈሩ ዶክተሩም ኣመስግነዋቸዋል። [463] Archived ጃንዩዌሪ 25, 2016 at the Wayback Machine [464] [465] ምክንያቱም የዩልዮስ ቀለንጦስ ተጠቃሚዎች የኢትዮጵያው ላይ ሰባት ዓመታት ግድም ቢጨመሩም የእኛው ወደ ትክክለኛው የቀረበ ሳይሆን ኣልቀረም። ከግዕዙ ሲነጻጸር የጎርጎርዮስ ቀለንጦስ ተጠቃሚዎች የሦስተኛውን ሺህ መጀመሪያ የኣከበሩት ሰባት ዓመታት ግድም ቀድመው ነው። ኢትዮጵያውያን በዓላትንና ኣጽዋማትን ሲያከብሩ የቆዩት 532 ዓመታትን የሚሸፍነውን ኣንድ ትልቅ ጠንጠረዥ ደጋግሞ በመጠቀም ነው። ኢትዮጵያውያን ሚሌንየሙን ዋሽንግተን ዲ.ሲ. ሲያከብሩ ዶክተሩ ተጋብዘው ይኽንኑ የቀለንጦስዎቹን ታሪክ ኣቅርበዋል። [466] [467] [468]

ከኣንድ ዓመተ ዓለም ጀምሮ መስከረም ኣንድ ቀን ምን ዕለት እንደዋለ ወይም እንደሚውል ማስላት ስለሚቻል የኢትዮጵያ ዘመን ኣቈጣጠር ለሌሎች ቀለንጦሶዎችም ማነጻጸሪያ ሊያገለግል ይችላል። ለምሳሌ ያህል በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. መስከረም ፩ ቀን ምን ዕለት እንደዋለ ለማወቅ 7494 ዓመተ ዓለም ላይ 1873 ደምሮ በሰባት ማካፈል ነው። ቀሪው ኣንድ ከሆነ ዕለቱ ማክሰኞ ነው። (1873 የተገኘው 5500 ዘመነ ብሉይንና 1994 ዓመተ ምሕረትን ደምሮ በኣራት በማካፈል ነው።) [469]

የኢትዮጵያና የጎርጎርዮስ ዘመን የዕለት ልዩነቶች በጥቂት ቀናት መለያየት እየጨመረ ይቀጥላል። ይህ በጎርጎርዮስ የሠግር ዓመታት ኣወሳሰን የተፈጠረ ልዩነት ነው። የጎርጎርሳውያን ሠግር በ፬፻ ዓመታት ፺፯ ብቻ እንዲሆን እ.ኤ.ኣ. በ፲፭፻፹፪ ስለወሰኑ የቀናቱ ኣመዳደብ በእየ ፬፻ ዓመታት ሦስት ሦስት ቀናት እየቀነሰ መለያየቱ ይቀጥላል። የጁልያን ካለንደር ላይ ዲኖስዮስ ሰባት ዓመታት ግድም ሲጨምር ጎርጎርዮስ ፲ ቀናት ቀንሷል። በእነዚህ የሮማውያን ለውጦችም ሳትስማማ ኢትዮጵያ ካለንደሯን እንደጠበቀች ቆይታለች። በኣሁኑ ጊዜ ኣንድ ዕለትን ከኢትዮጵያ ወደ ጎርጎርሳውያን ወይም ከጎርጎርሳውያን ወደ ኢትዮጵያ ኣቈጣጠር የሚመነዝሩ ድረገጾች ኣሉ። [470] [471] Archived ፌብሩዌሪ 19, 2016 at the Wayback Machine የቀለንጦስዎቹም ዕውቅና ጨምሯል። [472] [473] [474] [475] ዓለማችን ከኣንድ ስፍራ ጀምራ ፀሓይን እየዞረች ተመልሳ እዚያ ገደማ የምትደርሰው በተለያዩ ዕለታት ስለሆነ ካለንደሮች ትክክል ኣይደሉም። የኢትዮጵያ ዕለት የሚጀምረው ጠዋት ነው። ስለ ጵጉሜን 7 የሚጽፉም ኣሉ። [476] ይህ በየስድስት መቶ ዓመታት የሚከሰተው በየዓመቱ የተጨመሩትን ደቂቃዎች ለመቀነስ ስለሚመስል ትክክል ሳይሆን ኣይቀርም ይላሉ ዶክተሩ።

በዶክተሩ የጽሑፍ ገለጻና ምክንያት የተባበሩት መንግሥታት ማሕበር እና የኣፍሪቃ ሕብረት ከመስከረም ፩፣ ፳፻ ዓ.ም. እስከ መስከረም ፩፣ ፳፻፩ ዓ.ም. የኣለውን የኢትዮጵያ ዓመት ሚሌንየሙን በማክበር ዕውቅና (Commemoration) ሰጥተዋል። [477] [478] ሦስተኛው የኢትዮጵያ ሺህ ዘመን የጀመረው መስከረም ፩ ቀን ፳፻፩ ዓ.ም. (September 11, 2008) ሲሆን መስከረም ፩ ቀን ፳፻ ዓ.ም. የሁለተኛው ሺህ የመጨረሻው የ2,000 ዓመት እንቁጣጣሽ እንጂ የሚሌንየሙ መጀመሪያ ኣልነበረም። [479] Archived ኖቬምበር 29, 2007 at the Wayback Machine [480]

ኢትዮጵያውያን [481] ካለንደራቸውን እንዲተዉ የተሞከሩት ስለኣልሠሩ ጽሑፎቹ ደራሲና ቀናት ወደሌላቸው እየተቀየሩ ነው። [482]

የኢትዮጵያ ዕለት የሚጀምረው ጠዋት ሲሆን የዩሊዮሱ እኩለ ሌሊት ላይ ነው። ስለዚህ ልዩነቶቹን ለማስላት ስድስት ሰዓታት መጨመር ወይም መቀነስ ያስፈልጋል።

የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ለማስተካከል

የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በ፲፱፻፺፪ ወይም Languages of Ethiopia, 1999 የሚል ድረገጽ SIL ያቀረበውን በመተርጐም ከእነካርታው በዶ/ር ኣበራ ቀርቦ ነበር። [483]እነዚህም፦ 1. ኣሪ 2. ኣፋር 3. ኣላባ 4. ዐማርኛ 5. ኣንፊሎ 6. ኣኝዋክ 7. ኣርቦሬ 8. ኣርጎባ 9. ኣውንጅ 10. ባይሶ 11. ባምቤሺ 12. ባስኬቶ 14. ቤንች 15. በርታ 17. ቢራሌ 18. ኦሮምኛ (ቦረና-ኣርሲ-ጉጂ) 19. ቦሮ 20. ቡርጂ 21. ቡሳ 22. ጫራ 23. ደሳነች 24. ዲሜ 25. ደራሻ 26. ዲዚ 27. ዶርዜ 28. ጉራጌ 29. ጋሞ-ጎፋ-ዳውሮ 30. ጋንዛ 31. ጋዋዳ 32. ጌዴኦ 34. ጉሙዝ 35. ሃዲያ 36. ሃመር ባና 37. ሆዞ 38. ካቻማ-ጋርጁሌ 39. ካሲፖ-ባለሲ 40. ካፊቾ 41. ከንባታ 42. ካሮ 43. ኮሞ 44. ኮንሶ 45. ኩረት 47. ኩንፈል 48. ክዋማ 49. ክዌጉ 50. ሊቢዶ 51. ማጃንግ 52. ማሌ 53. ምኢን 54. ሜሎ 55. መስመስ 56. ሙርሌ 57. ሙርሲ 59. ናዪ 60. ጉራጌ (ሶዶ) 61. ኑአር 62. ንያንጋቶም 63. ኦፑኦ 64. ኦይዳ 65. ቆቱ (ኦሮምኛ) 66. ሳሆ 67. ሰዘ 68. ሻቦ 69. ሻካቾ 70. ሼኮ 71. ሲዳሞ 72. ሱማሌ 73. ሱሪ 75. ትግርኛ 76. ፃማይ 77. ኡዱክ 78. ጉራጌ (ምዕራብ) 79. ኦሮምኛ (ምዕራብ-መካከለኛ) 80. ኣገው (ምዕራብ) 81. ወላይታ 82. ጫምታንግ 83. የምሳ 84. ዛይ 85. ዛይሴ-ዘርጉላ ናቸው። [484] በኣጭሩ ኢትዮጵያ ሰማንያ ቋንቋዎች ኣሏት ማለት ይቻላል።

ሌሎች ዝርዝሮችም እዚህ [485] [486] ኣሉ።

እዚህ ዝርዝር ውስጥ የግዕዝ ቋንቋ ኣልተካተተም። [487] የግዕዝ ቋንቋና [488] ግዕዝ ፊደል [489] እንዳይምታቱ መጠንቀቅ ያስፈልጋል። እስከኣሁን በኣብዛኛዎቹ የግዕዝ ፊደል ቀለሞቻችን ተጠቃሚ ቋንቋዎች ብዙ ጽሑፎች ስለኣልተጻፉ ብዙ የቃላት ክምችቶችም የሉም።

በኣሁኑ ጊዜ ውጪ ኣገር የኣሉ ኢትዮጵያውያንን በዓማርኛ ማስተናገድ ተጀምሯል። [490] በዓማርኛ ለማንበብ “Amharic” የሚለውን መምረጥ ያስፈልጋል። ወደፊት በሌሎቹም የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚ ቋንቋዎች መስተናገድ እንዲጀመር በየቋንቋዎቹ መጻፍ መስፋፋት ጠቃሚ ሳይሆን ኣይቀርም። በሁሉም ቋንቋዎቻችን በግዕዝ ፊደል መክተብ እንዲቻል ቀለሞቹ ዩኒኮድ ውስጥ ገብተው መክተቢያዎቹ በዶክተሩ ስለተዘጋጁ ባለመጠቀም ለሚዳከሙ ቋንቋዎች ተጠያቂዎቹ የየቋንቋዎቹ ተጠቃሚዎች ናቸው። ዕውቀት እየበዛና እየገዘፈ ወደ ኢንተርኔት ስለገባ የሚፈለገውን በቀላሉ ማግኘት ተችሏል። ይህ በተለያዩ ቋንቋዎቻችንም እንዲኖር መጻፍ ያስፈልጋል። ቃላትና ጽሑፎች በብዛት ሲኖሩ ወደ መተርጐም ይኬዳል። በኢትዮጵያ ከ80 በላይ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች እንዳሉ፣ ከእነዚህም መካከል ወደ 51 የሚጠጉት ቋንቋዎች በመጀመርያ ደረጃና በቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ለሚሰጡ ትምህርቶች በመማርያነት እንደሚያገለግሉ ናቸው፡፡ [491]

ከተለያዩ የፊደል ዓይነቶች ዶክተሩ ስሙን ለጥቂቶቹ የሰጡት ሥራ ለማቅለል ነው። ለምሳሌ ያህል የቤንች ገበታ ሲመረጥ የሚጠቀሙበት ቋንቋዎች ብዙ ናቸው። ምሳሌ ኣዊንጊ። የ“ዸ” ፊደል እርባታዎች ለኦሮሞ የተሰጡት ዶክተሩ ፊደሉን ቀድመው ስለዓወቁና መረጃዎቹ ስለቀደሙ እንጂ ይኸው ፊደል የሳሆ ቋንቋን ድምጽ ስለሚወክልና የሳሆም ምሁራን ፊደሉን እንዲጨምሩላቸው ስለላኩላቸው ፊደሉ የሳሆም ነው።

የኣንዳንድ የቦታዎች ስሞችም እየተለዋወጡ ስለሆነ ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ምሳሌ በረራ [492] Archived ፌብሩዌሪ 9, 2022 at the Wayback Machine

የቋንቋዎች ፊደላት ለማስተካከል

ከግዕዝ በፊት የደኣማቱ ቅድመ-ግዕዝ (Proto-Ethiopic) ፊደል ነበር። [493] ግዕዝ (Ethiopic) የሚለው ቃል ሁለት ትርጕሞች ኣሉት። ኣንደኛው የግዕዝ ቋንቋ ስም ሲሆን ሌላው የፊደሉ (Script) [494] ነው። የግዕዝን ፊደል የሚጠቀሙት የተለያዩ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የእየራሳቸው የሆኑ ቀለሞች ኣሏቸው። የግዕዝ ቋንቋ ፊደሉን ብቻውን ሲጠቀም ቆይቶ ሌሎች ቋንቋዎች የእየራሳቸው የሆኑ ቀለማትን ጨምረውበት ተስፋፍቷል ይባላል። [495] ዓማርኛ፣ ትግርኛና ኦሮምኛ ብዙ ቀለሞች ከመቶ ዓመታት በላይ ቢጋሩም ሁሉም የእየራሳቸው ብቻ የሆኑ ቀለማት ኣሏቸው። ቢሆንም ግዕዝ የሁሉም ተጠቃሚ ቋንቋዎች የፊደል ስምም ነው። ከእነዚህም መካከል ብዙ ተጠቃሚዎች የኣሉት የዓማርኛ [496] ፊደል ነው። የዓማርኛው ፊደልም በቅርቡ የተጨመረለትን የ“ቨ” ቤት ጨምሮ ከ፸ በላይ የግዕዝ ቋንቋ የሌለውን እነ “ሸ”፣ “ቸ”፣ “ኘ”፣ “ጀ”፣ “ጨ”፣ “ኸ”፣ “ዠ” እና ሌሎችንም ቀለማት ያካትታል። (ይህ ገለጻ ዓማርኛ የኣልሆነውን የታይፕራይተር ፊደል ስለማይመለከት ቅጥልጥል ፊደሉም ግዕዝ ኣይደለም።) ስለዚህ ዓማርኛ የሚጠቀመው በእራሱ ፊደል ነው። ይህ ኣገላለጽ የሌሎች ቋንቋዎች ፊደላትንም ይመለከታል። ለምሳሌ ያህል ሁሉም የዓማርኛ ቀለሞች የትግርኛው ውስጥ እንደሌሉት ሁሉም የትግርኛ ቀለሞች (ለምሳሌ “ቐ”) ዓማርኛው ውስጥ የሉም። ኣንዳንድ ሰዎች በስሕተት ዓማርኛ የእራሱ ፊደል የለውም ይላሉ። ዓማርኛ የእራሱ ፊደል (Amharic Alphabet) የኣለው ቋንቋ [497] ነው። የግዕዝም ቋንቋ የእራሱ ፊደል ኣለው። የግዕዝ ቋንቋ ፊደላት የዓማርኛው ውስጥ ሲኖሩ ሁሉም የዓማርኛ ፊደላት የግዕዙ ቋንቋ ፊደላት ውስጥ የሉም። የግዕዝ ወይም Ethiopic የተለያዩ ቋንቋዎች የሚጠቀሙበት የፊደሉም ስም ሲሆን ለተለያዩ ቋንቋዎች ተጨማሪ ቀለሞች ተጨምረዋል። ኦሮሞም የእራሱ የግዕዝ ፊደል ኣለው። እንዲሁም ሁሉም የኦሮሞ ፊደላት (ምሳሌ “ዸ”) የዓማርኛው ውስጥ የሉም። የኤርትራው ቢለንና የጎጃሙ ኣገው ቋንቋዎች ፊደላት ቀለሞች ኣንድ ዓይነት ናቸው። ጉራጌኛ ሰባቱንም ቤቶች ያጠቃልላል። [498]

የኣብዛኛዎቹ ኣዳዲስ ተጠቃሚ ቋንቋዎች ፊደሎች ዓማርኛው ላይ የተጨመሩ ናቸው። በእዚህም የተነሳ የቀለሞቹ መልኮች እየጨመሩ ቢሆንም ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆኑ ማወቁ እየቀለለ ነው። ተጠቃሚው የሚፈልገውን ቋንቋ በመምረጥ በቋንቋው ቀለሞች ብቻ መጠቀም ተችሏል። በላቲን (Latin) ፊደል እንደሚጠቀሙት እንደእነ እንግሊዝኛ፣ ጀርመንኛና እስፓንኛ ፊደላት [499] [500] [501] በመባል እንደሚታወቁት ሁሉ በግዕዝ ፊደል የሚጠቀሙትም የትግርኛ፣ [502] ዓማርኛ፣ [503] ግዕዝ፣ [504] ኦሮምኛ [505] Archived ዲሴምበር 28, 2016 at the Wayback Machine ሌሎችም ፊደላት በመባል በፊደል ስማቸው ተከፋፍለዋል። ኣንዳንድ ምሁራን በስሕተት ዓማርኛና ትግርኛ የእራሳቸው ፊደላት የላቸውም ይላሉ። ይህ እንግሊዝኛና እስፓንኛ የእራሳቸው ፊደላት የላቸውም እንደማለት የተሳሳተ ነው። ከእዚህ ጎን የኣለው ሥዕል እንደሚያሳየው ፊደላቱን በቋንቋ ቀለሞች (Character sets) የመከፋፈሉ ጥቅም ኣጻጻፍ ለማቅለልም ሲሆን በሁሉም የግዕዝ ቀለሞች ለመጠቀም “Ethiopic ግዕዝ” የሚለውን መምረጥ እንደሚቻል ለማሳየት ነው። Ethiopic (ኢትዮፒክ) በእንግሊዝኛ ግዕዝ ነው። በግዕዝ ቋንቋ ፊደላት ለመጠቀም "ግዕዝ ቋንቋ" የሚለውን መምረጥ ያስፈልጋል። በኣንድ ምሳሌ ቋንቋ የተሰየሙትንም ብዙ ቋንቋዎች ሊጠቀሙባቸውም ይችላሉ። ምሳሌ፦ ኣዊንጂ፣ ዲዚ። ወደፊትም ገበታውን በእያንዳንዱ ቋንቋ ለየብቻ ማቅረብ ያስፈልጋል። ምክንያቱም ወደፊት እያንዳንዱ ቋንቋ በእራሱ ሰዋሰው፣ መዝገበ ቃላት፣ ማረሚያና የመሳሰሉት መጠቀም ስለኣለብን ሳይንሱንና ቴክኖሎጅውን በጀመርንበት በኣሁኑ ጊዜ ለየብቻቸው ማዳበር ስለሚያስፈልገን ነው። ይህ እንግሊዝኛና ፈረንሳይኛ ተቀላቅለው በላቲን ፊደላት እንደማይቀርቡት ዓይነት መሆኑ ነው። ለጥቂቶቹም መደበኛ ቅርጽ የተሰጣቸው ፊደላቱ በቋንቋ ስሞቻቸው ወደ ዩኒኮድ ሲገቡ ነበር። (በግዕዝኤዲት ኣጠቃቀም እንግሊዝኛ ለመቀላቀል የ“ቍጥጥር” (“Ctrl”) እና “ኣማራጭ” (“Alt”) ቁልፎች መጫን ያስፈልጋል።) በዶክተሩ ፓተንቶች የተጠቀሱት የግዕዝ ቀለሞች ብዛት [506] ዊኪፔዲያ ውስጥ [507] ከተጠቀሱት የበለጡ ናቸው።

ዶክተሩ ግን በግላቸው በዓማርኛ ፊደል መቀነስ ከማይስማሙባቸው ምክንያቶች ኣንዱን ለመጥቀስ ያህል ኣንዳንድ የኣናሳ የግዕዝ ቀለሞች ተጠቃሚ ቋንቋዎች ቀለማት የተሠሩት ይቀነሱ የተባሉትን በመጠቀም ስለሆነ ነው። [508] ሞክሼዎች ይቀነሱ የተባለው የኣናሳ ተጠቃሚዎች ቋንቋዎች ፊደሉ በዛ ብለው ቅር እንዳይላቸው ነው የሚባልም ወሬ ኣለ። በእዚህ የተነሳ ጸሎቱ “ጸ” የፀሓዩ “ፀ” ሞክሼ ከሆነ የጉሙዙ “ꬨ” “ጸ” ሞክሼውን መመርኰዝ ኣልነበረበትም። “ጿ” ቀለም ያለውን ጸሎቱ “ጸ” ሞክሼ ነው ተብሎ ተዘልሎ የምኢኑ ዘጠነኛ እንዚር ፀሓዩ ላይ ስለቀረበ ዶክተሩ ለፀሓዩ ስምንተኛ ቀለም ኣቅርበዋል። ምክንያቱም በዶክተሩ ኣስተሳስብ ፊደል መቀነስ የሚፈልጉ ፊደል እንዳይቀነስ የሚፈልጉትን መብት መንካት የለባቸውም። “ኳ”ን ኣጥፍቶ “ክዋ” ወይም “ኩዋ” እንደ “ኳ” ይነበቡ ማለት ብቻ በቂ ኣይደለም። ምክንያቱም ግዕዝ ድምፃዊ ፊደል ስለሆነ ነው። “ሀ” እና “አ” የእየራዕቦቻቸው ሞክሼዎች መስለዋቸው ከኣናሳ ቋንቋዎች ቀለሞች ውስጥ ሊያጠፏቸው የሚፈልጉም ኣሉ። ይኸን ልዩነት በኣለማወቅ የዩኒኮድ ፊደላችንም ላይ ችግር የፈጠሩ ኣሉ። [509] ስለዚህ የሚሻሻሉ ነገሮች ጥናት ላይ ቢመረኰዙ ኣይከፉም። ሞክሼ የተባሉት ቀለሞች የእየእራሳቸው ጥቅሞች ኣሏቸው። ምሳሌ፦ መሳሳትና መሣሣትን በማጥበቂያ ወይም በማላልያ ምልክት ከመለየት የቃላቱን ኣመጣጦች ማወቅ ለዕውቀቱም ሆነ ለኮምፕዩተሩ ሳይበጅ ኣይቀርም።

“መሣሣት” (“messassat”) (“ትክክል ኣለመሆን”) እና “መሳሳት” (“mesasat”) (“ስስ መሆን”) ሁለት ቃላት በዓማርኛ ለመክተብ የሚወስዱት ሥፍራዎች ስምንት ሲሆኑ የሚከተቡት በ14 መርገጫዎች ነው። ላቲኖቹ የሚወስዱት እጥፍ ሥፍራዎችና 16 መርገጫዎች ስለሆኑ ሞክሼዎችን ማስወገድ ሥፍራዎችንና መርገጫዎችን ስለሚያስጨምር ለዓማርኛውም ጠቃሚ ኣይደለም። ምሳሌ፦ “መሳ'ሳ'ት”። ምክንያቱም የ“መሳሳት”ን ሁለት ኣጠቃቀሞች ከዓረፍተ ነገሩ መለየትም ይቻላል። እነዚህም እንደልብስ ያልጠነከረ “ስስ” መሆንና እንደሰው ርኅሩህ የሆነ “ስስ” መሆን ናቸው።

በጊዜውም የኮምፕዩተር ክፍል ባይኖርም ፲፪ የሞዴት ፕሮግራሞች የኢትዮጵያ ኮምፕዩተሮችና ሶፍትዌር ለኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ (በፕሮፌሰር ዓለማየሁ በኩል) በ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. በነፃ ኣበርክቶ ነበር። ኦሮምኛን በግዕዝ ፊደሉ መክተብ ያስቸግራል በተባለበት ጊዜ ለቀረቡት ኣንዳንድ ምክንያቶች ዶክተሩ መፍትሔ ነበራቸው። [510] ኦሮምኛን ከግዕዝ ይልቅ በላቲን ፊደል መጻፍ ይሻላል ተብሎ የቀረቡት ዘጠኝ ምክንያቶች ደካማዎች ነበሩ። ለምሳሌ ያህል በኣንደኝነት የቀረበው ምክንያት ላቲን 26 ቀለሞች ሲኖሩት የግዕዙ 189 ናቸው ይላል። የላቲን “ኤ” ፊደል ዓይነቶች 27 ሲሆኑ ከእነዚህ ስምንቱ “aàáâãäåæ” ናቸው። “ብላ” በግዕዝ ፊደል “ኛዹ” ተብሎ በኦሮምኛ ሲጻፍ የሚወስደው ስፍራ ሁለት ብቻ ሲሆን እያንዳንዱን ቀለም ለመክተብ ኣንድ ስከንድ ቢወስድ በላቲን ፊደል በእንግሊዝኛ “nyaadhuu”፣ በፈረንሳይ “gnaadhuu”፣ እና በእስፓኝም ፊደል ኣያታርፉም። በሌላ በኩል ኣንዳንድ ኦሮሞዎች ወደ ላቲን የዞሩት በግዕዝ ፊደል እንዳይጠቀሙ ስለተከለከሉም ነው ይባላል።

የግዕዝ ፊደልና ተጠቃሚ ቋንቋዎቹ ጥቃት እየደረሰባቸው ነው። [511] [512] Archived ማርች 6, 2016 at the Wayback Machine [513] ለምሳሌ ያህል ውክፔዲያ ስለ እንግሊዝኛ ፊደል [514] ገጽ ሲኖረው ስለ ዓማርኛ ቋንቋ እንጂ [515] በእንግሊዝኛ ስለ ዓማርኛ ፊደል ወይም የኣማርኛ የጽሕፈት መኪና ገጽ የለውም። በጽሑፍ የሌለ ነገር እንደሌለ ይቆጠራል ነው የሚባለው። በዓማርኛ ፊደል [516] በነፃ መጻፊያ እዚህ [517] Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine ኣለ። የተሟሉ የዓማርኛ መክተቢያዎች ኣሉ። [518] [519] ስለዚህ ኣሁን በግዕዝ ፊደላችን በትክክለኛው ኣጠቃቀም በተለያዩ ቋንቋዎቻችን በሕጋዊ ሁኔታ በተገዙ ሶፍትዌር በመጻፍ ጽሑፎች ወደ ኮምፕዩተርና ኢንተርኔት የሚገቡበት ጊዜ ነው። በቅርቡም ሕዝብ ለብዙ ዘመናት የተጠቀመበት ዓማርኛ ብሔራዊነቱ ቀርቶ የሥራ ቋንቋ በመሆን በእንግሊዝኛ እንዲተካ ተደርጓል ይባላል። ኢትዮጵያ የእንግሊዝ ቅኝ ኣገር ስለኣልሆነች ባይሆን ዓማርኛው ላይ እንግሊዝኛን መጨመር (Grandfathering) እንጂ መተካቱን ዶክተሩ ይቃወማሉ። ተማረ የሚባለው ኣንድአንድ ኢትዮጵያዊ እያተኮር የኣለው ከጻፈልኝ ምን ኣለበት እየኣለ በተገኘው ሶፍትዌር ይጽፋል እንጂ ሁሉንም የዓማርኛ ቀለሞች እንኳን ከትቦ የሚጠቀምበት የመክተብ ችሎታ እንዳለው ማጣራቱ ኣጠራጣሪ ነው። “ባለፈው አንድ ዩኒቨርሲቲ ሄጄ አንድ ጓደኛዬ የነገረኝ አሳዛኝ ነገር ነበር። የአማርኛ መምህር ለመቅጠር የተሰጠው ፈተና ዩ፣ ዪ፣ ዬ እና ዮን መጻፍ ነበር። በጣም የሚገርመው ግን ከተፈተኑት ኣምስት የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው መምህራን ኣንዱ ብቻ አሟልቶ ጽፏቸዋል። ወደፊት አማርኛን ማንበብና መጻፍ የሚችል ሰው ለማግኘት ሥዕለት ሳያስፈልግ አይቀርም።” ይላል እዚህ [520] Archived ማርች 6, 2016 at the Wayback Machine የኣለ ኣንድ ጽሑፍ። ለእዚህ ችግር የአማርኛ የጽሕፈት መኪናም ኣስተዋጽዖ ሳይኖረው እንዳልቀረ የኮሚሽነር ኣበበ ሙሉነህን የ፲፱፻፹፪ ዓ.ም. ደብዳቤ ውስጥ የኣሉት የ“የ” እንዚራን መቀጠያዎች ያሳያሉ። [521] (“ኢትዮጵያ”፣ “ዩናይትድ” እና “ኮምፒዩተር” የሚሉት ቃላት የተጻፉባቸው የ“የ” መቀጠያዎች መለየት ኣስቸጋሪ ነው። የአማርኛ የእጅ ጽሑፍ መጻፊያ “ዮ”ን መጻፍ የኣልቻለ ቢመስልም ስሕተቱ የፀሐፊው ሳይሆን ኣይቀርም። [522])

የትግርኛ ቀለሞቻችንን ለኣለመጠቀምና ቀስ በቀስ ለማጥፋት ያቀለሟቸውንም ዶክተሩ ተቃውመዋል። [523] [524] [525] ለምሳሌም ያህል በአማርኛ የ“ሀ” ድምጽ ወደ “ኸ” የቀረበ ነው አንጂ “ሀ” የ“ሃ” ሞክሼ ኣይደለም። የ“ሀ” እና “ኸ” ድምፆች ኣንድ ባይሆኑም “ሀ” እና “ሃ” ኣንድ መሆን የለባቸውም። “ሐ”፣ “ኀ”፣ እና “ዀ”ም ኣሉ። የተለያዩ ቋንቋዎች ብቻ የሚጠቀሙባቸው ቀለሞችና ድምፆች ኣሉ። ምሳሌ የጉራግኛው “ⷐ”። ይኸ ለምሳሌ ያህል የቀረበ የጉራጌ ፊደል እንደ ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ዓይነት የተሟላ የግዕዝ ፊደል ለሌላቸው ኣይታይም።

የሁሉም የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚ ቋንቋዎች ተለይተው መታወቅ እንደየፍላጎቱ ለማዳበር ይጠቅማል። [526] [527] ለምሳሌ ያህል ኦሮምኛ ከቴክኖሎጅው ጋር እንዲጓዝ እነኢትዮስዊትን ማዳበር ያስፈልጋል። ግዕዝ ትክክለኛ ፊደል ስለሆነ ወደፊት ሌሎች ዓለማት ስንሄድ ይዘናቸው የምንሄድ ስለሆኑና ከዋክብትን ስለሚጎበኙ በኣቋራጭ ኣንሸወድ። በግዕዝ በሚገባ ለመጠቀም ወጪ ማውጣትና ለመክፈል መዘጋጀት እንጂ [528] ለላቲን የተሠሩ ፕሮግራሞችና መሣሪያዎች ሲባል ፊደል መቀነስ [529] Archived ኦገስት 5, 2021 at the Wayback Machine ላይ ማተኮርን ዶክተሩ ይቃወማሉ።

የግዕዝ ፊደል መክተቢያዎች ሁሉንም ቀለሞች የማስተናገድ ችሎታ ሊኖራቸው ይገባል። በዓማርኛ ብቻ የሚያስጽፈውን ግዕዝ ማለትም ተገቢ ኣይደለም። የዓማርኛ ከታቢም በሌሎች ፊደላት መኖር እንዳይዘናጋ ዓማርኛው ብቻ ተመርጦ እንዲከተብበት ኣማራጭ ሊኖር ይገባል። ፊደላትን በተለያዩ ቋንቋዎች ማቅረብ ለትርጕምና የተለያዩ ሥራዎች ማዳበር ይጠቅማል። ለምሳሌ ያህል ኦነሲሞስ ነሲብ በሁሉም የግዕዝ ቀለሞች ኣልተጠቀሙም።

ጽሑፎች ለማስተካከል

ኢትዮጵያንና ጠቅላላ ዕውቀት የሚመለከቱ ጉዳዮች [530] በተለይ Ethiopic.com በእየጊዜው የቀረቡ ኣሉ። ለምሳሌ ያህል፣ ስመ እጸዋት፣ [531] [532] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine [533] Archived ኖቬምበር 1, 2013 at the Wayback Machine [534] የኢትዮጵያ ዘመን ኣቈጣጠር፣ [535] Archived ጁላይ 31, 2021 at the Wayback Machine[536] [537] [538] Archived ዲሴምበር 19, 2007 at the Wayback Machine [539] [540] [541] [542] ስመ በሽታ፣ [543] የግዕዝ ፊደል፣ [544] [545] [546] Archived ማርች 7, 2016 at the Wayback Machine ስመ ኣኃዝ፣ [547] Archived ሜይ 21, 2013 at the Wayback Machine [548] [549] የኢትዮጵያ እንስሳት ስመ አንሰሳት፣ [550] [551] የግዕዝ ስምና ኣኃዝ [552] [553] ስመ ምልክቶች፣ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች፣[554] ኣንዳንድ የፊደል ስሕተቶች፣ [555] Archived ጁን 14, 2006 at the Wayback Machine [556] [557] ግልጽ ደብዳቤ ለቫቲካን ጳጳስ ቤነዲክት ፲፮ተኛ [558] Archived ጃንዩዌሪ 25, 2016 at the Wayback Machine [559] [560] እና Amharic Glossary ምሳሌዎች ናቸው። [561] ሌላ ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል የኢትዮጵያ ሚሌንየም መከበር ያለበት መስከረም ፩ ቀን ፳፻፩ ዓ.ም. እንጂ መስከረም ፩ ቀን ፳፻ ዓ.ም. መሆን እንደኣሌለበት ኣንድ ድረገጽ ላይ ዶክተሩ ጽፈውና ኣሳምነው የኢትዮጵያ ምክር ቤት ከሰኔ ፩ ቀን ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. እስከ መስከረም ፩ ቀን ፳፻ ዓ.ም. እንዲከበር የተደነገገው ስሕተት ተደርሶበት ሚሌንየሙ ዓመቱን ሙሉ እንዲከበር ተደርጓል። [562] Archived ጁላይ 31, 2021 at the Wayback Machine [563] [564] የኢትዮጵያ ስመ እጽዋት ምንጭ የዶ/ር ኣበራ ሞላ ሥራ ነው። [565] [566]

በተጨማሪም ዶክተሩ በየጊዜው የሞዴትኢትዮወርድግዕዝኤዲት ኣማርኛና እንግሊዝኛ መመሪያዎችን ለመክተብና ማቀነባበሪያ ከተጠቀሙባቸውና የሌሎችም ሥራዎች ሌላ ብዙ መጽሓፍት ከ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. ጀምሮ ከጻፉባቸው ታዋቂ ደራስያን መካከል ዶ/ር ዓለሙ ቢፍቱ እና ዶ/ር ለይኩን ብርሃኑ ይገኙበታል። እነዚህ በዓማርኛው ፊደል መጽሓፎቻቸውን ኣሜሪካ የጻፉና ያሳተሙ ደራስያን ዶክተሩን በመጥቀስ ኣመስግነዋል። ዶ/ር በቀለ ሞላ እና ጌታቸው ሞላ ዋሽንግተን ዲ.ሲ. ውስጥ ፈጣን ማተሚያ ቤት [567] የመጀመሪያው የሆነውን ግዕዝ ማተሚያ በ፲፱፻፹፱ ዓ.ም. ኣቋቁመው ብዙ መጽሓፍትና ጽሑፍ-ነክ ሥራዎች በሶፍትዌር ታትመዋል። ዶ/ር በቀለም ተመስግነዋል። ዶክተር ኣበራም የግዕዝ ፊደል የረዥም ጊዜ ተጠቃሚ ናቸው። [568] [569] [570] [571] [572] [573] ለኣሥር ዓመታት ያህልም የ“Ethiopian Review” [574] (ኤልያስ ክፍሌ) “ላንዳፍታ[575] (መኮንን ገሠሠ) መጽሔቶች ተባባሪ ኣዘጋጅ ነበሩ። ዶክተሩ ዲጂታይዝ በኣደረጉት ግዕዝ በተለያዩ ርዕሶች ኢንተርኔት ላይ የተለያዩ ጽሑፎችን ኣቅርበዋል። [576] [577]

የዶክተሩ ሥራዎች የተለያዩ መጽሓፍትና መጽሔቶች ውስጥም ተጠቅሰዋል። ምሳሌ፦ History of Mathematics in Africa, AMUCHMA 25 Years (ገጽ 526) [578] [579] Encyclopedia of Time, (ገጽ 128) [580] [581] [582] Archived ሴፕቴምበር 26, 2014 at the Wayback Machine [583] [584] [585] [586] ዶክተሩንም ስለ ሥራዎቻቸው የኣመስገኑ ብዙዎች ናቸው። [587] [588][589] [590] ቪድዮዎችና ሌሎችም ኣሉ። [591] [592] [593] Archived ጁን 5, 2016 at the Wayback Machine [594] Archived ኦገስት 2, 2021 at the Wayback Machine [595] Archived ዲሴምበር 28, 2016 at the Wayback Machine [596] [597] [598] Archived ጁን 22, 2015 at the Wayback Machine [599] [600] [601] [602] ይህ “ኣበራ ሞላ” የውክፔዲያ (Wikipedia) ገጽም በብዛት ከሚነበቡት ኣንዱ ነው። [603] የዓማርኛና እንግሊዝኛ ቅልቅል ጽሑፎች ምሳሌ እዚህ ኣለ። [604] ዶክተሩ ይኸን የዓማርኛ ዊኪፔዲያ ገጽ ከኣቀረቡት ፀሓፊዎች ኣራተኛ ናቸው። [605] ገጹም በትልቅነት ኣንደኛ ነው። [606] ሌላ ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል የአማርኛ ዊክፔዲያ ስመ እጽዋትና [607] ስም አንስሳት [608] መነሻዎች የዶክተሩ ጽሑፎች ናቸው።

ዶክተሩ ከታዋቂ ሰዎች ኣንዱ ናቸው። [609] በኣከናወኗቸው የተለያዩ ሥራዎች ጥቅሞቻቸው የተነኩ ጥቂት ሰዎች ስለእሳቸው የተጻፉ የእንግሊዝኛ ጽሑፍችን የሚሠርዙ ቢኖሩም ኣልተሳካላቸውም። [610] [611] [612] [613] Archived ጁን 10, 2015 at the Wayback Machine [614]

ግዕዝ አከታተብ ለማስተካከል

ዶክተሩ (Dr. Aberra Molla) ከ564 በላይ የሆኑትን የግዕዝ ዩኒኮድ ቀለሞች ማንኛቸውንም በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ብቻ እንዲከተቡ ለፈጠሩት ቀልጣፋና ግሩም ኣዲስ ዘዴ መረጃ Ethiopic Character Entry ፔንዲንግ ፓተንት (Pending Patent) እዚህ [615] Archived ፌብሩዌሪ 10, 2015 at the Wayback Machine ወይም እዚህ [616] [617] ማንበብ ይቻላል። ኣብሻ (ABSHA) በመባል በታወቀው በእዚህ ኣዲስ የመክተቢያ ዘዴ ወይም ሥርዓት ሕዝቡ በነፃ በአማርኛ መጻፍና የዓለም ድረገጾችንና የመሳሰሉትን (ኢንተርኔት) በአማርኛ መፈለግ እንዲችል http://freetyping.geezedit.com Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine (ፍሪታይፒንግ.ግዕዝኤዲት.ኮም) የሚባል ድረገጽ በ፳፻፪ ዓ.ም. ኣበርክተዋል። ከእዚያም ወዲህ ብዙ መቶ ሺህ ሰዎች ተጠቅመውበታል። በኣብሻ ሥርዓት ብዛቱ ከ፭፻ በላይ ከሆነው የግዕዝ ፊደል፣ ምልክት፣ ኣኃዝና ማዜሚያ ሌላ ኮምፕዩተሩ የሚጠቀምባቸውን የእንግሊዝኛ ቊጥሮችና ምልክቶችን ግዕዝ በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ተጠቅሞባቸው መክተቢያዎቹ ተርፈዋል። በኣንድና ሁለት መርገጫዎች የእንግሊዝኛውን ቀለሞች እንዲከትብ የተሠራው የኮምፕዩተር የፊደል ገበታ ግዕዝን ወደ እንግሊዝኛው ዓይነት ኣከታተብ በቀረበ ዘዴ እንዲከትብ ሠርተዋል። በእዚህ ዘዴ ግዕዝ የእንግሊዝኛ እስፔሊንግ ጣጣ ውስጥ ሳይገባ የእንግሊዝኛውን የኮምፕዩተር ገበታ በመጋራት፣ በማዋሃድና ለብቻውም እንዲጠቀም ሆኗል። ይኸንንም ያደረጉት በፓተንት ማመልከቻቸው እንደጠቀሱት ግዕዝን በቀላሉና በቀለጠፈ ዘዴ መክተብ የሚያስችል ዘዴ ስለኣልነበረ ነው። [618]

ነፃውና የሚሸጠው ግዕዝኤዲት ሶፍትዌር የተሸፈኑት በኣንድ የባለቤትነት መታወቂያ ስለሆነ ማስጠንቀቂያው ለሁለቱም ነው። ፓተንቱ ቢኖርም ባይኖርም ከፈጠሩት ዘዴ የተሻለ በኣሁኑ ጊዜ ስለሌለ ማንኛውምን ቀለም በሁለት መርገጫዎች መክተብም ያስችላል። ለምሳሌ ያህል በፈጠሩት ኣዲስ ዘዴ ኮምፕዩተሩ በኣለው 47 መርገጫዎች የግዕዝ ሳድሳንና ኣኃዞች በኣንድ ኣንድ መርገጫዎች ሲከተቡ ሌሎች ከ400 በላይ የሆኑት የግዕዝ ቀለሞች እያንዳንዳቸው በሁለት መርገጫዎች ይከተባሉ። [619] ስለዚህ በእዚህ ዘዴ መፈጠር የተነሳ ቀለሞችን በሁለትና ከእዚያ በላይ መርገጫዎች በመጠቀም ወይንም የግዕዝን ቀለም ላቲን በማይጠቀምበት ኣዲስና ኋላ ቀር ዘዴ እንደላቲን ቃላት በእስፔሊንግ መክተብ ኣያስፈልግም። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዓማርኛውን [620] በኣራት መርገጫዎች የሚያስከትቡ ዘዴዎችንና የኮምፕዩተር ፕሮግራሞች በነፃ በማደል እያዘናጉ በማለማመድ ላይ የኣሉም ኣሉ። ይህ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች በኣራት መርገጫዎች ስለማያስከትብና ሊያዛልቅ ስለማይችል ዓማርኛውንም ሆነ እንግሊዝኛውን ሳይጠቅም ሁለቱንም ከሌሎች የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች እንዳያጣላና እንዳያስተዛዝብ ዶክተሩ የፈጠሩት ይራዳል። ቸልተኝነት ከቀጠለ ግን የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች ኣናሳ እንዳይሆኑ ሳያስተውሉ በተገኘው በመጠቀም ይሀን ወሳኝ ጊዜ ከማባከን መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ግዕዝኤዲት የሚከትበው እንደ እንግሊዝኛው ኣከታተብ በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ቢመስልም ከእንግሊዝኛው በተሻለ፣ በረቀቀ፣ ኃይለኛና ኣዲስ ዘዴ ስለሆነ ፊደላችንን በዓለም ላይ ለማስፋፋትና በድምፃዊነቱ ጥቅም ላይ ለማዋል በሚገባ ተዘጋጅቷል። ሥራውም ሳይንስን የተመረኰዘ ነው። የግዕዝ ፊደል የረዥም ጊዜ ተናጋሪዎችና ጸሓፊዎች የኣሉት ሲሆን ድምጽን እንዲወክል የተሠራውን የእንግሊዝኛውን ዓለም-ኣቀፍ ድምፃዊ ፊደል (International Phonetic Alphabet) ሊረዳ ይችላል። [621] በኣሁኑ ጊዜ ግዕዝ በዩኒኮድ ዕውቅና ያገኙትን የቢለን፣ ቤንች፣ ምኢን፣ ሙርሲ፣ ሱሪ፣ ትግረ፣ ትግርኛ፣ ኣገው፣ ኣውንጂ፣ ኦሮምኛ፣ ዓማርኛ፣ ዲዚ፣ ዳውሮ፣ ጉሙዝ፣ ጉራጌ፣ ጋሞ ጎፋ እና ግዕዝ ቋንቋዎች የሚጋሯቸውን ቀለሞችና ሌሎችንም ያስከትባል። ይህ የውክፔዲያ ገጽም የተጻፈውና የቀረበው በግዕዝ ፊደል ነው። [622]

ግዕዝኤዲት.ኮም [623] (Geezedit.com) [624] የኮሎራዶው ኣብሻ/የኢትዮጵያ ኮምፕዩተሮችና ሶፍትዌር ኩባንያ ሌላ የእሳቸውና ባለቤታቸው ወ/ሮ ሠናይት ከተማ ድረገጽ ነው። የሁሉም ስም ግዕዝኤዲት ቢሆንም የነፃው ኃይልና ኣጠቃቀም የተወሰነ ነው። ዶክተሩም እንዴት የግዕዝ ፊደል ለኮምፕዩተሮች፣ የእጅ ስልኮችና ለመሳሰሉት መቅረብ እንደሚቻል በሳይንሳዊ ምርምር የደረሱበትን ለገበያና በነፃ ከማድረስ ኣልፈው ለፊደሉ መብት ታግለው ስለተሳካላቸው በምርምሩ በመቀጠል ትክክለኛ መደብ ፈጥረዋል። [625] እየተሻሻለም ነው። ስለዚህ እያንዳንዱን ቀለም በሁለት መርገጫዎች መክተብን ጨምሮ ከኣሁን ወዲያ መጠቀም ኣስፈላጊ ኣይደለም። ሕዝቡም ይሀን ተገንዝቦ ሳይንስ በፈጠረው የተራቀቀ መሣሪያ በሳይንሳዊ ወጉና በማዕረጉ መጠቀም እንጂ ለተለያዩ ዓላማዎችና በነፃ የሚቀርቡት ኋላቀር ኣከታተቦች ኣንዳንዱን እያበላሹት እንደሆነ መገንዘብ ይገባል።

ግዕዝ በኮምፕዩተር እንዲሠራ ኣዲስ ግኝት ሲቀርብ በኮምፕዩተር ዘመን ብቻውን ማሠራት በቂ ስለኣልሆነ ሞዴት የግዕዝና የእንግሊዝኛ ማተሚያ ነበር። የኮምፕዩተር ኣጠቃቀም ከዶስ ወደ ዊንዶውስ ሲዞር ዶክተሩ ኢትዮወርድን በማቅረብ ለመጀመሪያ ጊዜ ግዕዝ ዊንዶውስን እንዲጠቀም ኃይል ኣገኘ። የኢትዮወርድ ኢትዮኤዲትም ሌሎች ጥቂት የዊንዶውስ ፕሮግራሞችም ውስጥ ይሠራ ነበር፦ ምሳሌ ወርድፐርፌክትና ኳርክኤክስፕሬስ። በግዕዝኤዲት ኮምፕዩተር በግዕዝ እንዲጠቀም ሆነ። ግዕዝ ወደ እጅ ስልክ ሲገባም የግሉ የማቀነባበሪያ (የግዕዝኤዲት) ገበታ ኖሮት ስልኩን በፊደሉና ከላቲን ጋር በመጋራት እንዲሠራ ኣደረጉ።

የግዕዝኤዲት ኣከታተብ ትክክለኛና ሳይንሳዊ ከመሆኑም ሌላ ሁሉም የግዕዝ ቀለሞች በእኩልነት ተስተናግደዋል። የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች ቀለሞቻቸውን በወጉና በቀላሉ እንዲጠቀሙ ኣስችሏል። ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዶክተሩ ፓተንት ማመልከቻ 20090179778 [626] በሚከተሉት የኣሜሪካ ፓተንቶች ተጠቅሷል፦ [627] 8,381,119 [628]፣ 8,645,825 [629]፣ 8,706,750 [630]፣ 8,700,653 [631]፣ 8,762,356 [632]፣ 8,812,733 [633] ከጠቃሾቹም የፓተንቶች ባለመብት ዋነኛው ጉግል [634] ነው። ይህ ለኢትዮጵያም ክብር ነው።

ስለ ዶክተሩ ሥራ የኣስተዋወቁና የኣመሰገኑ ከኢትዮጵያውያን ማሕበሮች እስከ ዩኒቨርሲቲ ዩኒየን የኣሉ ቢኖሩም [635] [636] [637] ስለ ሥራዎቻቸው የኣልሰሙም ኣሉ። [638] [639]

በቅርቡ ከኣንድ ኣንባቢ ስለ ዓማርኛና እንግሊዝኛ ኣጻጻፎች ጥያቄ ለግዕዝኤዲት ፌስቡክ (GeezEdit Facebook) (https://www.facebook.com/GeezEdit/) ቀርቦ ነበር። [23] ጽሑፍን በግዕዝ ፊደል መጻፍ ያታርፋል። ኣንድን ገጽ በዓማርኛ ወይም እንግሊዝኛ ጽሑፎች ለመሙላት ዓማርኛውን የበለጠ ጊዜ ይወስድበታል። ምክንያቱም ዓማርኛ ቃላቱን ሲጽፍ ከእንግሊዝኛው በኣንድ ሦስተኛ ግድም በኣነሰ ስፍራ ስለሚያሰፍረው ነው። በእንግሊዝኛ ሦስት ገጾች ለሚያስፈልጉት በዓማርኛው ሁለት ገጾች ገደማ ይበቁታል። ይኸም የሆነበት ግዕዝ ድምፃዊ ፊደል ሲሆን ላቲን ፊደላዊ በመሆኑ ነው። እንግሊዝኛው የሚጻፈው በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ሲሆን ግዕዝ ወደ ኮምፕዩተር ሲገባ በሁለት መርገጫዎች ስለተከተበ እንግሊዝኛው ብልጫ የኣለው ይመስል ነበር። በቅርቡ ግን በዶ/ር ኣበራ ሞላ ግኝት ግዕዝን በኣንድና ሁለት መርገጫዎች መክተብ ስለተቻለ ኣከታተቡ ከእንግሊዝኛው ጋር እኩል ቢመስልም በላጭ ሆኗል። እንግሊዝኛ 47 መርገጫዎች የኣሉትን ኮምፕዩተር ከዝቅ (Shift) መርገጫዎች ጋር በመጠቀም 94 ቀለሞችን ያስከትባል። ግዕዝኤዲት (GeezEdit) የዝቅ መርገጫዎችን ሳይጠቀም ወደ 500 የግዕዝ ቀለሞችን ያስከትባል። ከላይ በቀረቡት ምክንያቶች ስፍራዎች ስለሚያስቀንስ ኣንድን ጽሑፍ ወረቀት ላይና በኮምፕዩተሮች ለማቅረብ ዓማርኛው ያታርፋል ማለት ይቻላል። ለምሳሌ ያህል “ዘ ኲክ ብራውን ፎክስ ጀምፕስ ኦቨር ዘ ሌይዚ ዶግ።” በዓማርኛ በ36 መርገጫዎች ተጽፎ 24 ስፍራዎች ይወስዳል። [640] Archived ኦክቶበር 11, 2017 at the Wayback Machine “The quick brown fox jumps over the lazy dog.” በእንግሊዝኛ በ37 መርገጫዎች ተጽፎ 36 ስፍራዎች ይወስዳል። [641] [24] ይህ የእጅ ስልኮችንም (Smartphones) ኣጠቃቀም ይመለከታል። ስለዚህ ማንኛውንም የግዕዝ ቀለም በሦስት መርገጫዎች መክተብ ጊዜና ስፍራ ያስባክናል። [642] ከላይ የኣሉት ሦስት ምሳሌዎች እንደሚያሳዩት በኣነሰ የኆኄያት ግድፈቶች (Spelling / አስፔሊንግ) እና ስፍራዎች (Space) ማስከተብ ብልጫዎች የነበረው የግዕዝ ፊደል በዶ/ር ኣበራ ግኝት የተነሳ የግዕዝ ፊደል ሓሳብን በኣነሰ ጊዜ (Time)፣ መርገጫዎች (Keystrokes) እና ገበታ (Keyboard) በማስከተብ ብልጫዎቹ ወደ ኣምስት ዓይነቶች ከፍ ብለዋል። ግዕዝ በእራሱ ፊደል እራሱን በዶክተሩ ግኝት ሲከትብ ከእንግሊዝኛው እስፔሊንግ ኣከታተብ የተሻለ ስለሆነ ግዕዝን በእንግሊዝኛ ፊደል እስፔሊንግ የሚያቀርቡትን ኣለመቃወም ሕዝቡን በማጃጃል ቀጥሎበታል።

ግዕዝን ወደ ኮምፕዩተርና ጮሌ ስልክ ሲያስገቡ ፊደሉ የኣገኘውን ኣዲስ ሳይንስና ቴክኖሎጂ በሚገባ እንዲጠቀም ዶክተሩ አቅርበዋል፣ አስተምረዋልም። ይህ መሻሻል ስለኣለበት በየጊዜው መከታተል ያስፈልጋል።

የአክሱም ሐውልት ለማስተካከል

ስለ ዶ/ር አበራ ሞላ [643] [644] እና የአክሱም [645] [646] [647] ሐውልት ከጣልያን ማስመለስ ጉዳይ ያውቁ ኖሯል? [648] Archived ኤፕሪል 3, 2012 at the Wayback Machine [649] Archived ማርች 15, 2012 at the Wayback Machine [650] Archived ኤፕሪል 3, 2012 at the Wayback Machine Aksum [651] Obelisk of Axum [652] [653] ጣልያኖች በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ከኣክሱም የዘረፉትን [654] የኣክሱም ሓውልት [655] Archived ጃንዩዌሪ 7, 2017 at the Wayback Machine እንዲመልሱ በ፲፱፻፵ ዓ.ም. የተባበሩት መንግሥታት ወስኖ ኢትዮጵያ እና ጣልያንም በጉዳዩ ተስማምተው ነበር። የተስማሙትም ጣልያን በኣሥራ ስምንት ወራት በወጪዋ ሓውልቱን ኢትዮጵያ መልሳ ኣክሱም እንድትተክል ነበር። ይህ ስለኣልተፈጸመ በፍርዱ መሠረትሓውልቱ [656] እንዲመለስ ቀዳማዊ ዓፄ ኃይለ ሥላሴ፣ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም እና ኣቶ መለስ ዜናዊ ጠይቀው ጣልያን ለመመለስ ፈቃደኛ ኣልነበረችም። [657] የሰውንም ልመና ስለኣልሰሙ ብስጭቱ ቀጠለ። [658] [659] [660] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine [661]

በኋላም የተተከለበት ሮም ከተማ እንዳለ መብረቅ እንደመታው እንዲመለስ ኣቶ መለስ ዜናዊ ቢጠይቁም ሊያናግሯቸው እንኳን ፈቃደኞች ስለኣልሆኑና [662] [663] [664] ጣልያኖች ስለኣልመለሱት [665] የኢትዮጵያ ወዳጆች ሓውልቱ እንዲመለስ የተቻላቸውን ሁሉ እንዲያደርጉ ግንቦት ፳፭ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. በሮም ንግግራቸው መጠየቃቸው ይታወሳል። [666] [667] የሮም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞም ነበር። ቀደም ብሎም የኣንዳንድ ታዋቂ የዓለም ሰዎች፣ ኢትዮጵያውያንና የኣክሱም ሕዝብ [668] [669] [670] Archived ዲሴምበር 28, 2013 at the Wayback Machine [671] Archived ዲሴምበር 27, 2013 at the Wayback Machine [672] [673] [674] [675] የጥያቄ ፊርማ ጣልያኖችን ከኣለማስጨነቁም ሌላ [676] ሓውልቱ ከተመለሰ ሥልጣኔን እለቃለሁ የኣሉም የጣልያን ባለሥልጣንም ነበሩ። [677] ለኣለመመለስ ከቀረቡት ሰበቦች ሓውልቱ ጣልያን ኣገር ስለቆየ ጣልያናዊ ሆኗል፣ [678] [679] ቀደም ብሎ ፈቅዶት የነበረውን ገንዘብ የለንም በማለት፣ [680] [681] Archived ኤፕሪል 3, 2012 at the Wayback Machine ሓውልቱ ስለኣረጀ ኢትዮጵያ ሲደርስ ይሰባበራል፣ በኣካባቢው ጦርነት ኣለ፣ በገንዘቡ ኣክሱም ያለውን ትልቁን የኣክሱም ሓውልት እንትከልበት፣ [682] መመለስ የሚችለው ኣይሮፕላን ጦርነት ላይ ነው፣ ዓፄ ኃይለሥላሴ ሓውልቱን በስጦታ ለሮም ከተማ ሰጥተዋል [683] ነበሩበት። [684] [685] [686] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine [687] ኢትዮጵያም ሓውልቱን ከፈለገች ለጣልያን መክፈል ኣለባት የኣሉም የጣልያን ኣክራሪ እንደነበሩ በኋላም ተደርሶበታል። [688]

ሓውልቱን መብረቅ ከመታው በኋላ ዶ/ር ኣበራም በግላቸው ለዩናይትድ እስቴትስ ፕሬዚደንት፣ ጥቂት ሴነተሮችና የኮንግረስ ወኪሎች እንዲረዱ የጻፉት ደብዳቤ መልስ ሳያገኝ ቀረ። በመጨረሻም ርዝመቱ 79 ጫማዎችና ክብደቱ 160 ቶን የሆነው ከ፲፯፻ ዓመታት በላይ ዕድሜ ያለው የኣክሱም ሓውልት ሦስት ቁርጥራጮች ተደርጎ መጋዘን የተቀመጠው [689] የትም ኣይሄድም ተብሎ በማዘናጋት ኣጀንዳ ቆየ። [690] ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለስ ኣሜሪካ ኣውሮፕላንና ጣልያን ገንዝብ ከለከሉ የሚለውን የጦቢያ የካቲት ፳፭ ቀን ፲፱፻፺፮ ዓ.ም. (March 4, 2004) ጽሑፍ [691] [692] የዓዩትና የፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክኸርስት በዩናይትድ እስቴትስ መማረር [693] Archived ኤፕሪል 3, 2012 at the Wayback Machine ያላስደሰታቸው ዶ/ር ኣበራ ሞላ ቅር ኣላቸው። በእዚህም የተነሳ ሓውልቱን በትናንሹ ኣስቆርጦ ገንዘብ ከዓለም ሕዝቦች ላይ በኢንተርኔት ማሰባሰብ እንደሚችሉ ኣዲስ ኣበባ ለሚገኘው የጣልያን ኤምባሲ በኢሜይል የካቲት ፳፰ ቀን ፲፱፻፺፮ ዓ.ም. ከዓሳወቁ በኋላ [694] Archived ጁላይ 25, 2015 at the Wayback Machine ኣጣብቂኝ ውስጥ የገባው የጣልያን መንግሥት ወጪውን ከፍሎ ሓውልቱን እቦታው እንደሚተክለው ገለጸላቸው። በተጨማሪም ሌላ የጣልያን ኤምባሲ ባለሥልጣን የሆኑ ዶክተር ሰርቦ ሓውልቱን ለማስጫን ተስማሚ ኣውሮፕላን እያፈላለግን ነው ብለው መጋቢት ፫ ቀን ፲፱፻፺፮ ዓ.ም. (March 12, 2004) ለዶ/ር ኣበራ ኢሜይል ላኩ። ይኸንንም ለሓውልቱ መመለስ ለኣያሌ ዓመታት ሲታገሉ ለነበሩት ፕሮፌሰር ገልጸው ሓውልቱን መብረቅ ከመታው በኋላ ሊረዱዋቸው ስለጀመሩ በኢሜይል ይጻጻፉ ስለነበረ ላኩላቸው። ፕሮፌሰር ፓንክኸርስትም የዶክተሩን ሓሳብ ከሰሙ በኋላ የታችኛውን ሁለት ማስቆረጥም እንደሚያስፈልግና ገንዘብ ሊዋጣ እንደሚችል ጣልያኖችን ማሳወቅ እንዲከፍሉ ሊያስገድዳቸው ሳይችል እንደማይቀር ደግፈው ኣስታውቀዋቸው ነበር። ግንኙነት ስለኣልነበራቸው ለኢትዮጵያ ባለሥልጣኖች ግን ሳያሳውቁ [695] [696] [697] ኣንዳንዶቹን ጽሑፎች ኢትዮፒክ.ኮም ድረገጻቸው ላይ ቢያስቀምጡም ብዙዎቹ ስለኣላነበቡት ጣልያን ወጪውን ለምን ለመክፈል እንደተስማማች ቢጻፍም በጊዜውና እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሳይታወቅ የቆየ ይመስላል። [698] [699] [700] [701] [702] ለኢትዮጵያ መንግሥት ግን ጣልያኖች ገንዘቡን እንደሚከፍሉ [703] እስከ ሓምሌ ፺፮ ዓ.ም. ድረስ ያላሳወቁ [704] [705] [706] [707] ይመስላል። [708] ጣልያኖች ቃላቸውን ደጋግመው ስለኣጠፉ እንደሚመልሱ የተስማሙበትንና የዶክተሩን ጉዳይ በሚገባ የሚያውቁት ፕሮፌሰር ፓንክኸርስትም ታግሰዋል። [709] ስለ ገንዘብና ኣይሮፕላን መጥፋት ጣልያኖች ሲያወሩ መቆየታቸውን ዘ ጋርድያን ጋዜጣ (The Guardian, July 16, 2004) የኣተመው ኣንድ ምሳሌ ነው። [710] በእዚህም ጊዜ (ሰኔ፣ ፺፮) ለሓውልቱ የብረት ማቀፊያ ተሠራለት።

በመጨረሻም ሓውልቱ በ፺፰ ሲመለስ እንኳን ደስ ያለዎት የሚል የምስጋና ኢ.ሜይል ዶክተሩ ስለጉዳዩ ለዓመታት ለታገሉት ፕሮፌሰር ላኩ። ኤምባሲውም ዶ/ር ኣበራን ድንጋይ ከምታመላልስ ለረሃብተኛው ሕዝብ በገንዘቡ እህል ግዛበት ያለበትን ኢሜይል ኣስታውሰዋቸው ሓውልቱ ኢትዮጵያ ሲደርስ ፕሮፌሰሩ ደረሰኝ ብለው ከኣቀረቡት የእንግሊዝኛ ኢ.ሜይሎች መካከል የዶክተሩ ኣንዱ ነበር። [711] [712] ኣሜሪካኖችም የሓውልቱን ቁርጥራጮች ትክክለኛ መጠን ለማወቅ ተጠይቀው ያወጡትን ወጪና የኣክሱም ኣይሮፕላን ማረፊያ ችሎታ ያጠኑበትን ገንዘብ ጣልያኖች ኣልከፈሉንም ብለዋል። [713] በእዚህ ኣኳኋን ወደ ስምንት ሚሊዮን ዶላር የጣልያን መንግሥት ወጪ [714] ሓውልቱ በሩስያ ኣንቶኖቭ ኣይሮፕላን ከጣልያን ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ [715]የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት መኃንዲሶች እርዳታና ሥራ (ኢንጂነር ክሮቺ) [716] ኣክሱም ተተክሎ ነሓሴ ፳፱ ቀን ፳፻ ዓ.ም. ተመርቋል። [717] Archived ማርች 15, 2012 at the Wayback Machine [718] ቪድዮዎችም እዚህ [719] [720] [721] ኣሉ።

ዓፄ ኃይለሥላሴ ሓውልቱን ጣልያኖች ከኣክሱም ሲወስዱትም ከመቃወማቸውም ሌላ ለብዙ ኣሥርት ዓመታት ሓውልቱ እንዲመለስ በሮም የኢትዮጵያ ኣምባሳደሮችና በየተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ወኪሎች ጠይቀዋል። [722] የኣክሱም ሓውልት ከሮም ወደ ኣክሱም እንዲመለስ በዓፄ ኃይለሥላሴ ዘመን መንግሥት የኢትዮጵያ ምክር ቤት ጠይቆ ነበር።

ፕ/ር ፓንክኸርስት የኣክሱም ሓውልት ለኢትዮጵያ እንዳልተመለስ ለኣንድ የጣልያን ጋዜጣ በ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. የጻፉትን የኣነበቡ ብሩኖ ኢምፔሪያሊ ለኣንድ ጋዜጣ የድጋፍ ደብዳቤ ጻፉ። የተጻፈውን የኣነበቡ ቪንሴንዞ ፍራንካቪግሊያ፣ ጁይሴፔ ኢንፍራንካ እና ኣልበርቶ ሮሲ የተባሉ ምሁራን ሓውልቱ እንዲመለስ ለጣልያን መንግሥት ደብዳቤ ከጻፉ በኋላ ፕሮፌሰሩም ይኸን ድጋፍ እንደሰሙ ኢትዮጵያውያን ፊርማ እንዲያሰባስቡ ጠየቁ። በእዚህም በመተባበር ከ500 ፊርማዎች በላይ በማሰባሰብ ከተሳተፉት መካከል ኣሰፋ ገብረማርያም፣ ልጅ ሚካኤል ዕምሩሺፈራው በቀለ፣ ክሎውድ ሰምነር፣ ደኒስ ጀራርድ፣ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም፣ ክቡር ደጃዝማች ዘውዴ ገብረሥላሴሎሬት ፀጋዬ ገብረመድኅንተክለጻዲቅ መኩሪያተፈራ ደግፌ፣ ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ፣ ፕ/ር ኣቻምየለህ ደበላ፣ ፕ/ር ኣሸናፊ ከበደካሳሁን ቸኮል፣ ሃሪ ችሃብራና ራስተፈሪያን ነበሩበት። በዓመቱም ፕሮፌሰሩን የጨመረ ፲ ሰዎች የኣሉት የኣስመላሽ ኮሚቴ ተቋቋመ። ፕ/ር ፓንክኸርስት ስለ ጉዳዩ ካነሱበትና ሌሎችም በእየጊዜው ሲጽፉ ሓውልቱን ለማስመለስ ከ፲፱፻፹፭ ዓ.ም. ጀምሮ የኣምስት ዓመታት የኣስተዋጽዖ ዝርዝር ውስጥ የሚከተሉት ኣሉበት። [723] [724] Archived ዲሴምበር 28, 2013 at the Wayback Machineኣዲስ ኣበባ ምክር ቤት[725]ኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የጥያቄ ፊርማ፣ ፕ/ር እስቲቨን ሩበንሰን፣ ፕ/ር ደኒስ ማክ እስሚዝ፣ ኣቡነ ጳውሎስ ፭ተኛ፣ ዶ/ር ሳሊም ኣህመድ ሳሊም፣ ፕ/ር ፓስካል ጄ. ኢምፐራቶ፣ ፕ/ር ፍረደሪክ ጋምስት፣ ፕ/ር ኖርማ ኮምራዳ፣ ራጌሽዋር ሲንግ፣ ባማን ኣሊፍ፣ ዶ/ር ነቪል እስሚዝ፣ ሲይልቭያ ኤይሊንግ፣ ግለንዳ ጃክሰን፣ ኣቶ ገብሩ ኣሥራት፣ ፊታውራሪ ኣመዴ ለማ፣ ፊታውራሪ ኣበባየሁ ኣድማስ፣ ቀኛዝማች ቢያዝን ወንድወሰን፣ ሻምበል ምሩጽ ይፍጠር፣ ሻለቃ ዻራርቱ ቱሉ፣ ዶ/ር ፈቃዱ ገዳሙልዑልሥላሌ ተማሙ፣ ኢንጂነር ታደለ ብጡልተስፋዬ ዘለለው፣ ሚስስ ዊንዞፕ ቦዝወል፣ ኣንጀሎ ደል ቦካ፣ ዶናልድ ክረሜይ፣ ጆን እስፔንሰር፣ ዴቪድ በክስተን፣ ኣልበርቶ እስባክቺ፣ ሰይድ ሳማታር፣ ቪራጅ ጉፕታ፣ ፕ/ር ሃጋይ አርሊችሪቻርድ ግሪንፊልድ፣ ፒተር ጋረትሰን፣ ዩሪ ኮቢስቻኖቭ፣ ማርያ ራይት፣ ካትሱዮሺ ፋኩይ፣ ጃክ ጎትሌ፣ ፕ/ር ኢማኑኤል ሴሚ፣ ሮጀር ሽናይደር፣ ፕ/ር ክሪስቶፈር ክላፋም፣ ፕ/ር ፍረድሪክ ሃሊደይ፣ ፖውል ብሪትዝኪ፣ ኣሊ ማዝሩይ፣ ቶማስ ፓከንሃም፣ ኮህን ለጉም፣ ኬረን ዳልተን፣ ሆዜ ጃፊ፣ ፕ/ር ዊሊያም ዲያኪን፣ ዶ/ር ኪርስተን ፒደርሰን፣ ካትርይን ባርድ፣ ዶ/ር ረይደልፍ ሞልቬር፣ ኣይቫን ኣድለር፣ ዊልፍረድ ተሲገርግራሃም ሃንኮክ፣ ሰር በርናርድ ብሬይን፣ ሉትዝ ቤከር፣ ሮደሪክ ግሪየርሰን፣ ሪታ ማርሌይ፣ ጀርሜን ግሪር፣ ሲሮ ታደኦ፣ ኒኮላ ደማርኮ፣ ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅ፣ ፕ/ር ሥዩም ገብረእግዚኣብሔር፣ ዶ/ር ጌታቸው ኃይሌ፣ ፕ/ር ኣሸናፊ ከበደ፣ ዶ/ር ካሳሁን ቸኮል፣ ዶ/ር ኣስፋወሰን ኣስራቴ፣ ልጅ ዘውዴ ኃይለማርያምሳሙኤል ፈረንጅ፣ ሪቻርድ ባልፍ፣ ሃሪ ካህን፣ ዶ/ር ካሳይ በጋሻውሪታ ፓንክኸርስት፣ ክቡር ደጃዝማች ዘውዴ ገብረሥላሴ፣ ኣርቲስት ኣፈወርቅ ተክሌ፣ ሴጉን ኦሉሶላ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ይገኙበታል። [726]

ሰለ ሓውልቱ ጉዳይ በየጊዜው በመጻፍ ከተራዱትም ውስጥ “ኢትዮፒያን ሪቪው” (ኤልያስ ክፍሌ)፣ “ኢትዮፕያን ሬጂስተር” (ግርማ በቀለ)፣ “ኢትዮፕያን ኮመንቴተር”፣ “ኣዲስ ትሪብዩን” እና “ቤዛ” ተጠቅሰዋል። ሓውልቱ እንዲመለስ እስከ ፲፱፻፺ ዓ.ም. እንቅስቃሴውን በመቀጠል ከተዘረዘሩት መካከል የሚከተሉት ኣሉበት። [727] Archived ዲሴምበር 27, 2013 at the Wayback Machine የኣክሱም ሓውልት ኣስመላሽ ኮሚቴ፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ፣ ኣቶ ኃብተኣብ ባይሩ፣ ፕ/ር ሳሙኤል ኣሰፋ፣ ኣቶ ዳዊት ዮሓንስየኢትዮጵያ ፓርላማ፣ ፕ/ር ባሕሩ ዘውዴ፣ ማርኮ ቪጎኒ፣ የትግራይ ክልል ፓርላማ፣ ቶኒ ሂኬይ፣ ናፍታለም ኪሮስ፣ እስቲፈን ቤል፣ ኣልበርቶ ኢምፔሪያሊ፣ የሮም ኢትዮጵያውን፣ ጃራ ኃይለማርያም፣ ክቡር ኣቶ ወልደሚካኤል ጫሙ፣ ክቡር ኣቶ ሥዩም መስፍን፣ ፕ/ር ፍራንካቪግሊያ፣ በላይ ግደይ፣ ዶ/ር ተቀዳ ዓለሙ፣ ፕ/ር እንድርያስ እሸቴ [728] [729]፣ ፕ/ር ኣበበ ከበደ [730] [731] ፣ ክቡር ኣቶ ተሾመ ቶጋ፣ ጆርጅዮ ክሮቺ፣ የታዋቂ ኢትዮጵያውያን ፊርማ፣ ፲፬ሺህ ፊርማ የፈረሙ የኣክሱም ሕዝብና ብዙ ሺህ ፊርማ ያለው በዓለም ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያና ሌሎች የጥያቄ ፊርማ (ፔቲሽን)፣ የጥቂት ኣፍሪቃ ኣገሮች ኣምባሳደሮች ደብዳቤዎችና ሌሎችንም ጠቅሷል። ስለ ፊርማውም በማሰማት የቢቢሲ ሬድዮና ቴሌቪዥን፣ የካናዳ ሬድዮ፣ የእንንግሊዝ፣ የጣልያንና ኣንዳንድ የዓለም ጋዜጣዎች ትኩረት በመስጠት ረድተዋል። ኣንድ ቪድዮም ተሠርቶ ነበር። ለእዚህ ጉዳይ ከተረባረቡት መካከልም ብርሃኑ ተሰማልዑልስገድ ተማሞቢያዝን ወንድወሰንኣበባየሁ ኣዳማኣፍሮሜት (AFROMET)፣ ኣሉላ ፓንክኸርስት፣ ታጋስ ኪንግ፣ ቶኒ ሂኪ፣ ሬናቶ ኢምፔሪያሊ፣ ጌይል ዋርደን እና ኣንድሩ ሎውረንስ ነበሩ። እዚህ የቀረበው በስም የተጠቀሱትን ብቻ ስለሆነ ወደፊት ማሟላትና ስለ እያንዳቸውም በስማቸው መጻፍ ይቻላል። ከእዚህ ሁሉ ድካም በኋላ ጣልያኖች ሓውልቱን እንደሚመልሱ ቃል ገብተው በ፲፱፻፺ ዓ.ም. ይመለሳል ተብሎ (ኢትዮጵያም ፕሮፌሰር ፓንክኸርስት የኣሉበት የኣክሱም ሓውልት ኣስመላሽ ኮሚቴ በ፲፱፻፹፭ ዓ.ም. ተቋቁሞም ስለነበረ (በ1988 ዓ.ም. ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በተጻፈ ደብዳቤ ለማስታወቂያና ባህል ሚኒስቴር ሐውልቱን ለማስመለስ የሚረዳ ብሔራዊ ኣስተባባሪ ኣካል እንዲቋቋም በተጠየቀው መሠረት፣ ሓውልት ኣስመላሽ ብሔራዊ ኮሚቴም ተቋቁሞ ነበር።) [732] ) የጣልያን ፕሬዚደንት ኢትዮጵያን ሲጎበኙ ይቅርታ ከጠየቁም በኋላ የመመለሱ ጉዳዩ በወሬ ቀረ። [733] [734] [735] [736] [737] [738] ይህ የኢትዮጵያና የጣልያን ጠቅላይ ሚኒስትሮች ስለ ሓውልቱ መመለስ ከተፈራረሙና ቴምብር ሁሉ ከተሠራ በኋላ ነበር። በመጨረሻም በዶ/ር ኣበበ ከበደ የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎች ኔትወርክ [739] [740] በኩል ለጣልያን ጠቅላይ ሚኒስቴር በእንግሊዝኛና ጣልያንኛ የተጻፈው የልመና ደብዳቤ (14 June 2001) መልስ ሳያገኝ ቆይቶ በዓመቱ ግድም ሓውልቱን መብረቅ መታው። ሓውልቱን መብረቅ ሳይመታው ከስድስት ወራት ቀደም ብሎ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስርት ለጣልያኑ ኣቻቸው በነበሩት ውለታዎች መሠረት ሓውልቱ እንዲመለስ ደብዳቤ ጽፈው መልስ እንኳን ተነፈጋቸው። [741]

እንዲህም ሆኖ ሓውልቱ እንዲመለስ የደገፉ ጣልያኖች ነበሩ። የጣልያን መንግሥት ግን ለመመለስ ፈቃደኛ ስለኣልነበረ ተስፋ ተቆርጦ ነበር። [742] የሓውልቱ መመለስ ጉዳይ እንደገና ያንሰራራው ጣልያኖች ሓውልቱን ሮም ሲተክሉት ብረት ኣስገቡበት እንጂ ከመብረቅ ስለኣልተከላከሉት ግንቦት ፲፯ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. (May 28, 2002) [743] መብረቅ ከመታውና ከላይ በኩል ተሰብሮና ከተጎዳ በኋላ ነበር። [744] [745] [746] ምክንያቱም ሌላ መብረቅ ቢመታው ሓውልት መሆኑ ቀርቶ የድንጋይ ክምር ሊሆን ስለሚችል ከልመና ያለፈ ኣስቸኳይ እርምጃ በኣንዳችን መወሰድ ስለነበረበት ነው ዶክተሩ በግላቸውና በብቸኝነት በጉዳዩ የገቡበት። የሚያሳዝነው ግን ሓውልቱን መብረቅ ከመታውም በኋላ እንኳን ለኢትዮጵያ እንዳይመለስ ተቋውሞ መቀጠል ነበር። [747] [748] [749]

ከእዚህ በላይ ለተዘረዘሩትና ሌሎችም ለኢትዮጵያ ስለ ኣደረጉት ኣስተዋጽዖ በተለይ ለፕሮፌሰር ፓንክኸርስት እግዜር ውለታቸውን ይመልስልን። [750] Archived ማርች 15, 2012 at the Wayback Machine [751] ጣልያኖች የኣድዋን ድል ለመበቀልና [752] ኢትዮጵያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጣልያንን ለሁለተኛ ጊዜ ስለ ኣሸነፈች ተበሳጭተው ሓውልቱ ላይ ቢንጠላጠሉም [753] [754] ከኣክሱም የወሰዱትን ሓውልት ሌላ ትውልድ ኣስመልሷል። [755] [756] [757] [758] Archived ኦክቶበር 19, 2014 at the Wayback Machine [759] [760] ታሪኩ እንዳይጠፋ ኣንድ ቦታ መጻፍ ተገቢ ነው። [761] ሓውልቱም ግዙፍ፣ ታዋቂና ተደናቂ በተባበሩት መንግሥታት የተመዘገበ የዓለም ቅርስ [762] እንጂ ጉራም ኣይደለም። [763] ይህ ሲደረግም በየተባበሩት መንግሥታት ስምምነት መሠረት ይኸን ትልቅ ቅርሷን [764] ለማስመለስ ለዓመታት ስትታገል ኢትዮጵያን የረዳት መንግሥት ኣልነበረም። [765] [766] የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት እንኳን ሓውልቱን መብረቅ ከመታው በኋላ ለኢትዮጵያ ይመለስ ኣላለም። [767] [768] ማንም ኣያስገድደንም ብለው የዓለም ሕዝቦች ላይ ሲቀልዱ የነበሩትን ጣልያኖች [769] Archived ማርች 4, 2016 at the Wayback Machine ኣንድ ሰው ሊያስመልሰውና እንደሚዋረዱ ኣስጠንቅቆ ሓውልቱን በማስገደድ ከማስመለስ በስተጀርባ ትምህርትነትም ኣሉት። [770] ጣልያኖች የኣክሱምን ሓውልት ዘርፈው ከ፷፱ ዓመታት በኋላ በ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. የመለሱት በዶክተሩ እንዳይዋረዱ ተገድደው እንጂ ወደ'ው ኣይደለም። [771] ጣልያኖች በዶክተሩ ያለጉራ የተሰጣቸውን በጎ ፈቃድ [772] Archived ጁላይ 25, 2015 at the Wayback Machine ተጠቅመው ሓውልቱን ቢመልሱም በፈቃዳችን መለስን ብለው ሸንግለዋል። [773] [774] [775] [776] [777] [778] ምክንያቱም በፈቃድ ለመመለስ ብዙ ኣሥርት ዓመታት መፍጀት ባላስፈለገ ነበር። በፈቃድ ለመመለስ ቆራርጠው ድንጋያችሁን ውሰዱ በኣላሉ ነበር። [779] በፈቃድ ለመመለስ ቆራርጠው ከኣስቀመጡበት ሮም ከተማ ለዘለዓለሙ የትም ኣይሄድም በኣላሉ ነበር። ከእዚያም ወዲህ ከዘረፏቸው መካከል እንኳን በፈቃዳቸው ተለምነውም ለኢትዮጵያ የመለሱት ሌላ ቅርስ የለም። [780]

የኢትዮጵያ መሪዎች [781] ሥልጣን ላይ ሲያተኵሩ ግፍ የሠሩባት ለፍርድ ሳይቀርቡና በቢሊዮን ዶላሮች ሊቈጠር የሚችል ካሳ ጣልያንን ኣልኣስከፈሉም። [782] (ሆኖም ሓውልቱ ሮም ሲነቀልና ኢትዮጵያም ሲተከል ጣልያኖች ከኢትዮጵያውያን ጋር ተባብረዋል።) [783] ግን፤ ይባስ ብለው ጣልያኖች በ፳፻፬ ዓ.ም. ለግፈኛው ግራዚያኒ ሓውልት ስለሠሩ ከታሪክ መማር ሳይጠቅመን ኣይቀርም። [784] [785] [786] [787] [788] [789] [790] [791]ቫቲካን ካቶሊክ ጳጳሶችም ከፋሺስት ጋር በመተባበር ወረራውን ቄሶቻቸው ስለባረኩና ስለሌሎች ጥፋቶችም ይቅርታ መጠየቅ እንኳን ከብዷቸዋል። [792] Archived ማርች 15, 2012 at the Wayback Machine በእዚህ ጉዳይ ለሃገር በመቈርቈር ኢትዮጵያ ፍትሕ እንድታገኝ የሚታገሉ ኣሉ፦ ኪዳኔ ዓለማየሁ[793] Archived ሴፕቴምበር 11, 2017 at the Wayback Machine የኣሁኖቹም መሪዎች ስልጣን ላይ እየኣሉ ጣልያን ለግራዚያኒን የሠራችውን ሓውልት እስክታፈርስ [794] [795] (እንደእነ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም የኣሉትን ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ከማሰር ይልቅ [796]) ዲፕሎማቲክ ግንኙነት ማቋረጥ ያንስባቸዋል።

በ፳፻፮ ዓ.ም. ጄፍ ፒይርስ (Jeff Pearce) የሚባሉ ታዋቂ ካናዲያዊ ደራሲ ስለ ኢትዮጵያውያን ጀግንነትና ጣልያንን በድጋሚ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት በማሸነፍ ዓለምን እንደቀየሯት በጻፉት "Prevail" (ISBN: 978-1-62914-528-0 አና ISBN: 978-1-63220-096-9) መጽሓፋቸው የኢትዮጵያን በደል የማይረሱ ዛሬም እንዳሉ በማሳሰብ ስለ ኣክሱም ሓውልት ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ሲያሰፍሩ ዶክተሩን (Dr. Aberra Molla) ገጽ 552 ላይ ጠቅሰዋል። “Besides Richard Pankhurst, who spearheaded the fight, there was Ethiopian-American scientist, Dr. Aberra Molla. There was...” በማለት ጽፈዋል። የፒይርስን መጽሓፍ መግቢያ የጻፉት ፓንክኸርስት ናቸው። [797] [798] [799] [800] [801] [802] [803] [804] Archived ማርች 7, 2016 at the Wayback Machine [805] [806] [807] ስለ ዶክተሩ ኣስተዋጽዖ የኣሰሙም ጥቂቶች ኣሉ። [808] [809] [810] [811] ኢትዮጵያን-ኣሜሪካን ፎረም ዶክተሩን የ2013 የዓመቱ ሰው በማለት ዕውቅና ሲሰጣቸው ከኣቀረባቸው ሥራዎቻቸው ኣንዱ ጣልያን የኣክሱምን ሓውልት በወጪዋ ስለኣልመለሰች እሳቸው ገንዘቡን ከዓለም ሕዝቦች በማሰባሰብ ሓውልቱን በትናንሹ ኣስቆርጠው ወደ ኢትዮጵያ ሊያስወስዱ እንደሚችሉ ከኣስፈራሩ በኋላ መሳካቱን ጠቅሷል። [812] በሓምሌ ፳፻፰ ዓ.ም. ዶክተር ኣበራ ንግግር እንዲያደርጉ የተጋበዙበት የዝነኛው ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተቋም የግብዣ ደብዳቤ ትርጕም እንደሚከተለው ነበር። “ዓማርኛን ዲጂታይዝ በማድረግዎ ተወዳዳሪ የሌለው ዘመናዊ እድገት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲኖር ኣድርገዋል፣ እንዲሁም ተጽንእዎ ባህላዊ ቅርሶችን ወደ ማስጠበቅ ዘልቆ የኣክሱምን ሓውልት ወደ ትግራይ ሲያስመልሱ በጉዳዩ ባይገቡበት ኖሮ ይህ የኢትዮጵያ ቅርስ ላይመለስ ይችል ነበር” ይላል። [813] የኢትዮጵያን ቅርሶች በማስከበርና በጥሩ ዓርዓያነት እ.ኤ.ኣ. በ2016 ሽልማት ተሰጥቷቸዋል። በቅርቡም በፕሮፌሰር ፓንክኸርስት ከእዚህ ዓለም በሞት መለየት የተነሳ ሓውልቱን ኣስመልክቶ ከሰይፉ ብሻው ጋር የተደረገ ቃለምልልስ እዚህ ኣለ። [814] ቀደም ብሎም (፳፻፯) ከኢሳት ሲሳይ ኣጌና ጋር በተደረገው ቃለ ምልልስ ስለ ኣክሱም ሓውልት ኣስተዋፅዖዋቸው እዚህ [815] Archived ጁን 22, 2015 at the Wayback Machine [816] ነበር። ዶክተሩ ከብዙ ዓመታት ቆይታ በኋላ ኢትዮጵያ ሄደው ሳለ የኣክሱምን ሓውልት ጎብኝተዋል። በኅዳር ፳፻፲ የኢትዮጵያ ቅርስና ውርስ ማሕበረሰብ በሰሜን ኣሜሪካ የዕውቅና ሽልማት ለዶ/ር ኣበራ ሞላ ሲሰጥ ከጠቀሳቸው ኣንዱ የኣክሱም ሓውልት ከሮም ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ጣልያንን በማስፈራራት ወሳኙን እርምጃ የወሰዱ ኣርበኛ መሆናቸውን ነበር። [817] Archived ሴፕቴምበር 2, 2018 at the Wayback Machine

በግንቦት 2008 ዓ.ም. በኣገራዊ የዕውቅናና የሽልማት ፕሮግራም ኣዲስ ኣበባ ሲደረግ ሟቹን ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ጨምሮ ሌሎች 250 ሰዎችና ለሓውልቱ መመለስ ጥረት ያደረጉ የኣስመላሽ ብሔራዊ ኮሚቴ አባላትና ባለሃብቶችን የኣካበተ ነበር። [818] ለጥረቱ ሽልማት መሰጠት ያስፈለገው ኣንዳቸው ኣሜሪካ መጥተው ሓውልቱን ኣስመለስኩ ሲሉ ማን እንዳስመለሰ ከተነገራቸው በኋላ ነበር።

የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ለማስተካከል

ስለ ዓማርኛ የጽሕፈት መኪና በዓማርኛም ሆነ በእንግሊዝኛ የተጻፉ ኢንተርኔት ላይ ብዙ የሉም። በእንግሊዝኛው እንደሚደረገው ኢትዮጵያውያን ፊደላቸውን በመጻፊያ መኪና መሣሪያ (Amharic typewriter / አማርኛ ታይፕራይተር) [819] ለመጠቀም ተመራምረው ከደረሱበት ዘዴ ፊደላቱን ቆራርጦ መቀጠል (Ligature) የኢ/ር ኣያና ብሩ የ፲፱፻፳፭ ዓ.ም. (እ..ኤ.ኣ. 1932) ገደማ ግኝት ሥራ ላይ ውሏል። [820] በእዚህ የተነሳ ኢንጂነሩ ለኢትዮጵያ ባለውለታ ሊቅ ናቸው። ከመቶ በታች መርገጫዎች የኣሉት የእንግሊዝኛ የመጻፊያ መሣሪያ ከሁለት መቶ በላይ ለሆኑት የዓማርኛ ቀለሞች እንዲብቃቃ ፊደላቱን ቆራርጦ መቀጠል ኣስፈለገ። “ሀ”፣ “ለ”፣ “ሐ”፣ “መ” እና “ሠ” ኣሉ እንጂ “ሁ”፣ “ሉ”፣ “ሑ”፣ “ሙ” እና “ሡ” ስለሌሉ የመቀነስ ምልክትን የመሰለ “-” ከሌላ መርገጫ በመክተብ “ሀ”፣ “ለ”፣ “ሐ”፣ “መ” እና “ሠ” ጎን በማስቀመጥ ቅጥሎቹ ካዕቦቹን ስለሚመስሉ ተመልካቹ እንዲቀበላቸው ሆነ። ኣንዱን መቀጠያ ብዙ ቀለሞች ሊጋሩት ስለሚችሉ የሁሉም ቀለሞች በኣለመኖር የተነሳ መርገጫዎች መቆጠብ ተቻለ። “ሃ” እና “ማ’ እንጂ “ሂ”፣ “ሚ”፣ “ሄ” እና “ሜ” ስለሌሉ “ሃ” እና “ማ” እግሮች ጎን መስመር ወይም ቀለበት በማስቀመጥ እነዚያን በሚመስሉ ቅጥሎች እንድንጠቀም ሆነ። እነ “ቻ”ን የመሰሉ ቀለሞች ከታችና ከላይ ከሁለት መርገጫዎች “ተ” ላይ በሚቀጠሉ ነገሮች ስፍራው ወደኋላ እየተመለሰ ሦስት ነገሮች ኣንድ ፊደል እንዲመስል ተሠሩ። ስፍራ ስለኣነሰ እንደነ “ኳ” ያሉ ቀለሞች “ካ” ስር በተቀመጠ መስመር በሚሠሩ ኣዳዲስ ቀለሞች ተተኩ። የ“ላ”ን ግራ እግር ማሳጠር ስለኣልተቻለ “ለ” ቀኝ እግር ላይ ከመስመር በታች በወረደ መቀጠያ የ“ለ” ቀኝ እግር ረዝሞ ያልተለመደ መልክ ይዞ ቀረበ። በመቀጠል ሊሠሩ ለማይችሉ ቀለሞች የእራሳቸው ስፍራ ሲሰጣቸው ቦታ ስለኣልበቃ ካልገቡት መካከል የዓማርኛ ኣራት ነጥብ ኣሉበት። [821] Archived ሴፕቴምበር 6, 2013 at the Wayback Machine ስለዚህ የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና የተመረኮዘውና ኣከታተቡ የተንፏቀቀ ፊደል በኣንድ የእንግሊዝኛ ገበታ ምትክ መቀጠል ላይ ነው። የዓማርኛ ቀለም ግን እያንዳንዱ እራሱን የቻለ ስለሆነና ኣንድ የእንግሊዝኛ የፊደል ገበታ ስለማይበቃው የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ፊደል ዓማርኛ ኣይደለም። [822] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine ፊደላት ለኮምፕዩተር ሲሠሩ ተለያይተው እንዲቀርቡ ሲደረግ የታይፕራይተሮቹ ግን እንዲነካኩ ተንፏቅቀው የተሠሩ ስለሆኑ ቦታዎቻቸውን የኣልጠበቁም ናቸው። ይህ ሁሉ ሲደረግ እንደእነ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት የመሳሰሉት ሲጠቀሙ የነበሩት በትክክለኛዎቹ የግዕዝ ቀለሞች ነበር። የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና [823] በዓፄ ኃይለሥላሴ ዘመን ተጀምሮ በደርግ ዘመን የኣበቃ የ፶ ዓመታት ግድም ዕድሜ የነበረው ቴክኖሎጂ ነው። የኣማርኛ ታይፕራይተር የሠሩ ሌሎችም ኣሉ። የኣማርኛ ታይፕራይተር ቴክኖሎጂ ያበቃለትም ዶክተር ኣበራ ሞላ የግዕዝን ፊደል ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው እ.ኤ.ኣ. በ1987 ሞዴትን ለገበያ ኣሜሪካ ውስጥ ስለኣቀረቡ ነበር። ስለዚሁ እውነታ ማቲው ሊንዳ በቅርቡ እንደጻፉት ዶ/ር ኣበራ ሞላ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ በማድረግ የዓማርኛውን ታይፕራይተር ሥራ ኣጥ ኣድርገውታል ይላል። Lindia, Matthew S. "Following Orders: A History of Amharic Typing." Book History, vol. 25 no. 2, 2022, p. 425-442. Project MUSE, doi:10.1353/bh.2022.0015. (https://muse.jhu.edu/article/872061 )

የዓማርኛ ፊደል የመክተቢያ ገበታና ዘዴ ስለ ኣልነበሩት ዶክተሩ ፊደሉን ወደ ኮምፕዩተር ሲያስገቡ ዘዴዎቹን ለመጀሪያ ጊዜ ከመፍጠር ሌላ [824] የዓማርኛ የመጻፊያ መኪና ቅጥልጥል ፊደልና ኣከታተቡ ወደ ኮምፕዩተር እንዳይገባ ጽፈዋል። [825] ኣንዳንዶቹም የቆዩና ኣዳዲስ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው። ፩ኛ. የዓማርኛ ፊደላት ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆኑ ዓማርኛ ያልሆኑ ፊደላት መኖር ዋጋ የለውም። በእንግሊዝኛው የጽሕፈት መኪና በዓማርኛ ለመጠቀም የተሠራው ዘዴ ጊዜው ያለፈበት ቴክኖሎጂ ነው። እንኳን ዓማርኛውን የማይጽፍ የጽሕፈት መኪና በሚገባ እንግሊዝኛውን የሚጽፈው የእንግሊኛ የጽሕፈት መኪና ዋጋ ኣጥቶ ሙዚየም ገብቷል። ስለዚህ የኮምፕዩተር ኣከታተብ ማሰልጠኛዎች የኣማርኛ ታይፕራይተር ኣከታተብ ማስተማር መተው ይጠበቅባቸዋል። ፪ኛ. የእንግሊዝኛው የመጻፊያ መኪና የተሠራው ለእያንዳንዱ የላቲን ፊደል መክተቢያና የመርገጫ ስም በመመደብ ሲሆን የዓማርኛው የመጻፊያ መኪና እነዚያን የሉትም። ዶክተሩ ለግዕዙ መክተቢያና የመርገጫ ስም ለመጀመሪያ ጊዜ ለኮምፕዩተር ፈጥረውለታል። ፫ኛ. የዓማርኛ የመኪና ፊደላት የሚሠሩት ለተወሰነ መጠን ተስተካክለው ወረቀት ላይ እንዲሰፍሩ ነው። በኮምፕዩተር ግን ኣንዱን መጠን መጨመርና መቀነስ ይቻላል። የመኪና ፊደላት ቁርጥራጮች መጠን ሲለወጥ ቅጥሎቹ ይደበቃሉ ወይም ክፍተታቸው ይጨምራል። የገጹ ስፋት ሲጠ'ብ ወይም ሲሰፋ ቅጥሎቹ ብቻቸውን ወደ ኣዲስ መስመር ሊዞሩ ይችላሉ። ቅጥሎቹ ስለሚበጣጠሱ ማሕተምን የመሳሰሉ ነገሮች ኣያሠሩም። ስለዚህ ቅጥልጥል የመኪና ቀለሞች የትክክለኛው ፊደል ተጠጊ እንጂ እራሳቸውን ችለው ሁሉንም ሥራዎች ስለማያሠሩ ኣስፈላጊ ኣይደሉም ብለው ዶክተሩ ጽፈዋል። በቅጥሎች ተንቀሳቃሽ የሚገላበጡ የሲኒማ፣ ቴሌቪዥና ቪድዮ ፊደላት ሊሠሩባቸው ኣይችልም። ፬ኛ. የላቲኑ የመጻፊያ መኪና እያንዳንዱን ቀለም የሚከትበው በኣንድና ሁለት መርገጫዎች ሲሆን የዓማርኛው መኪና ከእዚያ በላይ መርጫዎችን ይጠይቃል። ስለዚህ ዓማርኛ ሳያስጽፍ ብዙ መርገጫዎችን መነካካት በሚያስፈልግ ዘዴ ግዕዝ ኮምፕዩተራይዝድ ሆኖ ከቀረበ ከ፴ ዓመታት በኋላ ዛሬም በ፳፻፱ ዓ.ም. መቀጣጠል ጥቅም የለውም። [826]ኣብሻ ሥርዓት የተከተበውን ትክክለኛ ቀለም ለመሰረዝም ኣንድ መርገጫ በቂ ነው። ለኣስቀጣይና ተቀጣይ ግን ኣንድ መሰረዣ በቂ ኣይደለም።

፭ኛ. ወረቀት ላይ ሲሰፍሩም ሆነ የኮምፕዩተር እስክሪን ወይም መዝገብ ኣብዛኛዎቹ የዓማርኛ መኪና ፊደላት ከኣንድ በላይ ስፍራና ኮድ ይጠይቃሉ። [827] ይህ ወጪ ያስጨምራል። የግዕዝና የላቲን የኮምፕዩተር ፊደላት እያንዳንዳቸው የሚያስፈልጓቸው ኣንድ ስፍራ ብቻ ነው። ፮ኛ. የፊደል ዋና ዓይነቶች ሁለት ናቸው። ኣንደኛው የሁሉም ቀለሞች ስፋት እኩል (Fixed) ሲሆን ሌላው የተለያዩ (Proportional) ስፋቶች ያለው ነው። በቅጥልጥል የዓማርኛ የመጻፊያ መኪና ቁርጥራጮች ስፋታቸው እኩል የሆኑ ቀለሞች መሥራት ኣይቻልም። በእንግሊዝኛና ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ በኣደረጉት ግዕዝ ቀለሞች ሁለቱንም ዓይነቶች መሥራት ይቻላል። ፯ኛ. ስፍራ ስለኣነሰ የግዕዝ ኣኃዞች ቀርተው የእንግሊዝኛው ቍጥሮች ብቻ የዓማርኛው ኣኃዛት ሆነው በዓማርኛው የጽሕፈት መኪና ቀርበዋል። ይህ ለግዕዙ ኣኃዞች መዳከም ኣንዱ ምክንያት ሆኗል። ግዕዝን ዲጂታይዝ ከማድረግ ሌላ ኣኃዞቹን ለማሟላት ዶክተሩ የግዕዝ ኣልቦ ሠርተው በማሰተዋወቅ ቊጥሮቹን ኣሟልተዋል። [828] Archived ሜይ 21, 2013 at the Wayback Machine [829] [830] ስለዚህ በኣማርኛ የጽሕፈት መኪና ድክመትና በግዕዝ ኣልቦ ኣለመኖር የተዳከሙት ኣኃዞቻችንን ኣሁን መጠቀም ይጠበቅብናል። በዶክተሩ ግኝት የተነሳ የግዕዝ ኣኃዞች ሠላሳ ናቸው።

፰ኛ. ለዓማርኛ የጽሕፈት መሣሪያ እንዲስማማ ተብሎ ፊደል መቀነስና መቀንጠስ ተለምዶ ዶክተሩ ሁሉንም ቀለሞች ኮምፕዩተራይዝ ከኣደረጉ በኋላም መቀነስና መቀንጠስ እንደማያስፈልግ ግንዛቤ ማስጨበጥ ማስቸገሩ ቀጥሏል። [831] ለምሳሌ ያህል “ኳ”ን በ“ኩዋ” ማንበብ የሚፈልጉ ሲኖሩ ፊደሉን ኣጥፍተው በ“ካ” እና መቀጠያው ሲጠቀሙ የከረሙ ስለኣላዋጣቸው የቆራረጡትን እንደመተው መልሰው በመቀጠል የኣሌለ መልከ-ጥፉ ኣዳዲስ ቀለሞች በመጨመር እያስለመዱ ናቸው። "ኳ" እራሱን የቻለ መስመር ላይ የሚያርፍ ቀለም ነው። "ካ" ላይ በተቀጠለ መስመር ተሠርቶ በኣዲስ ቅርጽነት የተሠራው የተሳሳተ ፊደል ነው። ለምሳሌ ያህል የ"ጡ"ን መቀጠያ ለ"ኩ" የሰጠ ኣለ። የማተሚያ ቤቶች መደበኛው ፊደል ተቆራርጦ ሲቀርብ ቅጥልጥል ዓማርኛ ያልሆነ ፊደል ይኸን [832] ይመስላል። ለኣንዳንቹም ይኸን ፊደል ከኣልተቀጠሉት የማተሚያ ቤቶች ቀለሞች መለየት ስለተሳናቸው ኣሁንም እየተወናበዱ ነው። ምክንያቱም የዓማርኛ የጽሕፈት መሣሪያ እንደ "ቋ" የኣሉትን ቀለሞች ስለሌሉት ከ"ቀ" እና መስመር በመቀጠል ሲያቀርቡ የነበሩትን እንደ ኣዲስ ፊደል የዩኒኮድ ፊደል መደብ እያቀረቡ ግዕዝ ያልሆኑ ነገሮችን በማሰራጨት ሰውን እያስቸገሩ ናቸው። የ"የ"ን እንዚራን ለማይለዩ ኣንዳኣንድ ምሁራን ሁለት ዓይነት "ቋ"፣ "ኋ"፣ "ኳ" እና "ጓ" ዓይነት ቀለሞች ማቅረብ የሚጎዳ እንጂ የሚጠቅም ኣይደለም። ትክክለኛዎቹ የግዕዝ "ቋ"፣ "ኋ"፣ "ኳ" እና "ጓ" የእየእራሳቸው መልኮች ያሏቸው መስመር ላይ የሚያርፉ ቀለሞች ናቸው። በተጨማሪም ትክክለኛዎቹን ቀለሞች የሚያዩት የዶክተሩን ፊደል ወይም ትክክለኛዎቹን ያሏቸው እንጂ በተሳሳቱ ቀለሞች የሚያዩት የተሳሳቱትን ስለሆነ መወናበዳቸውን ላይረዱ ይችላሉ።

፱ኛ. ከሚያስገርሙት ነገሮች መካከል ኣንዱን ለመጥቀስ ያህል 128 ስፍራዎች ይበቃሉ ብለው ሌሎች ለዩኒኮድ ሲያቀርቡ (ገልባጮች እንጂ) ከዶክተሩ በስተቀር ለዓማርኛ እንኳን እንደማይበቃ የሚያስተውሉና የሚጽፉ ምሁራን መጥፋት ነበር። በኋላም ቢሆን ቅጥልጥሎቹ እንደማያዋጡ ገባቸው እንጂ ሞዴት ፕሮግራም ውስጥ ጭምር የኣሉት የኣናሳ ተጠቃሚዎች የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ቀለሞች በቅጥልጥል እንዲሠሩ ስለፈለጉ የዩኒኮድ መደብ ውስጥ እንዳይገቡ በ፲፱፻፹፱ ዓ.ም. ሌሎች ኣስወግደዋቸው ነበር። [833] ፲ኛ. የኣማርኛ የጽሕፈት መኪና መሣሪያዎች ቁርጥራጮች፣ ኣከታተቦቻቸውና ኣመዳደቦች የተለያዩ ስለሆኑ ኣይናበቡም። ፲፩ኛ. የጽሕፈት መጻፊያ መሣሪያ ዓላማ በዓማርኛም ሆነ እንግሊዝኛ ፊደል ለመክተብ ነበር። ዓማርኛ የሚያስጽፍ የጽሕፈት መሣሪያ ግን ስለሌለ የኣማርኛ የጽሕፈት መኪና ዓላማ ቁርጥራጮችን ለመቀጣጠል ነው። [834] ግዕዝ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ መቀጣጠል ኣስፈላጊ ኣይደለም። ምክንያቱም እያንዳንዱ የግዕዝ ኆኄ እራሱን የቻለ ቀለም እንጂ ቅጥልጥል ፊደል ኣይደለም። ፲፪ኛ. ቁርጥራጮቹ የተመደቡባቸው ስፍራዎች መደበኛ ስለኣልሆኑ ፕሮግራም በተቀየረ ቍጥር ለደራሲው እንኳን ላይነበቡ ይችላሉ።

፲፫ኛ. ጽሑፉ የተጻፈበት ቁርጥራጮች ከሌሉ ጽሑፉ ኣይነበብም። [835] Archived ሜይ 24, 2018 at the Wayback Machine በግዕዝ ዩኒኮድ የተጻፈ ጽሑፍ ኮምፕዩተሩ ወይም የእጅ ስልክ ላይ በኣለው ኣንዱ የዩኒኮድ ፊደል ይነበባል። ጽሑፉን ኣቅልሞ ወደ ሌላ የግዕዝ ፊደል መልክ መቀየር ይቻላል። የታይፕ ቈርጥራጮች ዓማርኛ እንኳን ስለኣልሆኑ ወደ ዩኒኮድ ፊደል ሲቀየሩ ዝብርቅርቅ የላቲን ፊደል ይሆናሉ። ፲፬ኛ. ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ፴፪ የላቲን ምልክቶችንና ሌሎችንም ለግዕዝ ኣውርሰዋል። የኣማርኛ የጽሕፈት መኪና መሣሪያዎች እንኳን ሌሎች የላቲን ምልክቶች መጨመር ሁሉንም ቀለሞች በመቀጣጠል በኣማርኛ እንኳን ኣያሠሩም። ፲፭ኛ. ኣንድን ጽሑፍ ለማረም ወይም ለማሻሻል የተጻፈበትን ኣከታተብ ዘዴ ዕውቅናና የመጻፊያው ኮምፕዩተሩ ላይ መኖርን ይጠይቃል። በነፃውና በሚሸጠው ግዕዝኤዲት ሲጻፍ የፊደል ገበታው እየታየ በመልቀም እንኳን መክተብ ይቻላል። በዩኒኮድ ፊደል የተጻፉትን በነፃው ግዕዝኤዲት ድረገጽ ላይ በመለጠፍ ማረምና ማሻሻል ይቻላል። በታይፕራይተር የተጻፉ ጽሑፎች ነፃው ግዕዝኤዲት ድረገጽ ላይ ሲለጠፉ ዝብርቅርቅ የእንግሊዝኛ ፊደል ሆነው ስለሚታዩ ማረምና ማሻሻል ኣይቻልም። ፲፮ኛ. የግዕዝ "ሀሁሂ" ቀለሞች እንደ እንግሊዝኛው "ABC" ስለሆኑ ትክክለኛና የተወስኑ መልኮች ስለኣሏቸው ፊደል የቈጠረ ሁሉ ያውቃቸዋል። ከኣስቀያሚ ቆብ፣ ሠረዞችና ቀለበቶች ሲሠሩ የነበሩት የኣማርኛ የጽሕፈት መኪና ቀለሞች ቀርተው ትክክለኛውን የማተሚያ ቤት ቀለሞች ወይንም ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ ያደገረጉትን ቀለሞች መቆራረጥ ስለተጀመረ መለየት እያስቸገረ ነው።

፲፯. የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ኣፍቃርያን በጀመሩት ሳይንሳዊ ያልሆነ ግትርነት ኣንድ ስፍራ የዩኒኮድ መደብ ውስጥ ሊቀርብ ይችል የነበረው የግዕዝ ቀለም ኣራት የተለያዩ ስፍራዎች ተበትኗል። ፲፰. የዓማርኛ ሞክሼዎች ይቀነሱ የሚለው ኃሳብ የመጣው ለኣማርኛው የጽሕፈት መሣሪያ ሲባልም ስለነበረ ያልተቀነሱትን ቀለማት ብቻ ማስተማር የቆዩ ጽሑፎችን ማንበብ የማይችል ትውልድ ሊያስከትል ይችላል። የግዕዝ ኣኃዛት የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ውስጥ ስለኣልነበሩ በኣሁኑ ጊዜ የዓማርኛ ኣኃዞችን የማይለዩ ምሁራን ኣሉ። ፲፱. የኣማርኛ የጽሕፈት መኪና ኣጻጻፍ ኣንዳንዱን ቀለም ለመክተብ እስከ ኣራት መርገጫዎችን መጠቀም ስለሚያስከትል ትርፉ እጅ ማሳመም ነው ተብሎ ወደ ፲፱፻፺ ዓ.ም. ግድም ተጽፏል። [836] ፳. የዓማርኛ የጽሕፈት መኪና በኣንድ የእንግሊዝኛ የፊደል ገበታ ምትክ እንዲያገለግል የተሠራው ጊዜው ያለፈበት ቴክኖሎጂና ያልተሟላ ከመሆኑም ሌላ ሊሻሻልም የማይችል ስለሆነ ቀርቷል። ዩኒኮድ የተፈጠረው ብዙ መርገጫዎች ላይ የተበተኑትን ዶክተሩ ኮምፕዩተራዝ ያደረጉት የግዕዝ ቀለሞች የእየራሳቸው ኮዶች እንዲኖራቸው እንጂ ለቅጥልጥሎች ኣይደለም። ቅጥልጥልና ግማሽ ፊደሎችን ዩኒኮድ ኣያውቅም። የእንግሊዝኛ የመጻፊያ መሣሪያ እንግሊዝኛ ቀለሞችን ስለሚያጽፍ የእንግሊዝኛ የኮምፕዩተር ገበታ ሆኗል። የኣማርኛ የጽሕፈት መኪና ዓማርኛ ስለኣልጻፈና ስለማያጽፍ የዓማርኛ የኮምፕዩተር ገበታ መሆን የለበትም። ኣልሆነምም። ይህ የተዘረዘሩትንም ለማክ (Macintosh) ኮምፕዩተሮች የቀረቡትንም ያጠቃልላል። [837] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine [838]

፳፩. የአማርኛ ታይፕራይተር ኮምፕዩተራይዝ ከተደረገ በኋላ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣደረግን ከኣሉት ኣንዳንዶቹ ጥፋታቸውን ማረም ስለተቸገሩ እንዳይዋረዱ ዝም ስለተባሉ ኤክስቴንድድ ኣስኪ የሚችለው ስፍራ ላይ ቁርጥራጮችን ኣቅርበው ተጠቃሚውን ከሃያ ዓመታት በኋላም ማታለል መቀጠላቸው በየቃለምልልሶቹ ቀርበዋል። [839] [840] ትክክለኛ የግዕዝ ፊደል መስለዋቸው በተቀጣጠሉ ፊደላት የተለያዩ ጽሑፎችና መጽሓፍት ሲጽፉ የከረሙ መታለላቸው ሲገባቸው የተበሳጩና እርዱን የኣሉን ኣሉ። [841] [842] በትክክለኛ ፊደላችን የተጻፉትን ወደፊት በተለያዩ ዓይነቶች ማቅረብ ስለሚቻል መጽሓፎችንም በኢንተርኔት መሸጥና ማንበብ ይቻላል፦ ምሳሌ ፒ.ዲ.ኤፍ.(PDF)። ፳፫. በኣማርኛ የጽሕፈት መሣሪያ ዓማርኛ ብሬል መጻፍ ኣስቸጋሪ ነው። [843] ፳፬. ኢንጂነር ተረፈ ራስወርቅ በቅጥልቅል የዓማርኛ ፊደል የሚሠራ የመጀመሪያውን ቴሌክስ መሣሪያ የፈጠሩ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ናቸው። [844] ዓማርኛ ያልሆነውን የቅጥልጥቅል ፊደልና የኢትዮጵያን ፊደላት የማይለዩ ኢንጂነሩ የኣልኣሠሩትን በፊደሉ ኣሠሩ የእሚል ጽሑፍ እዚህ ኣለ። [845] ኣንዳንድ ደራስያን ስለ ሳይንስ ከመጻፋቸው በፊት መረጃዎችን መመልከት ቢጀምሩና ቢያቀርቡ ሳይጠቅም ኣይቀርም። ምክንያቱም ኮምፕዩተር የኢትዮጵያን ፊደላትና ኣኃዞች የተረከበው በኮምፕዩተር ዘመን ከማተሚያ ቤቶች እንጂ ችሎታውን ከኣልነበረው የቴሌክስ መሣሪያና ዘመን ኣልነበረም። አንዲሁም ኮምፕዩተር የኢትዮጵያን ፊደላትና ኣኃዞች የተረከበው በኮምፕዩተር ዘመን ከማተሚያ ቤቶች እንጂ ችሎታውን ከኣልነበረው የኣማርኛ የጽሕፈት መሣሪያና ዘመን ኣልነበረም።

፳፭. የኣማርኛ ታይፕራይተርና ለኮምፕዩተር የተሠራው ፊደሉ እንኳን ግዕዝን ኣማርኛ ቀለሞች ኣላስከተበም። በኣንድ የእንግሊዝኛ መደብ (Character set) ምትክ የተሠራውን የኣማርኛ የጽሕፈት መኪናና የኮምፕዩተር ቅጥልጥል ፊደል በሓሰት ግዕዝ (Ethiopic) ነው በማለት ሰውን የሚያወናብዱ ኣሉ። ኣንድ የእንግሊዝኛ ፊደል ሥፍራ ለኣማርኛ ስለማይበቃ ሳይንስን ኣለመደገፍና እነዚህን ኣለመቃወም ግዕዙን እያበላሸው ነው። ፳፮. ግዕዝን ዲጂታይዝ ወይም ኮምፕዩተራይዝ ማድረግ ሳይንስ እንጂ ልብወለድ ኣይደለም። የኣማርኛውን ታይፕራይተር ፊደል ዲጂታይዝ ኣድርጎ ግዕዝን (Ethiopic) ዲጂታይዝ ኣደረግሁ [846] Archived ሴፕቴምበር 2, 2007 at the Wayback Machine (http://abyssiniagateway.net/fidel/legends/FessehaAtlaw/) የሚለውን በዝምታ ማሳለፍ ቦዘኔ ምሁራን ሳይንስን ወደ ልብወለድ እንዲቀይሩ እያበረታታ ነው። የታይፕራይተር ቁርጥራጮችን ኣቅርቦ ከማተሚያ ቤት ኣዲስ ዘመን ጋዜጣ ፊደላት ዓይነቶች ጋር ተመሳሳይ ናቸው የሚለውን ወሬኛ ወይም "ሶ"ን ፊደል ለመጻፍ የ"ሰ" ግራ እግር ላይ መሰመር ጨምሮ የ"ሰ"ን ቀኝ እግር ኣሳጠርኩ የሚለውን ወይም የግዕዝ ፓተንት ሳይኖርው ኣለኝ የሚለውን የኣለመረጃ የሚያሳልፍ ጋዜጠኛ መተቸት ካልቻልን ፊደላችን ከኩራታችን ምንጭች ኣንዱ መሆኑ ቀርቶ የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ ሊያደርገን ይችላል። ይህ ለኢትዮጵያ የሚጠቅሙ ሥራዎች የሠሩ ኢትዮጵያውያን እንዳይታወቁ የሚሰርዙትን እያበተረታታ ነው። [847] ሶፍትዌር የሚሠሩ ሠራተኞች እንደማንኛውም ሥራ ለጊዜዎቻቸውና ውጤቶቻቸው መከፈል ስለኣለባቸው ዶክተሩ በነፃ ማደል ኣልቻሉም። ገልባጮች ቀን፣ ፀሓፊና መረጃ በሌላቸው ልብ ወለዶች Legends እና Pioneers ተብለውበታል። ፳፯. የአማርኛ የታይፕራይተር ፊደል የግዕዝ ፊደል ኣይደለም። የማተሚያ ቤቶቻችን ፊደልም ኣይደለም። የእውሸት የዓማርኛ (Fake Amharic) ፊደል እንጂ የዓማርኛም ፊደል ኣይደለም። መጽሓፍትም ሲታተሙ የነበሩት በግዕዝ ፊደል በማተሚያ ቤቶች ነበር። ኣሁንም ቢሆን በድሮው የማተሚያዎቹ ዓይነት ወይም ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ በኣደረጉት የዩኒኮድ የዓማርኛ ፊደል ነው። የታይፕራይተርንና በቅርቡም ተቈራርጠው ሲቀጣጠሉ የነበሩትን የማተሚያውን ፊደላት የማይለዩና ሁለቱ ኣንድ የሚመስሏቸው ኣሉ። የግዕዝ ዩኒኮድ ፊደል ከአማርኛው የታይፕራይተር ነገሮች ጋርም ግንኙነት የለውም። [848] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine የአማርኛውን ታይፕራይተር ፊደል ግዕዝ እያሉ ስለጉዳዩ ያልሰሙትን ማታለልና ኣዳዲስ የታይፕራይተር ቁርጥራጮች ፊደላትን በመሥራት ጊዜዎቻቸው እየተባከነባቸው የኣሉ ኣሉ። [849] ኦሮምኛም የእራሱ የግዕዝ ፊደል ስለኣለው ችግር ቢኖር እንኳን መፍትሔ ይፈጠርለታል እንጂ መቀጣጠል ኣስፈላጊ ኣይደለም። ፳፰. የኣማርኛ ታይፕራይተር እንደ ማተሚያ ቤቶች ፊደሎቻችን የግዕዝን ዜሮ ሳያውቁ የኣረብኛውን ኣልቦ በመውረስ እንዘልቅ ነበር።

፳፱. ከአማርኛ የጽሕፈት መኪና ኣጠቃቀምና ኣስተሳሰብ መላቀቅ ተቸግረው የግዕዝን ኣራት ነጥብ (ዓቢይ ነጥብ) በሁለት የላቲን ሁለት ነጥብ እየከተቡ የዓማርኛውን የዩኒኮድ ጽሑፍ እያበላሹ የኣሉት ደራስያን ቍጥር ብዙ ነው። የእዚህ ስሕተት ምንጭ የግዕዝን ኣራት ነጥብ የሌለው የአማርኛ የጽሕፍት መሣሪያ የአማርኛ ቁቤ ኣጠቃቀም ነው። በኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች ኣጠቃቀም ሁለት ባለ ሁለት ነጥቦች ጎን ለጎን ስለተቀመጡ የዓረፍተ ነገሮች መዝጊያ የሆነው የኣራት ነጥብ ምልክት ኣይደሉም። ለምሳሌ ያህል በግዕዝኤዲት ኣራት ነጥብ የሚከተበው በ“ዝቅ” (“Shift”) እና “፫” (“3”) ቊልፎች መርገጫዎች ነው። ፴. ለተለያዩ የፊደል መጠኖች ለእየብቻቸው የሚገጣጠሙ ቀለሞችን መሥራት ኣድካሚና የማያዛልቅ ሥራ ነው። ለኣሥራ ሁለት ፖይንት የተሠራው ፊደል መጠን ሲለወጥ ፊደላቱ ይበላሻሉ። የአማርኛው ታይፕራይተር የእራሱ ፊደል ስለሌለው እንደግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ዓይነት የኣለውን ፊደል እየቆራረጡ በመቀጠል ሰዉን ሲያወንናብዱ ቆይተዋል። ምክንያቱም ገልባጮች ኣስቀያሚ መቀጣጠያዎቻቸውን መቀጣጠል (Ligation) ትተው ይኸን የማተሚያ ቤቱም ትክክለኛ ፊደል ቈራርጠው መቀጠል ስለጀመሩ ነው። የሚያቀርቡትም ጥቂት ዓይነቶች የፊደል መጠኖች ብቻ በመሆኑ ፊደላቱን ለማሳደግ ወይም ለማሳነስ ሲፈለግ ይዛነፋሉ። (ምሳሌ- ፊደል ሶፍትዌር) ፴፩. ለመቀጠል ሲባል ኣስቀጣዮች በወጉ ስለማይሠ'ሩ ስፍራዎቻቸውን የለቀቁ ቀለሞች ናቸው። በእዚህ የተነሳ የታይፕ ፊደላት የተዛነፉና ክፍተቶች የበዙባቸው ናቸው። ፴፪. እ.ኤ.ኣ. በ1987 በአማርኛ የእጅ ጽሑፍ ፊደል በኮምፕዩተር የተጻፉ ገጾች ምሳሌ እዚህ ሰምና ወርቅ መጽሔት የገጾቹ ሥዕሎች አሉ።

፴፫. የአማርኛን ታይፕራይተር የፈጠራ ቀለሞች Ethiopic ወይም ግዕዝ እያሉ የሚያወናብዱና የሚተባበሩዋቸው ጋዜጠኞች ኣሉ። ዶክተሩን የታይፕራይተር ኣፍቃርያን ኣሸንፈው ቢሆን ኖሮ ግዕዝን ኣንድ የፊደል ገበታ ላይ በኣሉት ሥፍራዎች መጠቀም ስለማይቻል ትርፉ ውርደት ይሆን ነበር። ፴፬. የአማርኛን ታይፕራይተር የፈጠራ ቀለሞች እንደ ዓማርኛው የኦሮሞውንም የግዕዝ ፊደል ስለኣልጻፉ ኣንዳንድ ኦሮሞዎች በላቲን ፊደል እንዲጠቀሙ ኣንዱ ምክንያት ሆኗል። ፴፭. በፊደል ቆራጮች ለዩኒኮድ እዚህ [850] የቀረበው ሥራ ላይ ያልዋለው የማተሚያ ቤቱ ፊደል ኣቀራረብ ለይስሙላ ብቻ ነበር። ምክንያቱም ስምንት በኣሥራ ስድስት ማለትም 128 ሥፍራዎች በቂ ኣይደሉም። የኣማርኛ ታይፕራይተር ወደ ኮምፕዩተር የገባው በኣስቀያሚ ቀጫጭን ቁርጥራጮች እንጂ በእነዚህ የተቆራረጡ ትክክለኛ የግዕዝ ቀለሞች ቍርጥራጮች ኣልነበረም። የትክክለኛ የግዕዝ ቀለሞችን ቍርጥራጮችንም ግዕዝ ነው ማለትም ቅጥፈት እንጂ ሳይንስ ኣይደለም። በኣስቀያሚ ቀጫጭን ቁርጥራጮች አማርኛ የጽሕፈት መኪና ፊደሎች ምን አንደሚመስሉ አዚህ [851] የኣለውን የኢትዮጵያ መዝሙር ገጽ ማየት ይቻላል። ሌላ ምሳሌ አዚህ ጎን የኣለው የ፲፱፻፹፪ ዓ. ም. የኣቶ ኣበበ ሙሉነህ ደብዳቤ ሥዕል ነው። ፴፮. ፊደል ቀናሾችና ቀንጣሾች ኣስቀያሚዎቹን የታይፕራይተር ፊደል ትተው የዶክተሩን ዓይነት ትክክለኛ ቀለሞች መቀንጠስ ጀምረው ሁሉንም የግዕዝ ፊደላትና መጻፊያ ስለሌላቸው ያልቀነጠሷቸውን ከሌላ በመውሰድ ኣንባቢውን በማታለል ቀጥለውበታል። ለምሳሌ ያህል የኣቶ ዘውዴ ረታ “የኤርትራ ጉዳይ” መጽሓፍ ርዕስ የውጭውና የውስጡ “ጉ” ቀለም መልኮች የተለያዩ ናቸው። ኣንዳንዶቹም ሲቀጥሉ የነበሩትን “ኳ”ን የመሰለ “ካ” እና መስመር ወይም “ቋ”ን የመሰለ “ቀ” እና መስመር መልሶ በቅርቡ በመቀጠል የዩኒኮድ ሥፍራ ላይ ጭምር በማቅረብ የተሳሳቱ ቀለሞችን በማስተዋወቅ ፊደሉን የማያስተውለውን ምሁር የሌለ ፊደልን ግዕዝ (Ethiopic) ነው እያሉት በማወናበዱ ገፍተውበታል። እንኳን 128 ቀርቶ 256 የኣንድ የእንግሊዝኛ ፊደል ተራዝሞም (Extended ASCII) ስፍራዎቹ ስለማይበቁ በቅጥልጥል የግዕዝ ፊደላችንን መጻፍ ስለማይቻል ዶክተር ኣበራ ሞላ ባይኖሩ ኖሮ ኣንዳንድ ውሸታሞች የግዕዝ ፊደልን በተለመደው ሓሰታቸውና ዩኒኮድንም በመጠቀም ገድለውት ነበር።

፴፯. የኣማርኛ የታይፕራይተር ፊደል የተሠራውና በኮምፕዩተር የተሠራለትም ዓይነት በኣንድ የእንግሊዝኛ ASCII ፊደል ምትክ የቀረቡ የእውሸት ነገሮች ነው። ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት ለመጀመሪያ ጊዜ የግዕዝ ፊደላቱን በስምንት የእንግሊዝኛ ASCII ፊደላት ምትክ በመጠቀምና በመበተን ነው። ፴፰. የኣማርኛ ታይፕራይተር ትክክለኛዎቹን ፊደላት ስለሌሏቸው የሚቀጣጠለው ፊደል ትክክለኛ ላይሆን ይችል ነበር። ለምሳሌ ያህል የግዕዝ “ጯ” ፊደል ኣንድ ወጥ የግዕዝ ቤቱ ሦስተኛው እግር ላይ የተቀረጸ መስመር ያለው ሲሆን ፊደሉን በሚገባ የማያስተውሉ፣ ታይፕራይተር ተጠቃሚዎችና ተማሪዎቻቸው ፊደሉ የሚሠራው “ጫ” ስር መስመር በመጨመር የሚመስሏቸው ኣሉ። ፴፱. ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ እንደኣደረጉ የማያውቁ ዓዋቂዎችም ኣሉ። [852] ፵. ኣንዳንዶቹም የታይፕራይተር ቅርጾች ወይም ሌሎችንም የሚከተቡት ከሁለት በላይ መርገጫዎችን በመጠቀም ነው። [853]

፵፩. ኣንዳንድ ሰዎች ዶክተሩ የሠሯቸውን የተሟላውን የዓማርኛ የታይፕራይተር ፊደል መልክ ስላላሳዩ የሚገርማቸው ኣሉ። ዶክተሩ ፊደሉን የሠሩት ፊደል የሌላቸው ሰዎች ስለ ኤድስ የጻፉትን ዓይነት ጽሑፍ በነፃ እንዲያነቡበት የለቀቁት ሲሆን GeezEdit Amharic P የሚል ስም የሰጡትን ያልተሟላ ወደ AmharicQ በመቀየር የሚያድሉ ሌባዎችም ስለበዙ ነው። [854] [855]

ጥሬ ሥጋ ለማስተካከል

ዶ/ር ኣበራ ሞላ ዕድል በኣገኙ ቍጥር ችሎታቸውን ለሌሎች ከማስተማርና ስለሚያውቁት ከማስረዳት ኣይቆጠቡም። ለምሳሌ ያህል በ፳፻፭ ዓ.ም. ከኣንድ የዋሽንግተን ዲ.ሲ. የዓማርኛ ሬድዮ ጣቢያ ጋር ስለ ጥሬ ሥጋ (Raw meat) ገለጻ ኣድርገው ነበር። ኢትዮጵያውያን ጥሬ ሥጋ ከሚበሉ ሕዝቦች መካከል ስለሆኑ [856] [857] ኣትብሉ ማለት ብቻ ትክክል ስለኣልሆነ የሚያዋጣው በምርምር የተደገፉ መረጃዎችን ማቅረብ ነው። [858] [859] [860] [861] በኣሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚደረገው ከብት በየቦታው እየታረደ ይበላ ስለነበረ ዩናይትድ እስቴትስ (ኣሜሪካ) ውስጥ እንዲቀር ተወስኖ በ፲፰፻፺፱ ዓ.ም. ፌዴራል ድንጋጌ የኣልተመረመረና ንጹህ ያልሆነ ሥጋ ለሕዝብ ማቅረብ ክልክል ነው። [862] ሕጉን ኣለማወቅ መከላከያ ኣይደለም። ሥጋው የተመረመረ ለመሆኑ ማሕተሙን ማየት ያስፈልጋል። እንዲህም ሆኖ ኣንድ ሰው የእራሱን እንሰሳ ኣሳድጎና ኣርዶ ሳያስመረምር ቤተሰቡን ብቻ የማብላት መብት ኣለው።

ጥሬ ሥጋ ጀርሞች ኣሉት። ስለዚህ የሚከተሉትንም ማወቅ ጠቃሚ ነው። [863] ፩. ኣንድ እንሰሳ ሲታረድና ቆዳው ሲገፈፍ ጀርሞች በተለያዩ ሁኔታዎች ሥጋው ውጭ ላይ ስለሚቀሩ ያንን ማስወገድ ኣይቻልም። ቆዳ ሲገፈፍ ቢላው እንዲጸዳ ሙቅ ውሃ ውስጥ እየተነከረ ነው። ፪. እንደ ባክቴሪያ የኣሉ ጀርሞች በእየ20 ደቂቃዎች ሁለት በመሆን ይራባሉ። ይኸን እርባታ ቅዝቃዜ ያዘገየዋል። ስለዚህ እንሰሳው እንደታረደ ሥጋው ጥቅም ላይ ከኣልዋለ ሁልጊዜ መቀዝቀዝ ወይም መፈረጅ (ፍሪጅ ውስጥ መቀመጥ) ኣለበት። ለብዙ ጊዜ መቀመጥ ከኣለበት ሥጋው ከውሃ በረዶ ቅዝቃዜ በኣነሰ ወይም መፈረዝ (ፍሪዘር መግባት) ኣለበት። ፫. ኣንድ እንሰሳ ከመታረዱ በፊትና ከታረደ በኋላ በእንስሳት ሓኪም መታየት ኣለበት። ሓኪም ከሌለ ረዳት ሓኪሞች ወይም በሥጋ ምርመራ የሰለጠኑ ኣይተው ኣጠራጣሪውን ለእንስሳት ሓኪም የሚያቆዩበት መዘጋጀት ኣለበት። ምክንያቱም ሓኪሞች ብቻ የሚያውቋቸው ከእንስሳት ወደ ሰዎች የሚተላለፉ ብዙ በሽታዎች ስለኣሉ ነው። [864] [865] [866] [867] [868] ፬. ሥጋ ውስጡ ንጹህ ነው።

፭. እንጨት ልሙጥ ስለኣልሆነ ለጀርሞች መደበቂያ ስለሚያገለግል ለብዙ ሰዎች የሚቀርብ ሥጋ ሲዘጋጅ መክተፊያ፣ የቢላው እጀታና ማቅረቢያው እንጨት ባይሆን ይመረጣል። ፮. የኮሶ በሽታ ሰውን የሚይዘው ያልተመረመረ ጥሬ ሥጋ በመብላት ነው። የኮሶ በሽታ ያለበት ሰው በየሜዳው ሰገራ ሲወጣ ከብቶች የኮሶውን እንቁላል ከሳር ጋር በመብላት ይበከላሉ። [869] የኮሶ ትላምነት የኋላ-ቀር ሕዝብ የሰው በሽታ እንጂ የከብት በሽታ ኣይደለም። ፯. ሥጋ ጀርሞች ስለኣሉት ሲዘጋጅ ሳይበስሉ ከእሚበሉ እንደሰላጣ የኣሉ ምግቦች ጋር መነ'ካካት የለበትም። ፍሪጅ ውስጥም ሥጋን ከታች ማስቀመጥ ጠቃሚ ነው። ፰. ሥጋ የኣለው የበሰለ ለብዙ ሰዎች የሚቀርብ ምግብ ጀርሞች እንዳያድጉበት እንደሞቀ እንዲቆይ ከኣልተደረገ በሁለት ሰዓታት ውስጥ ከኣልተበላ ወደ ማቀዝቀዣ ማግባት ጠቃሚ ነው። ማቀዝቀዣ ያልሞቀ ምግብ ማቀዝቀዣ ነው።

፱. የበሰሉ ሥጋ-ነክ ምግቦችን ማቀዝቀዣ (ፍሪጅ) ውስጥም በንጽሕና ማስቀመጥ ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም እንደ ሊስቴሪያ (Listeria) የኣሉ ባክቴሪያዎች ማቀዝቀዣም ውስጥ ስለሚያድጉ ነው። [870] ፲. ሥጋን ማብሰል የኮሶውን እንቁላል ይገድላል። የኮሶ ትል (Taenia saginata) እንቁላል ያለበትን ጥሬ የከብት ሥጋ ለሁለት ሳምንታት ፍሪዝ ማድረግም ይገድላቸዋል። ፲፩. ኣልፎ ኣልፎ ሥጋ እየበሉ ስለታመሙ ሰዎች ይሰማል።[871] [872] [873] [874] ፲፪. ኣንድ ሰው በኮሶ በሽታ ከተያዘ በኣንድ ጊዜ የሚኖረው ኣንድ የኮሶ ትል ብቻ ነው።

፲፫. ጥሬ ሥጋ ውስጥ የኣሉ ጀርሞች ኣደገኝነት ሕጻናትና በቂ መድኅን የሌላቸው እንደኤድስ በሽተኞችና ኣዛውንት ላይ የበረቱ ናቸው። ፲፬. ለትላልቅ ድግሶች በስለው ፍሪዝ የተደረጉ ሥጋ-ነክ ምግቦችን ለማብሰል ከበረዶነታቸው እንዲሟሙ እንደ እቃው ትልቅነት እስከ ሦስት ዕለታት (፸፪ ሰዓታት) ሊያስፈልጉ ይችላሉ። ፲፭. ጥሬ ሥጋን የተመለከተው ሕግ ሌሎች እንስሳትንም ይመለከታል። ፲፮. ኣንድ ከብት ለምግብነት እንዲያልፍ ወይም እንዲወድቅ የመወስን ሥልጣን የኣላቸው የእንስሳት ሓኪሞች ብቻ ናቸው።

፲፯. የሚሰራጭ ካንሰር የኣለበት እንሰሳ ለምግብነት ኣያልፍም። የኣልተሰራጨ ካንሰር በማየት የሚያውቁና የሚጠረጥሩ ሓኪሞች ናቸው። ፲፰. ጥሬ የኣሳማ ሥጋ ከመብላት ሰው የሚኖረው የኮሶ በሽታ ኣደገኝነት የከፋ ነው። [875] [876] ፲፱. ጥሬ ሥጋ መብላትና ጥሬ ኣሳ (ሱሺ) መብላት ኣንድ ኣይደለም። ፳. ኣንድ ጀርም ሰውና የተለያዩ እንስሳት ውስጥ የተለያዩ በሽታዎች ሊያመጣ ይችላል። ለምሳሌ ያህል ኣባሰንጋ (Anthrax) ኣእዋፍን ኣይተናኰልም።

፳፩. ኮሮናቫይረስ (Coronavirus) [877] ከጥሬ ሥጋ እንደሚተላለፍ ወይም እንደማይተላለፍ መረጃው ስለሌለ ሥጋን በጥንቃቄ መያዝና ኣብስሎ መብላት ይመከራል። [878] [879] [880] [881] [882] በነገራችን ላይ ኮሮናቫይረስ እንጂ ኮሮና ወይም ኮሮና ቫይረስ የሚባል ቫይረስ የለም። በእንግሊዝኛም ስሙ coronavirus ነው። [883]

ግዕዝኤዲት ለኣይፎን 4 እና በላይ እና ኣይፓድ ለማስተካከል

የእጅ ወይም ተንቀሳቃሽ ስልክ ለእንግሊዝኛ ኣጠቃቀም ከተሠራ ፵ ዓመታት ቢያልፉም [884] [885] ለዓማርኛ ሥራ ላይ ማዋል ይቻላል። [886] Archived ጁላይ 31, 2021 at the Wayback Machine ግዕዝኤዲትኣፕል ኣይፎን 6 (iPhone 6 GeezEdit app) [887] ከኣፕሮባቲክስ (Approbatics) ቀርቦላችኋል። [888] [889] [890] [891] በኣፕል ኣይፓድም (iPad) ያስከትባል። ከኣይፎን 4ኤስ (iPhone 4s) ወዲህ ለተሠሩትም ኣዲሱን የኣይኦኤስ 8 (iOS 8) ሥርዓት በማስገባት ማሻሻል (Upgrade) በዓማርኛው መጠቀም ያስችላል። GeezEdit (Amharic Typing) ከኣፕ ሱቅ (App Store) ወይም ኣይቲዩንስ (iTunes) ወደ ኣይፎን 6 የእጅ ስልካችን ስናስገባ "Allow Full Access" የሚለው ከፊደል ገበታዎች ኃይል ጋር ያሉትን ልዩ ጥቅሞች ለመጠቀም የሚያስፈልግ ስለሆነ ለጊዜው መዝለል ይቻላል። እንዲህም ሆኖ ኣፕል እንጂ የኢትዮጵያ ኮምፕዩተሮችና ሶፍትዌር የገዥዎችን ክሬዲት ካርድና ኣድራሻ ኣያውቅም። ይህ ለኣዲሱ የኣፕል የእጅ ስልክ የተለያዩ ቍሳቍሶች ውስጥ እንዲሠራ የቀረበው ቁስ ኣከታተብ የባለቤትነት መብቱ ለዶክተሩ ሊሰጥ እየተጠበቀ ባለው ኣብሻ ዘዴ ለዊዶውስና ማክ ኮምፕሩዩተሮች መክተቢያ በነፃ ከተሰጠውና ከሚሸጠው ግዕዝኤዲት ጋር ኣንድ ዓይነት ነው። ለተወስነ ጊዜ ዋጋው ዶላር ፩.፱፱ (1.99) ነው። ቁሱ ተወዳጁን የግዕዝኤዲት ዩኒኮድ (GeezEdit Unicode) የዓማርኛውን ፊደል ይጨምራል። የግዕዝ ፊደል ያላቸው የኣንድሮይድ ስልኮችም ከኣይፎን የተላከላቸውን ማስነበብ ይችላሉ። የፊደል ገበታው ለጊዜው ለዓማርኛ ብቻ ቢሆንም ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች ማለትም [892][893][894] እና [895] ከኣንድ ገበታ እንዲያስከትብ የተሠራ ነው። እየተሻሻለ ስለሆነም የሌሎች ቋንቋዎቻችን መክተቢያዎች እንደኣስፈላጊነታቸው ወደፊት ይከፈታሉ።

ከኣፕል ሱቅ GeezEdit App ቁስ ከተገዛ በኋላ ኣዶው ስር Amharic Typing የሚል ስሙ ይታያል። ከእዚያ Settings፣ General፣ Keyboard፣ Keyboards በኩል Amharic Typing ገበታውን መጫንና ወደ Settings ከእዚያ General ተመልሶ በProfile በኩል GeezEdit Font ፊደሉን በInstall ማስገባት ያስፈልጋል። GeezEdit ሲከፈት የሚታየው እንግሊዝኛ ስለሆነ ለዓማርኛው የዓለም ካርታ ያለበትን ኣዶ መጫን ነው። ተጭኖ መቆየትም “Amharic Typing” “ኣማርኛ” የሚለው የፊደል ገበታ እንዲመረጥ ያቀርባል። ለኣጻጻፉ “Help” የሚለውን በኣማርኛ ወይም እንግሊዝኛ/English ማንበብ ይጠቅማል። ግዕዝኤዲት ኣንዴ ከተጫነ ጽሑፍ የሚያስፈልጉበት ቦታዎች ሁሉ ከእንግሊዝኛው ገበታ ስር በዓማርኛ ለመጻፍ ዝግጁ ስለሆነ የሚያስፈልገው ገበታውን መክፈት ብቻ ነው። የግዕዝኤዲት ገጽ ላይ ከትቦና ኮፒ ኣድርጎ ሌሎች ስፍራዎች መለጠፍ ሌላ ዘዴ ነው። በግዕዝኤዲት የተጻፈን የዓማርኛ ጽሑፍ በፋይል መልክ ለማስቀመጥ ወደ “ኖትስ” (“Notes”) መገልበጥ ወይንም ኖትስ ውስጥ መክተብ ጠቃሚ ናቸው።

ቀደም ብሎም ለእጅ ስልክ ዓማርኛውን ለመጀመሪያ ጊዜ ማቅረባቸው ቢታወስም ዓማርኛ ከዓለም ቋንቋዎች መደብ እንዲገባ ኣፕል (Apple) ገበታችንን እንድናስገባ ስለወሰነና የመጀመሪያው ኩባንያ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል። የግዕዝኤዲት ቁስ የተለያዩ የኣይፎን 6 የእጅ ስልክ ፕሮግራሞች ውስጥ እንድንሠራ ኣዲስ ችሎታ ኣስገኝቷል። ቴክስት (Text)፣ ኢ-ሜይል (Email)፣ ትዊተር (Tweeter) እና በመሳሰሉት ተደሰቱ። በኣሁኑ ጊዜ ኣንዳንድ ድረገጾችና ጽሑፎች ግን ላይነበቡ የሚችሉት በሌሎች ምክንያቶች ሲሆን ችግር የሌላቸው ድረገጾች ምሳሌ እዚህ [896] ኣለ። ለምሳሌ ያህል እንደነፃው የግዕዝኤዲት ገጻችን [897] Archived ዲሴምበር 4, 2020 at the Wayback Machine የመሳሰሉት በኮምፕዩተር የሚነበቡት በኣዶቢ ፍላሽ ስለሆነና ኣፕል ፍላሽን ስለማያስገባ ድረገጹ ባይነበብ ችግሩ የግዕዝኤዲት ኣይደለም። ወጪና ጊዜ ያስጨምራል እንጂ ለኣንዳንዳቹም ተግዳሮት መፍቻ ዘዴዎች ኣሉ። ኣንዳንድ ፕሮግራሞችም በእንግሊዝኛ እንጂ በዩኒኮድ ፊደላት የመጠቀም ኃይል ገና የላቸውም። ምሳሌ ለመጥቀስ ያህል ፌስቡክን በድረገጽነት ማንበብ የዓማርኛውን ቀለሞች በኣለማቅረብ ሳጥን ስለሚያደርጋቸው በፌስቡክ ቁስ (Facebook App) መጠቀም ያስፈልጋል። ኣይኦኤስ ፰.፫ እነዚህን ችግሮች ስለኣስወገደ ግዕዝ ብዙ ፕሮግራሞች ውስጥ ይሠራል። ከጉግል፣ ቢንግ፣ ያሁ፣ ሳፋሪ የመሳሰሉት ሌላ ይኸን የዓማርኛ ውክፔድያ ገጽ ያስነብባል፣ ያስከትባልም። ለተጨማሪ መረጃ የግዕዝኤዲት ፌስብክ ገጽ መከታተል ይጠቅማል። የፌስቡክ ኣጓዳኙም እዚህ [898] ኣለ።

በኣይፓድና ኣይፎን ግዕዝኤዲትን ለመጠቀም ለጊዜው እንግሊዝኛውን በቋንቋነት በLanguage & Region በኩል ትቶ ኣማርኛን ኣንደኛ ማድረግ ይሻላል። ኣንዳንድ ፕሮግራሞች የተሠሩት ለእንግሊዝኛው ብቻ ስለሆነ በሚገባ ከኣልሠሩ ወደ እንግሊኛ መመለስ ያስፈልጋል። ኣይፎንና ኣይፓድ ለኣለው ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ፊደል ጨምሮ የሚከፈለው $1.99 ለሦስቱም ነው። የኮምፕዩተሩና የስልኩ ግዕዝኤዲት ኣከታተብና ፋይሎች ኣንድ ከመሆናቸው ሌላ ይናበባሉ።

ከእዚህ በፊት መጻፊያ ጠፍቶ በእንግሊዝኛ ፊደል ዓማርኛውን ፓልቶክ (Paltalk) በመሳሰሉ ድረገጾች ውስጥ ሲጽፉ የነበሩትን ነፃው የግዕዝኤዲት ድረገጽ መገላገሉ ይታወሳል። ከእዚህ በፊት መጻፊያ ጠፍቶ በእንግሊዝኛ ፊደል ዓማርኛውን ሲጽፉ ወይም ለጄልብሬክ ሲከፍሉ የነበሩትን ግዕዝኤዲት ገላግሏል። ከእንግዲህ ወዲያ ማንኛውንም የግዕዝ ቀለም በሦስት መርገጫዎች መክተብና ቴክኖሎጂን በሚ'ገባና ሳይንሳዊ ባልሆነ ዘዴ መጠቀም ኣስፈላጊ ኣይደለም። ይኸን በፔንዲንግ ፓተንት የተጠበቀ ትክክለኛ ቴክኖሎጂ ላልሰሙት እንድታሰሙና እንድታሳዩ እናበረታታለን። ስለ ቁሱ እዚህ የተጻፈው ጥቂት ሰዎች ግዕዝኤዲትን ከገዙ በኋላ ገበታውንና ፊደሉን ሳያስገቡ መጻፍ እየሞከሩ ስለተቸገሩም ነው። [899] [900] “Amharic Typing” የሚለው ባለ ሰንደቅ ዓላማ ካርታችን ያለበት ኣዶ ከታየ በኋላ ያንን መንካት እንደተራ ቁስ ግዕዝኤዲትን ኣይከፍትም። በቁሱ ለመጠቀም የፊደል ገበታውና ፊደሉ በሴቲንግስ (Settings) በኩል መግባት ኣለባቸው። [901] የእንግሊዝኛው የፊደል ገበታ ከታየ በኋላ የዓለም ካርታው ያለበትን ኣዶ መንካት ወይም ተጭኖ መቆየት የዓማርኛውን የፊደል ገበታ ያቀርባል። በቅርቡ ወደ ኣይኦኤስ 10 ሲሻሻል የቁሱን ክፍል 1.3 በማድረግ ስሙም GeezEdit Amharic ተብሏል። ማሻሺያውም (Upgrade) ነፃ ነው።

የእጅ ስልክ ኣከታተብ ለማስተካከል

የእንግሊዝኛው የኮምፕዩተር ኣከታተብ የእጅ ስልክ ኣጠቃቀምም ሆኗል። ግዕዝም ለኮምፕዩተር ሲጠቀምበት የነበረው ኣከታተብ ዓይነት ወደ እጅ ስልክ በዶ/ር ኣበራ ግኝት ገብቷል። [902] የተለመደው የእንግሊዝኛና የግዕዙ ገበታ መርገጫዎች እየታዩ ለሁለቱም ፊደላት እንዲያገለግሉ የፈጠሩት ጥቅም ቀጥሏል። [903] ኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ የሚጠቀሙት የግዕዝ ዩኒኮዱን ፊደል ስለሆነ ውበቱን እንደጠበቀ ሁሉም መሣሪያዎች ይናበቡበታል። በእጅ ስልክ በኣንድ ጣት ከመክተብ ስልኩን ወደጎን ኣዙሮ በኣውራ ጣቶች መክተብ ያፈጥናል። በእዚህ የተነሳ ላቲን ለቀለሞቹ መክተቢያ የማይጠቀምበትን ከግዕዝ መጠየቅ ለእስማርት (ጮሌ) ስልኮችም ኣያስፈልግም። የግዕዝ ኣከታተብ ፈጣሪ ፓተንት (የግኝት ባለቤት) ከዶ/ር ኣበራ ሞላ ጋር ቃለ ምልልስ (ኢቢኤስ / EBS Tube) ቪድዮ እዚህ [904] Archived ሴፕቴምበር 23, 2015 at the Wayback Machine ኣለ። ለኮምፕዩተር የቀረቡት የላቲን ምልክቶችም ለግዕዝ ፊደል እንዲጠቅሙ በእጅ ስልክም ሥራ ላይ ውለዋል።

የእጅ ስልኩ ገበታና ፊደል ከተበተነ በኋላ መክተብ ሲያስፈልግ የመጻፊያው ስፍራ ሲነካ የመክተቢያ ገበታ (GeezEdit Amharic) ይቀርባል። በዓማርኛ ለመክተብ የሚያስፈልገው የዓለም ካርታ ያለበትን በመንካት ገበታውን ወደ ዓማርኛ መለወጥ ነው። ለላቲን ኮምፕዩተር ኣከታተብ የተፈጠረው "QWERTY" ገበታ ለላቲን የእጅ ስልክ እንደሆነው ሁሉ የግዕዙም "ቀወኸረተየ" የኮምፕዩተር መደበኛ ገበታ የእጅ ስልክም የግዕዝ ገበታ ሆኗል። [905] ለስልክ የተገዛው ለኣይፓድም ጭምር ነው። ጽሑፍን ለማስቀመጥ "Notes" ውስጥ መጻፍ ያስፈጋል። ዊንዶውስና ኣፕል የሚጠቀሙት በግዕዝኤዲት ዩኒኮድ (GeezEdit Unicode) ፊደል ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለኮምፕዩተር ለዓመታት ሲቀርቡ የነበሩት ዓይነት የማያዛልቁ ኣከታተቦች ለእጅ ስልኮች መቅረብ ስለጀመሩ ሕዝቡ በኣዲስ ዙር መታለል እንዳይቀጥል መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ለእዚህም የሚከተሉትን እንድንዘረዝር ተገድደናል። ፩. ግዕዝ ወደ ኮምፕዩተር ሲገባ እያንዳንዱ የግዕዝ ቀለም የተከተበው በሁለት መርገጫዎች ነበር። ይህ ተሻሽሎ በኣንድና በሁለት መርገጫዎች እንዲከተብ ሆኗል። እንደእንግሊዝኛው የኮምፕዩተሩ ኣጠቃቀም ለእጅ ስልኩም ቀርቧል። ኣጠቃቀሞቹም ይቀጥላሉ። ፪. ይህ በሳይንስ የተደገፈ ኣጠቃቀም ይቀጥላል እንጂ ጥልቅ እየተባለ ለእጅ ስልክ ኣዲስ ኣጠቃቀም ኣይሠ'ራም ወይም ችግር ኣለበት ተብሎ ወደቀረው ኋላቀር ኣከታተብ መመለስ ኣስፈላጊ ኣይደለም። ፫. የኣማርኛ ታይፕ መቀጣጠያው ኣሠራር የትክክለኛ ኣማርኛ ፊደል መጻፊያ ኣልነበረም። የታይፕራይተሩ ኣጠቃቀም ሁለት ነጥብ ምልክት ለባዶ ስፍራነትና ሁለቱ፣ ሁለት ነጥቦችን በኣራት ነጥብ ምልክት ምትክነት መጠቀም ከመሣሪያው ኣጠቃቀም ችግሮች ጋር በተያያዙ የቁጠባ ኣሠራሮች የመጡ ነበሩ። ወረቀት ላይ ብቻ ሰፍረው የምናያቸው የጽሕፈት መሣሪያ ኣጠቃቀም ውጤቶች ከኮምዩተሩና የእጅ ስልክ ኣጠቃቀሞች ጋር ኣንድ ዓይነት ኣይደሉም። ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት የግዕዝ ፊደል ኣንዱን ምልክት ለሁለቱም ኣይጠቀምም፤ ኣልተጠቀመምም። ፬. የላቲንን የኮለን (Colon) ሁለት ነጥብ ምልክት ዶክተሩ እንደሌሎቹ ለግዕዝ ኣጠቃቀም ቢያወርሱም ኣጠቃቀሞቻቸውን ማወቅ የተጠቃሚው ኃላፊነት ነው። ኮለን የግዕዝ ሁለት ነጥብ የባዶ ስፍራ ምልክት እንዳልሆነው ሁሉ የግዕዝ ሁለት ነጥብ ምልክትም ኮለን ኣይደለም። ሁለት፣ ሁለት ነጥቦችም ሆኑ ሁለት ኮለኖች የግዕዝ ኣራት ነጥብ ምልክት ኣይደሉም። የእዚህ ገጽ ኣንዱ ዓላማ ኣዳዲስ ጥፋቶች በቴክኖሎጂ እየተደገፉ እንዳይስፋፉ ነው።

፭. የዓማርኛን ጽሑፍ ለማስቀመጥ ኖትስ (Notes) ቁስ ውስጥ መጻፍ ያስፈልጋል። ፮. የግዕዝ ፊደል የእጅ ስልክ ትክክለኛ ሳይንሳዊ ቴክኖሎጂ ኣጠቃቀሞች ዘዴዎቹን ለፈጠሩት ለዶ/ር ኣበራ ሞላ ቍጥራቸው 9000957፣ 9733724፣ 10067574 እና 10133362 በሆኑ የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንቶች ተሰጥተዋል። ፯. ኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች የሚጠቀሙት ግዕዝኤዲት የኢትዮጵያ ኮምፕዩተሮችና ሶፍትዌር ፕሮግራሞች ኣንድ ዓይነት በሆነው የግዕዝ ፊደሉ ነው። ስለዚህ የቴክኖሎጅው ተጠቃሚዎች የተላኩላቸውን ኢሜይል የመሳሰሉ ጽሑፎች በኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች የሚመለከቱት በግዕዝኤዲት ፊደል ነው። ፊደሉን ለሌላቸው ግን መሣሪያዎቹ ላይ በኣሉ ፊደላት ይቀርባሉ። ፰. ኣንዳንድ የግዕዝኤዲት ተጠቃሚዎች ፊደሉ በኣስቀያሚና የተሳሳተ የግዕዝ ፊደል ተቀየረብን የኣሉ ኣሉ። ይህ በቅርቡ ኣፕል መጠቀም በጀመረው ፊደሉ ኣጠቃቀም የመጣ ችግር ነው።

የዓማርኛ ስሕተቶች ለማስተካከል

በእዚህ ርዕስ (Errors) ዶክተሩ ከዓመታት በፊት ያቀረቡትን ብዙ ኣንባቢዎች ስለኣላዩት ኣልታረሙም። [906] Archived ጁን 14, 2006 at the Wayback Machine [907] እዚህ ውክፔዲያ ገጽ ላይ የቀረቡት ውጤት ማምጣት ስለጀመሩ ተሻሽለው ቀርበዋል። ወደፊት ኮምፕዩተሩ በግዕዝ ፊደል የቀረቡትን ያነባ'ል፣ ያሰማናል፣ ያርማል፣ ይተረጕማል፣ ወዘተርፈ። ስለዚህ ዶክተሩ ኣርቆ በማሰብ ስሕተቶችና ግድፈቶች ወደ ኮምፕዩተር ሳይገቡ እንዲታረሙ ከመጻፍ ኣልተቆጠቡም።

፩. እንደ ኤውሮጳ ኣቆጣጠር ማጠር ያለበት በ“እ.ኤ.ኣ.” እንጂ “እ.ኤ.ኣ” ማድረግ ከሚገባው በታች ማሳጠር ነው። ኣንድ ሰው በስሕተት የተጠቀመበትን ኣሠራር ሌሎቻችን በሚገባ ሳናስተውል መከተል የለብንም። “ኣ” ጎን ነጥብ ከኣሌለ “ኣ” ብቻውን እንዳለ ቃል መቆጠሩ ስለሆነና ኣጠቃቀሙም ትክክል ስለኣልሆነ ቋንቋ ሲበላሽ ዝም ብሎ መመልከት ተገቢ ነው? ፪. “ዓመተ ምሕረት” ማጠር ያለበት በ“ዓ.ም.” እንጂ “ዓ/ም” ያሳስታል። የእዝባር ጥቅም እንደ “ወይዘሮ” የሚጻፉትን ቃላት በ“ወ/ሮ" ለማሳጠር እንጂ ሁለት ቃላትን ለማሳጠር ኣይመስልም። ፫. የ“ሊቅ” ብዙ “ሊቆች” ወይም “ሊቃውንት” እንጂ “ሊቃውንቶች” የሉንም። እዚህ ላይ በተለይ ከግዕዝ የመጡ ቃላት ላይ መጠንቀቅ ሳይጠቅም ኣይቀርም። ኣባላት፣ መምህራን፣ መኳንንት የመሳሰሉ ቃላት የብዙ ቍጥሮች ናቸው። ስለዚህ ኣባላቶች፣ መምህራኖች፣ መኳንንቶች፣ ቃላቶች የሚባሉ የብዙ ብዙ ስለሆኑ እንዲህ የኣሉ የዓማርኛ ቃላት የሉም። ፬. ሞክሼ ቀለሞች የተለያዩ ጥቅሞች የኣሏቸው ለግዕዝ ቋንቋ እንጂ ለዓማርኛ ኣይደለም የሚባለው ትክክል ኣይደለም።

፭. ዌብ (Web) ድር፣ ዌብፔጅ (Webpage) ድረገጽ ወይም ገጸድር ነው። ድህረገጽ ከገጽ በኋላ ስለሆነ ትክክል ኣይደለም። ይህ ስሕተት ምን ያህል እንደተስፋፋ ለማስተዋል ድህረገጽ፣ ድኅረገጽ እና ድሕረገጽ ቃላትን ኢንተርኔት ላይ በመፈለግ ስህተቶቹን መመልከት ይቻላል። ድሕር ማለት ኋላ ነው። Website ድረገጽ ነው። ስለዚህ ድሕረገጽ ወይም ድኅረገጽ Website ኣይደለም። ፮. የ“ው” ድምጽ ሳድስ እንጂ ካዕቡ “ዉ” ስለኣልሆነ “ነው” መከተብ ያለበት በሳድሱ “ው” ነው። ዓማርኛ “ዉ” ቀለምን የሚጠቀምባቸው ብዙ ቃላት ስለሌሉት መጠንቀቅ ጠቃሚ ነው። በ“ዉ” ቀለም ከመጠቀም ልዩነቱ ላልገባቸው “ዉ”ን ኣለመጠቀም ያዋጣል። ፯. “ጊዜ” እንጂ “ግዜ” ዓማርኛ ኣይደለም። ፰. ኣንዳንድ ደራስያን “እ” ቀለምን መቀነስ ይወዳሉ። “ተእኛ” እና “ተኛ” እንዲሁም “የእርሷ” እና “የርሷ” የተለያዩ ናቸው።

፱. ኣራት ነጥብ (“።”) እራሱን የቻለ ኣንድ የግዕዝ የምልክት ቀለም ነው። ኣንዳንድ ደራስያን ምልክቱን ከሁለት ባለሁለት ነጥቦች (ነቊጦች) ወይንም በእንግሊዝኛ ኮለን (“Colon”) መክተብ ስለጀመሩ ይህ ትክክል ከኣለመሆኑም ሌላ ኣስፈላጊ ያልሆኑ ሁለት መርገጫዎች በማስጨመር ጊዜና ስፍራ የሚያስባክን ግድፈት ነው። ከሁለት ቀለሞች የተሠሩትን ለመሠረዝም ሁለት መሠረዣዎች ያስፈልጋሉ። ኣራት ነጥቦች የሌሉት ጽሑፍም ችግር ውስጥ ሊወድቅ ይችላል። ፲. ዶክተሩ የእንግሊዝኛው ኮለን ለግዕዝ እንዲጠቅም ያደረጉት በኮለንነት ስለሆነ የግሉ የዩኒኮድ ቊጥር ከኣለው ባለሁለት ነጥብ (ወይም ነቊጥ) የባዶ ስፍራ የግዕዝ ምልክታችን ጋርም ኣንድ ኣይደለም። ኣራት ነጥብን ከሁለት ባለ ሁለት ነጥቦች (“፡”) በኮምፕዩተር መክተብም ግድፈት ነው። ምክንያቱም ይህ ኣሠራር ኣራት ነጥቦች ከሌሉት የኣማርኛ የታይፕ መጻፊያ የመጣ የኣሠራር ችግር ስለሆነ [908] እንጂ ሁለት ባለ ሁለት ነጥቦች ኣራት ነጥቦች የሚሆኑበት ኣከታተብ ወደ ኮምፕዩተር እንዳይገባ ዶክተሩ ከተከላከሉት ኣንዱ የጎደለ ኣጠቃቀም ነው። [909] Archived ማርች 5, 2016 at the Wayback Machine በሞዴት፣ ኢትዮወርድ፣ ግዕዝኤዲት በኮምፕዩተርና ግዕዝኤዲት በእጅ ስልክ የግዕዝ ኣራት ነጥብ ምልክት የተከተበውና እየተከተበ የኣለው በሁለት መርገጫዎች (“ዝቅ 3”) ነው። በግዕዝ ዩኒኮድ መደብ ውስጥ እንደሚታየው [910] እና እዚህ ጎን ላይ የኣለው ሥዕል እንደሚያሳየው ሁለት ነጥብና ኣራት ነጥብ የተለያዩ ናቸው። ሁለት ሁለት ነጥብና ኣራት ነጥብ የተለያዩ ናቸው። ኢትዮጵያውያንም ኣራት ነጥብን በማያስከትብ ፕሮግራም መጠቀም የለባቸውም። ፲፩. የመጽሓፎች ይዘት (Contents) እና ማውጫ (Index) የተለያዩ ናቸው። ፲፪. የኣንዳንዶች ስሕተቶች ምንጮች የተሳሳቱ ፊደላት ወይም መክተቢያዎች ናቸው፦ ምሳሌ “ቍጥር”ን በ“ቁጥር” መጻፍ።

፲፫. “ው”ን አንጂ “ዉ”ን የሚጠቀሙ ብዙ የዓማርኛ ቃላት የሉም። በቅርቡ ግን በኣለማወቅ በ“ው” ቀለም ምትክ “ዉ”ን በግድፈት የሚጠቀሙ ፀሓፊዎች እየበዙ ነውና ቢታሰብበት ኣይከፋም። መዝገበ ቃላትም ጠቃሚዎች ናቸው። (እንግሊዝኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት 1972)። “ው”ን በትክክል ከ40 በላይ ቃላት ውስጥ የተጠቀመ ጽሑፍ ምሳሌ እዚህ ኣለ። [911] “ው”ን በስሕተት ከ400 በላይ ቃላት ውስጥ የተጠቀመ ጽሑፍ ምሳሌ እዚህ ኣለ። [912] ፲፬. የግዕዙ “ሀ” ድምጽ ወደ “ኸ” የቀረበ ነው። “አ” እና “ኣ” ድምጽ ኣይጋሩም። [913] Archived ጁን 14, 2006 at the Wayback Machine [914] [915] [916] ፲፭. ኣንዳንድ ፀሓፊዎች በነጠላ ሰረዝ (“፣”) ምትክ ኮማ (“,”) (Comma) በኣራት ነጥብ (“።”) ምትክ ፔርየድ (“.”) (Period) መጠቀም ስለጀመሩ ፊደሉንና ቋንቋውን እያበላሿቸው ናቸው። ኣንዳንድ ምሁራን ስለማያስተውሉ ሁሉንም የዓማርኛ ቃላት መክተብ በማይችሉ እየተጠቀሙ የሚያወሩትን መጻፍ ኣይችሉም። የግዕዝ ፊደል ታዋቂነት የኣለ እስፔሊንግ ስሕተት ድምጽን በማስፈር ትክክክለኛ ድምፃዊ ፊደል መሆኑ ነው። ፲፮. ማንኛውንም የግዕዝ ቀለም በሦስት መርገጫዎች መክተብ ጊዜና ጉልበት ማባከን ነው። (Typing any Ethiopic glyph with three keystrokes is a waste of time and effort.) ምክንያቱም የዶክተሩ ኣሠራር እንግሊዝኛውን ከኣጋጠመው ችግር ጭምር ለማላቀቅ እንጂ ለግዕዙ የእንግሊዝኛውን ችግር ለማካፈል ስለኣልሆነ ነው። ፲፯. ኣንዳንድ ፀሓፊዎች የተሳሳቱ ቅርጾች ያሏቸውን ቀለሞች እየተጠቀሙ ስሕተቶችን እያስፋፉ ናቸው። ለምሳሌ ያህል የ“ኩ” እና የ“ቡ” መቀጠያዎች ኣንድ ዓይነት ኣይደሉም። ኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ ላይ የኣሉ ፊደላት የተሳሳቱ ከሆኑ መሳሳቱ ስለማይታወቅ የተሳሳቱ ቀለሞች ተለምደው መቸገርና ማስቸገር ኣይቀርም። እነ “ቋ”፣ “ኋ”፣ “ኳ” እና “ጓ” እራሳቸውን የቻሉ መስመር ላይ የሚያርፉ ቀለሞች እንጂ እነ “ቀ”፣ “ኃ”፣ “ካ” እና “ጋ” ስር በተጋደሙ መስመሮች የሚቀርቡ ኣዳዲስ የታይፕራይተር የእውሸት ፈጠራዎች ተቀጣጥለው እንደ ኣዳዲስ ቀለሞች ማቅረብ ተገቢ ኣይደለም። የ"የ”ን እንዚራን መለየት ለኣቃታቸው ኣንዳንድ ምሁራን የኣሌሉ ቀለሞችን መልኮች ማስተዋወቅ ኣይበጅም። [917] Archived ማርች 6, 2016 at the Wayback Machine ስለዚህ የግዕዝን ፊደል ከመለገስ መለየቱ ቢቀድም ሳይሻል ኣይቀርም። ፲፰. መስከረምና ሰፕቴምበር ብዙ ቀናት ይጋራሉ እንጂ ኣንድ ኣይደሉም። መስከረም 1 ሰፕቴምበር 1 ወይም September 1 ኣይደለም። ፲፱. ሁለት ዓመታት ወይም ዓመቶች እንጂ ሁለት ዓመት በማለት መጻፍ ስሕተት ነው። ፳. በግዕዝ ጽሑፍ ውስጥ ኣራት ነጥብና የመሳሰሉት (በቀለማት እንጂ) በባዶ ስፍራ መቀደም የለባቸውም። ምክንያቱም ግዕዝ ከእጅ ጽሑፍና የማተሚያ ቤቶች [918] ኣጠቃቀም ወደ ኮምፕዩተር ሲሻሻል መለ'የት የሚገባቸውን ዶክተሩ ስለኣቀረቡ ነው።

፳፩. የግዕዝ ፊደል የኦሮምኛው ፊደል ውስጥ ያለውን የግዕዙን “ዸ” እና ሰባት እንዚራን ቀለሞቹን ያጠቃልላል። ስለዚህ እንደ “በዻዻ” የኣሉትን ቃላት በ“በዳዳ” ወይም “ዻራርቱ"ን በ“ደራርቱ” መክተብ ግድፈት ነው። የኦሮምኛው ፊደል የዶክተሩ ሞዴት፣ ኢትዮወርድ፣ ግዕዝኤዲትና ሌሎች ፕሮግራሞች ውስጥ ቀርበው የሚፈልጓቸው ተጠቅመውባቸዋል። ፳፪. ሁሉንም ቀለማት የሌሉት ወይም የማይከትቡ ዓማርኛ እየተባሉ ሲቀርቡ ኣለተቃውሞ መቀበል ነውር ነው። ምክንያቱም ይህ ለፊደሉና ለሰዋሰው የኣለመጨነቅን ስለሚያሳይና የፀሓፊዎችን ችሎታ ጥያቄ ውስጥ ስለሚያስገባ ነው። ፳፫. ዓማርኛ “መጠጥ” እና “መጠጥ ኣደረገ” የሚለውን በማጥበቅ መለየት ኣይችልም የሚሉ ኣሉ። [919] [920] “መጠጥ” እና “መጠጥ ኣደረገ” ሁለት ትርጕሞች ያሏቸው ቃላት እንጂ በማጥበቅ የሚለዩ ኣይደሉም። ፳፬. በኮምፕዩተር ሁለት ነጥብ “፡” የግዕዝ የባዶ ስፍራን ምልክት ነጥብ በሌለው የባዶ ስፍራ የእንግሊዝኛው ኣጠቃቀም ጋር ደርበው ዓማርኛውን የሚያቀርቡ ኣሉ። ከሁለቱ ዘዴዎች ኣንዱን መምረጥ እንጂ ሁለቱንም መውደድ ኣያዋጣም።

፳፭. ኣንዳንድ ሰዎች ዓማርኛ የእራሱ ፊደል የለውም ይላሉ። ዓማርኛ የእራሱ ፊደል (Amharic Alphabet) የኣለው ቋንቋ ነው። [921] የግዕዝም ቋንቋ የእራሱ ፊደል ኣለው። የግዕዝ ቋንቋ ፊደላት የዓማርኛው ውስጥ ሲኖሩ ሁሉም የዓማርኛ ፊደላት የግዕዙ ቋንቋ ፊደላት ውስጥ የሉም። ግዕዝ ወይም Ethiopic የተለያዩ ቋንቋዎች የሚጠቀሙበት የፊደሉም ስም ሲሆን ለተለያዩ ቋንቋዎች ተጨማሪ ቀለሞች ተጨምረዋል። ፳፮. የኣማርኛ የታይፕራይተር ፊደል የግዕዝ ፊደል ኣይደለም። የእውሸት (Fake) ወይም የፈጠራ የዓማርኛ ፊደል እንጂ የዓማርኛም ፊደል ኣይደለም። መጽሓፍትም ሲታተሙ የነበሩት በግዕዝ ፊደል በማተሚያ ቤቶች ትክክለኛ ቀለሞች ነበር። ኣሁንም ቢሆን በድሮው ዓይነት ወይም ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ በኣደረጉት መነሻው ይህ ፊደል በሆነው የዩኒኮድ የግዕዝ ፊደል ዓይነት ነው። [922] የታይፕራይተርንና የማተሚያውን ፊደላት የማይለዩና ሁለቱ ኣንድ የሚመስሏቸው ኣሉ። ፳፰. በወልጋዳ፣ የተሳሳቱና ከሲታ ቀለማት ተጽፈው የሚቀርቡ ጽሑፎችና መጻሕፍት እየበዙ ነው። የፊደል መልክ ከኣላማረ ለማንበብም ኣያጓጓም። ጥሩ የግዕዝ ፊደል ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት “ነጋሪት ጋዜጣ”ን ሲያትምበት የነበረው ፊደል ነው። ብዙ መጻሕፍትም ታትመውበታል። [923]

፳፱. ግዕዝ ኮምፕዩተራይድ ስለሆነ በኮምፕዩተር የሚቀርቡት በዓለም ዙሪያ ሊታዩ ስለሚችሉ ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ዓማርኛውን በላቲን ፊደል የሚጽፉ ኣሉ። ግዕዝ ድምጻዊ ስለሆነ የተለያዩ ቋንቋዎችን ያስከትባል። እንግሊዝኛ ውስጥ የኣሉ ኣንዳንድ ችግሮችም የሉትም። [924] ፴. ግዕዝን በኣንድና ሁለት መርገጫዎች መክተብ ስለተቻለ ኣከታተቡ ከእንግሊዝኛው ጋር እኩል ሆኗል። ስለዚህ ማንኛውንም የግዕዝ ቀለም በሦስት መርገጫዎች መክተብ ያካስራል። ይህ የእጅ ስልኮችንም (Smartphones) ኣጠቃቀም ይመለከታል። ፴፩. ከላይ የተጠቀሱት ስሕተቶች ጥቂቶቹ ትግርኛንም ያጠቃልላሉ። ፴፪. ግዕዝ ኮምፕዩተራይዝድ ሆኖ ለኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች ቀርቧል። ወጉንና ሕጉን ጠብቆ መጠቀም የእራስንና የፈጣሪዎችን መብት መጠበቅ ነው። በተሰረቁ፣ በማይጽፉና የኣልተሟሉ ሶፍትዌሮች መጠቀም ለእራስና ለሌላው መብት ኣለመጨነቅን ያሳያል። ለጽሑፍ ጥቅም የሚያስፈልጉ ነፃ ሶፍትዌሮች ስለኣሉ ከእንደግዕዝኤዲት ዓይነት በስተቀር መግዛት ግዴታ ኣይደለም።

፴፫. ትክክለኛ ሰዋስው፣ የተሟሉ ቀለሞች፣ ትክክለኛ ቅርጾች እና የመሳሰሉትን በኣሌሏቸው መጠቀም ለቋንቋው መዳከም ምክንያቶች እንዳይሆኑ መጠንቀቅ ኣስፈላጊዎች ናቸው። ስሕተቶች ሲደጋገሙ ሊለመዱ ይችላል። [925] ዶክተሩ ከሰዋስው ተሳሳቶች ኣንዱ ናቸው። ፴፬. ስለ ግዕዝና ዓማርኛ ፊደላት ሲጻፍ ስለ ግዕዝ ቋንቋ የሚመስሏቸው ኣሉና ይታሰብበት። ፴፭. ፊደላችን ለኣፍሪቃውያንና ሌሎችም እንዲተርፍ በወጉ መጠቀምና መንከባከብ ይጠቅማል። [926] ፴፮. "ዓማርኛ" በግዕዙ "ዐ" የማይጻ'ፈው ቀለሙ ድምጹን ስለማይወክል ነው።

፴፯. ብዙ ስሕተቶችና ግድፈቶች የኣሉትን ጽሑፍ በዋቢነት ለመጠቀም ኣያስተማምንም። ምክንያቱም ደራሲው ኣስፈላጊዎቹን ጥንቃቄዎች ኣለማድረጉን ስለሚያሳይ ኣለመግዛት ወይም መተቸት ሳይሻል ኣይቀርም። ለምሳሌ ያህል "ነው" እና "ነህ" የመሳሰሉትን ቃላት "ነዉ" [927] Archived ጁን 6, 2020 at the Wayback Machine እና "ነክ" የሚሉ ኣሉ። "ኢትዮጵያ"ን በትክክል መጻፍ የማይችሉ ፊደል በሚገባ ኣልቈጠሩም ወይም ረስተዋል ማለት ኣይደለምን? ፴፰. የኣንዳንዶቹ ስሕተቶች ምንጮች ማተሚያ ቤቶች ናቸው። ለምሳሌ ያህል ቀደም የኣሉ ጽሑፎች ውስጥ የ"ፏ" ፊደል መስመሩ የኣለው ከላይ ሆኖ ሳለ የኣዳዲሶቹ ከታች ነው። ቀደም የኣለውን ምልክት ዶክተሩ ሲጠቀሙ የተሳሳቱ የሚመስሏቸው ኣሉ። ይኸንኑ መቀጠያ ከግዕዝ ወግ ውጪ "ፍ" ላይ ተደርጎ በቅርቡ የቀረበ ፊደልም ኣለ። ማተሚያ ቤቶች በትክክለኛዎቹ ቀለሞች ከመቶ ዓመታት በላይ የተጠቀሙ ስለሆኑ መሪዎች እንጂ ተከታይ መሆን የለባቸውም። ፴፰. ዓማርኛ ማጥበቂያ ኣይጠቀምም የሚሉ ፈረንጆችም ኣሉ። በዓማርኛ ፊደል ሲደረብ እንደእንግሊዝኛው ኣይጠብቅም። [928] ፴፱. ኣንዳንድ የዓማርኛ ተጠቃሚዎች ዓማርኛ ሞክሼዎ ድምጾች የሉትም የሚሉ ኣሉ። "ኣባይ"ና "ዓባይ" ኣንድ ኣለመሆናቸው በቅርቡ ከወንድሜ ጋር ስከራከር የዓባይ ጉዳይ የ"ባ" መጥበቅና ኣለመጥበቅ ነው በማለት ስላሳመነኝ ምርምሮች ኣስፈላጊ ናቸው። ፵. ዶክተሩ ለመንግሥት የኣቀረቡት የፓተንት ማመልከቻ በወጉ ጥበቃ ሳይደረግለት መንግሥትና ኣብዛኛው ሕዝብ ከዶክተሩ በተሰረቁ የግዕዝ ቴክኖሎጂ ሲጠቀም ቆይቷል። ኣሁን ለውጥ መጥቷል ስለተባለ ሁሉም ሌቦች መስረቅ ማቆም ይገባቸዋል። ሌብነት ተለምዶ የዶክተሩን ሥራዎች የሚደብቁም ኣሉ። ፵፩. ይህ ጽሑፍ ብዙ ዓይነት ግድፈቶች ኣሉት፦ ለምሳሌ ያህል ኣራት ነጥብ የለውም፣ በሳድሱ “ው” ምትክ ካዕቡን “ዉ” ተጠቅሟል፣ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ፣ ኢትዪጵያ እና ኢትዩጵያ በማለት ኣቅርቧል። [929] ፵፪. ኣንድ ሰው ነዋሪነቱን (Citizen ወይም Residence) እንጂ ዜግነቱን (Nationality) መቀየር ኣይችልም።

ሞክሼ ኆኄያት ለማስተካከል

የዓማርኛ ሞክሼ በተለያዩ ቀለሞች የተወከሉ ኣንድ ዓይነት ድምጽ ኣሏቸው የሚባሉ ኆኄያት ናቸው ይባላል። ሞክሼዎች ቢያንሱ ሁለት ሰዎች ስለሆኑ ስሞች ተጋሩ እንጂ ኣንድ ስለኣልሆኑ ኣንዱ ሞክሼ ሌላውን ሊሆን ኣይችልም። ስለዚህ የዓማርኛ ቀለሞች ሞክሼዎች ስለሆኑ ኣንዱን በሌላው መተካት ይቻላል የሚባለው ኣስተሳሰብ ትክክል ኣይደለም። የኣማርኛ ሞክሼዎች ናቸው የሚባሉት የእየእራሳቸው ቅርጾች፣ ድምፆችና ስሞች ስለኣሏቸው ሞክሼዎች ኣይደሉም። [930] ምሳሌ “ዓይን” የሚጻፈው በዓይኑ “ዐ” ነው። [931]

የዓማርኛ ሞክሼዎችን ማስወገድ በሚከተሉት ምክንያቶች ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል። ፩. ሞክሼዎች ኣንድ ስለኣልሆኑ ኣንድ ናቸው ብሎ ኣንዱን ማንሳትና ሌላውን መጣል ከመነሻውም የተሳሳተ ኣስተሳሰብ ነው። ፪. የእነዚህ ሞክሼዎች ፊደላት ድምጾች እስከ ፲፭፻፴ ዓ.ም. ድረስ ማለትም እስከ ዓፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥት ድረስ ተለይቶ ሲነገር ነበር። [932] ሞክሼ ቀለሞች ይቀነሱ የተባለው ኃሳብ የመጣው በታይፕ መኪና ዘመን መርገጫዎቹ ስለኣነሱ ነበር። የኣማርኛ የጽሑፍ መሣሪያ ዓማርኛ ስለኣልጻፈና ግዕዝ በዶክተር ኣበራ ዲጂታይዝድ ስለሆነ የታይፕ መሣሪያውና ቅጥልጥል ቅርጾቹ ቀርተዋል። ኣሁን ሁሉም ቀለሞች ዲጂታይዝድ ስለሆኑ የዱሮ ችግሮችም መፍትሔ ኣግኝተዋል። መፍትሔ የፈጠሩትን ማመስገንና ሥራዎቻቸውን ማስተዋወቅ የጥቂቱ ብቻ መሆን የለበትም። ፫. የኣማርኛ ታይፕራይተር ፊደል የዩኒኮድ ፊደል እንዲሆን የሞከሩት በሳይንሳዊ መረጃ ተሸንፈው ቀርተው ትክክለኛዎቹ የግዕዝ ቀለሞች የዩኒኮድ መደብ ውስጥ ገብተዋል። ይህ ከሆነ በኋላ ስዉ የሚያውቃቸው ቀለሞች ይቀነሱ ማለት የተማረውን ማስቸገር ስለሆነ ተገቢ ኣይደለም። ምክንያቱም የእያንዳንዱ ቀለም የሚከተበው በሁለት መርገጫዎች ስለሆነ በኋላም ከኣንድ መርገጫ የተረፉት ኣብላጫዎቹ የግዕዝ ቀለሞች የሚከተቡት በሁለት መርገጫዎች ስለሆነ የሞክሼዎች መኖር የፈጠረው ችግር የለም። ኣንዳንዶቹ ሞክሼዎችን የሚከትቡት ከኣንድ የመርገጫ ቍልፍ ስለሆነ እያንዳንዱን ሞክሼዎች የሚከትቡት ብዙ መርገጫዎችን በመጠቀም ነው። ሞክሼዎችን የሚጠሉት የማያዋጣው መክተቢያዎቻቸውን ለመጥቀም ሊሆን ይችላል። ይህ በተለይ የዓማርኛውን ቀለሞች በእንግሊዝኛ እስፔሊንግ መክተብ የሚፈልጉትን ይመለከታል። ፬. በስመ ሞክሼና መሻሻል ሞክሼዎች የኣልሆኑትን መቀነስ የፈለጉ ኣሉ። ምሳሌ፦ “ጐ”ን በ“ግወ” መተካት። ይህ ድምፃዊ ፊደላችንን ወደ ኣክሳሪው ፊደላዊ ፊደል በመቀየር ያዳክመዋል። የፊደል ጥቅም ቋንቋን ለመግለጽ እንጂ ለፊደል ኣጠቃቀም ሲባል ቋንቋን መቀየር ወይም መቀነስ ኣይደለም።

፭. የሞክሼዎቹ ማንነት በጥናት ላይ የተመረኰዘ ኣይደለም። ለምሳሌ ያህል መንትያ እንጂ ሞክሼዎች ኣይደሉም የሚሉ ኣሉ። [933] ፮. ሞክሼዎችን መቀነስ ጥቅም ቢኖረው ኖሮ የ“ከ" ቤት ድምጽን የሚጋሩትን “C” (“ሲ”)፣ “K” (“ኬ”) እና “Q” (“ኪው”) (ምሳሌ “Cake” እና “Queen” ወይም “ኬክ” እና “ኲን”) የላቲን ቀለሞች ተጠቃሚዎቻቸው ሊቀንሷቸውና ሦስቱንም በ“C” ብቻ መጠቀም በመረጡ ነበር። ይህ ኣስቸጋሪነቱን ለማመልከት የቀረበ ምሳሌ ነው። ፈረንጆች ለእነዚህ ቀለሞቻቸው የተለያዩ መርገጫዎች ቢመድቡም ለእነ “ሐ”፣ “ኀ”፣ “ኸ”፣ የግሎቻቸው መርገጫዎች መመደብ ኣይገባም የሚሉ ኣሉ። ዶክተሩ ይገ‘ባል በማለት ይኸን ኣይደግፉም። ፯. ሞክሼዎች እንዲጠፉ ከመቸኰል ልዩነታቸውንና ጥቅሞቻቸውን ማስተማር ከምሁራን ይጠበቃል። ምሳሌ፦ [934] [935] Archived ኦገስት 7, 2020 at the Wayback Machine [936] Archived ሜይ 5, 2018 at the Wayback Machine [937] [938] ኣለ። ፰. ሞክሼዎች የሌሉት ጽሑፍ ተለምዶ ሞክሼዎቹ ሊረሱ ይችላሉ። ሞክሼዎችን የማያውቋቸው ምሁራን የቆዩ ጽሑፎችን በሚገባ ላያውቁና ትርጕሞቻቸውን ላይረዱ ይችላሉ። ዶክተሩ የሠሩት የማጥበቂያና የማላልያ ቀለሞችም ላይጠቅሙ ይችላሉ። በቍጥሮቹ በኣለመጠቀም የተነሳ የግዕዝን ኣኃዞች የማይለዩ ምሁራን ኣሉ ይባላል።

፱. ምክሼዎችን የማይወዱ ጥቅሞቻቸውን መማር የማይፈልጉ ሊሆኑ ይችላሉ። የማይጽፉና ያልተሟሉ መክተቢያዎች የሚያቀርቡ ስለኣሉ ዘላቂ ችግሮችን ሲፈጥሩ ዛሬ መታገስ ኣስፈላጊ ኣይደለም። (የሞክሼዎች ኣለመኖር የፊደላቱን ቊጥሮች በማስቀነስ ኣከታተብ ቢያቀል'ም ኣማራጭ እንጂ ግዴታ መሆን የለበትም ባይ ናቸው ዶክተሩ። ምክንያቱም ኣማራጭነቱ አንደማያዋጣ ኣቅርቦ ማሳመን ስለሚቻል ነው።) ፲. ወደፊት በኮምፕዩተር እንድንራቀቅ ትክክለኛዎቹንና ሳይንሳዊ መሠረቶችን ስለፈጠርን ከሞክሼዎች መኖር ይልቅ ኣለመኖር ሊጎዳ ይችላል። ወደፊት ኮምፕዩተር ስለሚያስተካክለው የሞክሼዎች ኣጠቃቀም ችግር ስለማይሆን የሚያስቸግሩት ቀለሞቹን የማያውቁት ሊሆኑ ይችላሉ። ጥቂት የኣናሳ ተናጋሪዎች ቋንቋዎች ቀለሞች የተሠሩት ሞክሼዎች የተባሉትን በመጠቀም ስለሆነ ሌሎች ኢትዮጵያውያን የሚያውቋቸውን የዓማርኛ ቀለሞች የማያውቁ ዓማርኛ ተናጋሪዎች መኖር ዓማርኛ ቋንቋንና ፊደሉን ይጎዷቸዋል እንጂ ኣይጠቅሙም። ስለዚህ በስመ ሞክሼ ዓማርኛውን ማዳከም ለዓለም ሕዝቦች ጭምር ጉዳት ነው። ፲፩. ኣንድ ጽሑፍ ሞክሼዎች በተባሉትም ይሁን በሌሎቹ ቢጻፍ ልዩነቶቻቸውን ለማያውቁ የሚፈጥሯቸው ችግሮች የሉም። ፲፪. ዓማርኛ የግዕዝ ቋንቋ ፊደል ላይ የሚያስፈልጉትን ኣዳዲስ ቀለሞች ጨመረ እንጂ የግዕዝን ፊደል ኣልቀነሰም። የግዕዝ ፊደል መክተቢያ ሁሉንም ቀለሞቹን ማስተናገድ የቴክኖሎጂው መጀመሪያ ነው። የኮምፕዩተር ቴክኖሎጂው የገላገለው የግዕዝን ቀለም ለዘመናት ሲለቅሙ የነበሩትን የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ሠራተኞች ጭምር ነው። ይህ ጉዳይ የአማርኛ የታይፕ መጻፊያውን ኣይመለከትም።

፲፫. የትግርኛ ቀለሞች በዓማርኛው ላይ ተጨማሪ ኣሏቸው እንጂ የተቀራረቡ ናቸው። የትግርኛ ፊደል ውስጥ የሌሉ ጥቂት የዓማርኛ ቀለሞች ኣሉ። ኣንዳንድ ፀሓፊዎች ግን ከትግርኛ ቀለሞች ውስጥ እነ “ሀ”፣ “ሐ”፣ “ኀ”፣ “አ” እና “ዐ” የራብኦቻቸው ሞክሼዎች መስለዋቸው ተሳስተው ሊቀንሷቸው ኣጥቊረዋቸዋል። [939]] [940] እንደ ዶ/ር ኣበራ ሞላ ገለጻ ግን ኆኄያቱ ሞክሼዎች ስለኣልሆኑ መብታቸው መከበር ኣለበት ነው። [941] ይኸንንምና የ“ሠ"ንና የ“ፀ" እንዚራን የኣጠቃለለውን ሞክሼነት በዓማርኛና በእንግሊዝኛ ተቃውመዋል። [942] ፲፬. ሞክሼነት ልብወለድ እንጂ ሳይንስ ኣይደለም። ዶክተሩ ዲጂታይዝ ያደረጉትና የእያንዳንዱ ግዕዝ ቀለም መብት ተጠብቆ ዩኒኮድ ውስጥ እንዲገባ የታገሉት ሳይንስንና ታሪክን በመመርኰዝ ነው። [943] ፲፭. የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች በፊደላቸው ሲጠቀሙ ብዛቱ ኣላስቸገራቸውም። ብዛት ችግር የሆነው መርገጫዎች ስለኣነሱ ስለሆነ የምሁራን ዓላማ ለችግሮቹ መፍትሔ መፍጠር እንጂ ለጊዜያዊ ችግርና መርገጫዎች ሲባል ፊደል መቀነስ መፍትሔ ኣይደለም። የታይፕራይተር ፊደል ቀናሾችና ቀንጣሾች ቢሳካላቸው ኖሮ ሞክሼዎቹ ስለማይኖሩ ዶክተሩ መፍትሔ ለመፍጠር ይቸገሩ ነበር። እንዲህም ሆኖ የታይፕራይተሩን ቍርጥራጮች ኣንዱ ግዕዝ ነው ብሎ ሲያወናብድ ዶክተሩን በመደገፍ የተማሩበት የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲም ይሁን የፊደሉ መብት ተከራካሪ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኣለፉት ፴ ዓመታት ስለ ዶክተሩ ሥራዎችም ይሁን ሁሉም የግዕዝ ቀለሞች ዩኒኮድ እንዲገቡ ስለታገሉት ትንፍሽ ኣላሉም። ፲፮. ስር የሰደደን ነገር መቀየር ኣስቸጋሪ ነው። [944] [945]

፲፯. በስመ ሞክሼ ቋንቋው እየተበላሸ ነው። ለምሳሌ ያህል “ቍጥር”፣ “ሽኵቻ”፣ “ጫጕላ”፣ “ጓጕቷል”ን የመሳሰሉ ትክክለኛ ቃላት እንዳይኖሩ ሊሆን ነው። ያም ካልሆነ እንደላቲኑ ኣስተሳሰብ ሁለት ቀለሞች በኣንድነት ኣንዲነበብ የማድረግን ባዕድ ኣጠቃቀም ያስከትላል። ፲፰. “ጸ” እና እንዚራኖቹ የ“ፀ” እና እንዚራኖቹ ሞክሼዎች ናቸው ተብለው ቀርተው ዩኒኮድ የሚያውቀው “ጿ” በሞክሼ ስም እንዲወገድ ተፈልጓል። ስምንተኛው የ“ፀ” ድምጽ በስሕተት ስለሌለና ዩኒኮድ ስለማያውቀው ዩኒኮድ ውስጥ እንደማስገባት ዝም ማለት በስመ ሞክሼ ፊደሉን ለማበላሸት እንጂ ለመቀነስ ብቻ እንዳልሆነ ያመለክታል። ምክንያቱም ለኣንዳንዶቹ ሁለቱም “ጿ"ዎች ሞክሼዎች ስለሆኑ ነው። “ጸሎት” እና “ፀሓይ” ውስጥ “ጸ” እና “ፀ” ሲነገሩ ኣፋችን ውስጥ ምላስ የሚያርፈው በተለያዩ ስፍራዎች ነው። ፲፱. ትግርኛ እንደ ዓማርኛው የግዕዝ ቋንቋ ፊደል ላይ የሚያስፈልጉትን ኣዳዲስ ቀለሞች ጨምሯል። ግዕዝና ትግርኛ የሞክሼ ችግር የለባቸውም ይባላል። የሞክሼዎችን ችግር ዓማርኛ ላይ ማጥበቅ ለምን ኣስፈለገ? ፳. ኣንዳንድ ሰዎች ሞክሼዎች የግዕዙን ድምጽ በዓማርኛ ኣጥተዋል ይላሉ። [946] የሞክሼዎች ጉዳይ ግን የቃላት ኣመጣጥንና በቀለም የትርጕማንን መለያየት ጭምር ያመለክታል። [947] ምሳሌ፦ ዓይኑ “ዐ” የጠበቀ ነው [948][2] ትክክለኛ ኣጠቃቀሞችንም ለመከተል መዝገበ ቃላት ኣሉ። “ፀ”ም የጠበቀ ነው። [949] ትክክለኛዎቹን የኣማርኛ ኆኄያት የተከተለው ኣፄ ኃይለ ሥላሴ በ፲፱፻፷፪ ዓ.ም. የኣሳተሙት መጽሓፍ ቅዱስ ኣስተማማኝ ነው ይባላል። [950]

፳፩. ቅዱስ ኦነሲሞስ ነሲብ “መጫፈ ቁልቁሉ”ን በግዕዝ ፊደል በ፲፰፻፺፪ በኦሮምኛ ጽፈው ሲያሳትሙ በኋላ ሞክሼዎች ከተባሉት ኣንዳንዶቹን ኣስወግደዋል። “ፍቅር እስከ መቃብር” [3] 67 ሞክሼዎች ቀለሞች በሌሉት አማርኛ በክቡር ዶ/ር ሓዲስ ዓለማየሁ በ፲፱፻፶፪ ታትሟል። (ይህ የሆነው የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ሞክሼ የተባሉትን ቀለሞች እየኣሉት ነው።) የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማእከል [951] ግዕዝ ኮምፕዩተራይዝድ ከሆነ በኋላ በታይፕራይተር ዓይነት ቅጥልጥል ፊደል “ኣማርኛ መዝገበ ቃላት” ሞክሼዎች የተባሉትን በሌሉት ቀለሞች በ፲፱፻፺፫ ኣትሟል። ስለ ሞክሼዎች በምሳሌ ቀረቡ እንጂ ደራሲዎቹ በሥራዎቻቸው ታላላቅ የኣገር ባለውለታዎች ናቸው። ፳፪. ዶ/ር ኣበራ ሞላ “ኧ” ስምንተኛው የ“አ” ቤት ፊደል መሆኑን በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. ጽሑፋቸው እስከኣመለከቱበት [952] ጊዜ ድረስ ብዙዎቹ የኣላወቁት ይመስላል። ሓዲስ ዓለማየሁ “ኧ” የእራሱ እንዚራን እንዳለው ቈጥረው በስሕተት ስድስት እንዚራኑን ጭምር ቀንሼዋለሁ ብለዋል። [953] የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲም "ኧ”ን ጥቅም ላይ ኣላዋልኩም ቢልም “ኧ”ን በስምንተኝነት ሳይጠቀምበት ጥሎታል። “አ” እና “ኧ” ሞክሼዎች ስለኣልሆኑ መጽሓፎቻቸው ውስጥ የማይመለከታቸው የሞክሼዎች ኣጠቃቀምና ውይይት ውስጥ ሁለቱም በስሕተት ጣልቃ ኣስገብተዋቸዋል። እነዚህ የኣለ በቂ ምርምር በስመ ሞክሼ የቀረቡ ጉዳዮች የኣለፉትን ችግሮች እያስወገዱ የኣሉትን የዶክተሩን ሥራዎች ኣክብደዋቸዋል። ሓዲስ የ“ኧ”ን ግዕዞች ብቻ ይዤ እርባታቸውን ጥያለሁ ቢሉም “ኧ” የግዕዝ ቤት ቀለም ኣይደለም። የ“ኸ”ን ግዕዝ ብቻ ይዤ እርባታቸውን ጥያለሁ ቢሉም “ኸ”ን ከእንዚራኖቹ ጋር ጥለዋል ማለት ይቻላል። ምክንያቱም ሓዲስ “ኹ”ን የጣሉት የ“ሁ” ሞክሼያቸው በመሆኑ "ኸ"ም የ"ሀ" ሞክሼያቸው ስለሆነ እንደሌሎቹ መጣ'ል ነበረበት። ዩኒቨርሲቲውም ነባር የፊደል ገበታው ውስጥ “ኧ”ን እንደ ግዕዝ ቤት ወስዶ እርባታዎቹን በጥያቄ ምልክቶች ኣቅርቧቸዋል። ፳፫. “ሀ” እና “ሃ” እንዲሁም “አ” እና “ኣ” ሞክሼዎች ኣይደሉም። እነዚህን ቀለሞች በስመ ሞክሼ ተሳስቶ በማስወገድ ማግደፍና ኣንዱን ቀለም ጥሎ ሌላውን ማንሳት ትክክል ኣይደለም። ይህ በስመ ሞክሼ ፊደል መቀነሰ ሳይሆን ፊደል ማስወገድ ነው። ለምሳሌ ያህል የሓዲስ መጽሓፍ ውስጥ ራብዖቹ “ሃ” እና “ኣ” የሉም። ሓዲስ መጽሓፋቸው ውስጥ በ“ሃ” ምትክ “ሀ”ን እና በ“ኣ” ቀለም ምትክ “አ”ን በስሕተት ተጠቅመዋል። እነዚህን ስሕተቶች ለማስወገድ በኣሁኑ ጊዜም አንደኣስፈላጊነቱ በ“ሀ” ምትክ “ሃ” እና በ“አ” ምትክ “ኣ”ን መጻፍ ትክክል መሆኑን ለኣንዳንዶቹ ማስገንዘብ ኣስቸግሯል። ምክንያቱም መመራመር በማይችሉባቸው ጊዜያት የተማሯቸውን ስሕተቶች ከኣደጉም በኋላ በምርምር ለማሳመንና ለማስተካከል ሲሞከር የሚያስቸግሩ ስለኣሉ ነው። ምሳሌ፦ “ኣበራ” አንጂ “አበራ” ትክክል ኣይደለም። በተጨማሪም ፊደል ቀናሾችና ቀንጣሾች ወደዱም ኣልወደዱም ዶክተሩ ኣሸንፈው ሁሉም የግዕዝ ቀለሞች የዩኒኮድ መደብ ውስጥ ስለገቡ በእነዚህ ስሕተቶችና ግድፈቶች መቀጠል ኣስፈላጊ ኣይደሉም። ወደፊት ኮምፕዩተር ትክክለኛዎቹን ስለሚያቀረብ ዛሬ ሥራ ከማበላሸት ይልቅ መማር ሳይጠቅም ኣይቀርም። ፳፬. ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ የምልክት መርገጫ ላይ ወደዳር ከመደቧቸው መካከል “ኸ” ኣንዱ ነበር። ሓዲስ የ“ኸ” እና “ኧ” ግዕዞቻቸውን ብቻ ይዤ እርባታዎቹን ጥያለሁ ሲሉ “ኸ” ወደ ግዕዙ “ሀ” ድምጽ የቀረበና “ኧ” (እንደ “Earth” “አርዝ”) የግዕዙ “አ” ድምጽ መሆኑን የተገነዘቡ ኣይመስልም። በሌላ በኩል ስማቸውን “ሀዲስ” እንጂ “ሃዲስ” ኣለማለታቸውና “ኸ” ኣራተኛ የ“ሀ” ሞክሼያቸው መሆኑን ስለኣልጠቀሱም የተቸገሩበት ይመስላል። ስለዚህ በሓዲስ ኣስተሳሰብ “ኸ” እና “ኧ” ለየት የኣሉ ቀለሞች ብቻ ተደርገው በስሕተት የተወሰዱ ናቸው ማለትም ይቻላል። የ“ኸ” ጉዳይ ኣንዳንድ ፈረንጆችንም ግራ ያጋባ ይመስላል። ለምሳሌ ያህል የ“ኧ” ድምጽ ወደ “እዋ” የቀረበ ስምንተኛ የ“አ” ቤት ቀለም በመሆኑ በተለምዶ “ኧረ” የሚለው ቃል ኣጻጻፍና ኣነባብ የተሳሳቱ ስለሆኑ ትክክለኛው “አረ” ነው። ስሕተቱ የ“አ”ን ድምጽ እንጂ የፊደሉን መልክ ኣይመለከትም። ምሳሌም እዚህ ኣለ። [954] የስሕተቱ ምንጭ “አ” እና “ኣ” እንደሞክሼ ተወስደው የግዕዙ “አ” ሥራ ስለጐደለ ለ“ኧ” የተሰጠው ሳይሆን ኣይቀርም ይላሉ ዶክተሩ። ቢሳካላቸው ሓዲስ “ኣ”ን የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ “አ”ን እያጠፉ ፊደላቱ ላይኖሩን ሲደረግ የሚቈረቈር እየጠፋ ነውና ትውልዱን ምን እንደነካው ማወቅ ኣስቸግሯል።

፳፭. ሊቁ ኣለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ ኣንዳንድ ፀሓፊዎች ሲጠነቀቁ ብዙዎቹ አዐ፣ ሀሐኀ፣ ሰሠ፣ እና ጸፀ ፪ እና ፫ የሆኑበት ምክንያት ምን እንደሆነ ኣያስቡም ብለው የጥንቱ “አበገደ” ፊደል ኣኃዛዊ ስለሆነ “ጐ” ሰባ ቍጥርን ይወክላል ይላሉ። ፳፮. ሞክሼዎችን ለማስወገድ በተጀመረው ዘመቻ ሳቢያ የማያስፈልጉ ቀለሞች ዓማርኛ ቃላት ውስጥ ብቅ እያሉ የቋንቋውን የኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች ጽሑፎች ማበላሸት ቀጥሏል። ፳፯. የዓማርኛ ፊደልን መጻፍ የኣልቻለው የጽሕፈት መሣሪያ ሳይጽፈው ተዘልሎ ኮምፕዩተር ደርሶለታል። ትክክለኛዎቹን ኆኄያት ከመማር ይልቅ መቀነስ የሚፈልጉትን ቴክኖሎጂ ስለሚደርስላቸው የሞክሼዎች ተግዳሮት ዘላቂ ኣይደሉም። በፊደሉ ብዛት የተነሳ መጻፍ ያስቸግራል ሲሉ የነበሩት መፍትሔ ከተፈጠረለት ፴ ዓመታት እንደኣለፉ የኣልሰሙ ይመስላል። [955] “The quick brown fox jumps over the lazy dog.” የሚለውን የእንግሊዝኛ ዓረፍተ ነገር “ዘ ኲክ ብራውን ፎክስ ጀምፕስ ኦቨር ዘ ሌይዚ ዶግ።” ብሎ ሞክሼውን ሳይቀንሱ ጭምር በዓማርኛ መጻፍ ያታርፋል። ለምሳሌ ያህልም የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲው ማዕከል ሞክሼዎች እንዲቀነሱ ስለወሰነና “ኲ” በ“ኩ” አንዲተካ ስለፈለገ ቀለሙ ስለማይኖር “ኲክ” (quick) የሚለው ቃል በዓማርኛ እንዲጻፍ የሚፈልገው “ኩክ” በማለት ነው። ከላይ የቀረበውን 36 ሥፍራዎች የወሰደውን የእንግሊዝኛ ዓረፍተ ነገር በግዕዝ 24 ሥፍራዎች መጻፍ ስለሚቻል ሞክሼዎችን የማስቀረት ጉዳት አንጂ ጥቅም ኣያሳይም። ጽሑፍን በፊደላዊ (Alphabetic) ፊደል ከመጻፍ ይልቅ በግዕዙ ድምጻዊ (Phonetic) ፊደል መጻፍ የወረቀትንና የኮምፕዩተር ጽሑፎች ማስቀመጫ ስፍራዎችን ስለሚቆጥብ ጽሑፎችን በላቲን ፊደል ለሚጽፉ ኢትዮጵያውያንም ትምህርት ነው። ምክንያቱም ዓረፍተ ነገሩን በኦሮምኛ ቁቤም ሆነ በአማርኛ ቁቤ መክተብም ኣያታርፍም። ፳፰. ዕውቀትን መቀነስ ሞክሼዎችን እንደመቀነስ ስንፍና እንጂ ጉብዝና ኣይደለም። ኢትዮጵያውያን ሞክሼ የተባሉትን ሳይቀንሱ ለረዥም ዘመናት በእጃቸውና ማተሚያ ቤቶች ሲጠቀሙ ቆይተው ታይፕራይተርን የኣዩ ለመቀነስ ታግለው ኣልተሳካላቸውም። ነገር በቀለለበት በእዚህ ዘመን እያንዳንዱ ፀሓፊ በቀላሉ ኣታሚ በሆነበት ጊዜ ስለ ፊደል ማስተማር እንጂ መቀነስ ምሁራዊ ተግባር ኣይደለም። “መሳሳት” (“ርህሩህ ወይም ስስ መሆን”) እና “መሣሣት” (“ትክክል ኣለመሆን”) ኣንድ የኣልሆኑት [956] በዓማርኛ ድምጽ መጥፋት ኣይደለም። ኣንዳንዶቹ ፊደል መቀነስ የሚፈልጉት ለዓማርኛው ከኣላቸው ጥላቻ ወይም ኣጎብጋቢነት ሊሆን ይችላል። የፊደላቱን መልኮች ከመቀየር ኣንስቶ ግዕዙን በላቲን ፊደል መተካት የሚፈልጉ ኣሉ። “ተደጋግሞ የሚነሳውም የቱርክ (ኣረብኛ) ፊደሏን ትታ የላቲን ፊደልን መቀበሏና የጃፓን ፊደሏን ሳትቀይር በሥልጣኔ የመገስገሷ ታሪካዊ ተሞክሮ ነው። የእኛ ኣገር የብሔር ፖለቲከኞችና ኣመራራቸው የቱርኩ ልምድ ይሻለናል ብሎ ከወሰነ፣ ይኼው ሁለት አሥርት ዓመታት ገደማ ተቆጠሩ” ይላል ይህ [957] ጽሑፍ። የዓማርኛውን ፊደል ትተው ቋንቋውን በላቲን ፊደል የሚጽፉ ባይጠፉም፤ ግኝቶቻቸው ከግዕዝ ኣልፈው ለላቲኑ ስለጠቀሙ ዶክተሩ በሥራና ተቃውሞ ቀድመዋቸዋል።

፳፱. ግዕዝ በማተሚያ፣ የኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ ቴክኖሎጂዎች በሚገባ እየተጠቀመ ነው። እንደሰዉ ብዛት ግን ብዙ ጽሑፎች በኮምፕዩተርና የእጅ ስልኮች ተጽፈው ኣልተቀመጡም። በኣንድ የፊደል ዓይነት መጻፍ የኣልቻለን ሕዝብ ሞክሼዎች በኣሉትና በሌሉት ጻፍ ማለት ተገቢ ኣይመስልም። ምክንያቱም ኣዲስ ነገር ከጥንቱ ጋር ይቀርባል እንጂ ስለማይተካው ነው። ፴. የግዕዝ ቋንቋ ቀለሞች የዓማርኛ ቋንቋ ፊደል መነሻ ቢሆኑም የተለያዩ ሰዎች የተለያዩ ቀለሞችን ሞክሼዎች ናቸው በማለት ከዓማርኛ ሲቀንሷቸው ተስተውሏል። እነሱ የኣሰቡት ቢሳካላቸው እነ “Quick”፣ “Which”፣ “Qwench”፣ “Guie”፣ “Kwikset”ን የመሳሰሉት ቃላት በእንግሊዝኛ እንጂ በዓማርኛ መጻፍ ላይቻል ነው። እንደእነዚህ ዓይነት ምሁራን ለማያውቋቸው የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚ ቋንቋዎች ቀርቶ ለሚያውቁት ዓማርኛ ደንታ የሌላቸው ሳይሆኑ ኣይቀሩም። ፴፩. በስመ ሞክሼ ፊደሉን መቀነስ የጀመሩት ጥቂት ዓማርኛ ተጠቃሚዎች ናቸው። የግዕዝ ፊደል ኣንዱ ትልቅ ችሎታ ለኣዳዲስ ድምጾች ኣዳዲስ ቀለሞች መፍጠር መቻሉ ነው። ፴፪. ዓማርኛ ፊደላቱን ከግዕዝ ቢወስድም ለቋንቋው የማያስፈልጉትን ሞክሼዎች መጣል ነበረበት የሚሉ ኣሉ። ዓማርኛ የሚጥላቸው ሞክሼዎች የሉም። እንግሊዞች ፊደላቸውን ለማሻሻል ሞክረው ኣልተሳካላቸውም እየተባለ ዓማርኛው መሻሻል ኣለበት ማለት ምንድን ነው? [958]

፴፫. የግዕዝ ፊደል ውስጥ ለሌሉ ድምጾች ኣዳዲስ ቀለሞች መፍጠር ሊያስፈልጉ ይችላሉ። ይህ ፊደላችን ለሌሎች ቋንቋዎችና ፊደላትም እንዲጠቅም ያስችላል። ዓማርኛ ከግዕዝ የወረሳቸውን ቃላት እየተጠቀመ እየኣደገ ነው። ፊደላቱ እንዳይቀነሱ ከሚፈልጉት ኣንዱ ዶ/ር ኣምሳሉ ኣክሊሉ ናቸው። [959] ይህ በእንዲህ እንዳለ ግዕዝ ውስጥ የኣሉት በተናጠል እየቀጠሉ ሞክሼዎች የሚሆኑት ዓማርኛ ስለሆኑ የሚመስላቸው ኣሉ። ይህ እውነት ኣይደለም። ፴፬. ኢትዮጵያውያን ቀለሞቻቸውን ሳይቀንሱ በብራናና ማተሚያ ቤቶች ብዙ ደክመው በሚገባ ተጠቅመውባቸው ኣቆይተውናል። ይኸንኑ ፍላጎት ዶክተሩ በኮምፕዩተር ከማሳካት ሌላ ለዩኒኮድ ኣቅርበው የፊደሉ ፍላጎት ተሟልቷል። የግዕዝን ፊደል ሳይጽፍ የእንግሊዝኛውን የታይፕ መሣሪያ ዓማርኛን እንደጻፈ መቍጠርና ይኸንኑ በኮምፕዩተር መጠቀም እራስን ማታለል ነው። ፊደል መቀነስና መቀንጠስ ከታይራይተር ጋር ጊዜው የኣለፈበት ኣስተሳሰብ ነው። ፴፭. በኣንድ በኩል ፊደል በዛ እያሉ በሌላ በኩል የሚጠብቅና የሚላሉ ቃላት ችግር ፈጥረዋል የሚሉ ኣሉ። [960] የፊደል ቀናሾች ስንፍና [961] ወደ ኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ ስለገባና ኣንዳንዱን ሰው ከሚገባው በላይ ቸልተኝነት ስለተጠናወተው መቀስቀስ ኣስቸግራል። ስለ ቴክኖሎጂ ኣንብቦ ከመረዳት ይልቅ በወሬ የተገኘውን ሶፍትዌር እየተጠቀመ ፊደል ሲጎድልበት መጠየቅ የማይችል ሆኗል። ፴፮. በተቀነሱ ቀለሞች የሚጠቀሙ ደራስያን ጽሑፎች ኢንተርኔት ላይ ተፈልገው ላይገኙ ስለሚችሉ እራሳቸውና ሥራዎቻቸውን ከጥቅም ውጪ እያደረጉ ናቸው።

፴፯. ሁለተኛው የሞክሼዎች ጥቅም ዓማርኛ ከሌሎች ሴማዊ ቋንቋዎች ጋር ያለውን ዝምድና ስለሚያመላክቱ ነው። [962] የዓማርኛ ሞክሼዎችን ለመለየት ከቃላቱ ብቻ ፍንጭ ማግኘት ስለሚቻል ምሳሌዎችን ከመሸምደድ ይልቅ መረዳት ሳይጠቅም ኣይቀርም ይላሉ ዶክተሩ። ለምሳሌ ያህል “ፀሓይ" የሚለ ቃል ውስጥ “ፀ" የጠበቀ ስለሆነ ፀሓዩን “ፀ" መጠቀም ይጠቅማል። “ንሥር"ና “ንስር"ን ለመለየት የቋንቋው ተናጋሪ በድምጽ ስለሚለያቸው “ንስር"ን ከእሳቱ “ሰ" ጋር በማያያዝ ኣገባቡን መለየት ይቻላል። ሌላ ምሳሌ “ምሥር" እና “ምስር" ሲሆን የጠበቀው እንደንጉሡ “ሠ” ባለ ንጉሡ “ሠ” “ምሥር" መሆኑ ነው። “ምሥር”ን ኣጥፍቶ እንደ “ምስ'ር” መጻፍ ሥፍራና መርገጫዎች በማስጨመር ያካስራል። “ምስር” እንዲሁ ወይም (Default) ያልጠበቀ ሲሆን “ምሥር” እንደ ዓይኑ “ዐ” የጠበቀ ስለሆነ ኣነጋገሩን ከፊደሉ ማገናኘት ሳይጠቅም ኣይቀርም። የሞክሼዎች ኣጠቃቀም ኃይማኖታዊ ነው የሚሉም ኣሉ። [963] "ዓይን"ና "ዓመት" የጠበቁ ናቸው ቢባል የወንዙን ስም በ"ኣባይ" የሚጽፉ ኣሉ። [964] ስለዚህ እነዚህ ነገሮች ጥናት ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ያህል "ኣባይ" እና "ዓባይ"ን በድምጽ መለየት ይቻላል እንዳይባል የሚጠብቀውና የሚላላው "ባ" ቀለም ስለሆነ ነው። ፴፰. የሞክሼ ተብዬዎቹ መኖር ዓማርኛውን ኣዳበረው እንጂ ኣልጎዳውም። ይህ ፊደሉን የሚጠቀሙ ሌሎች ቋንቋዎችንም ሊመለከት ይችላል። የላቲን ፊደል ስለኣስቸገረ ፈረንጆች ኣዳዲስ ፊደላት እየፈጠሩ እያሻሻሉት ነው። ፴፱. የሞክሼ ፊደል ጉዳይ ጊዜው የኣለፈበት ክርክር ነው። በኮምፕዩተር ዘመን ቴክኖሎጅው ችግሮቻችንን ስለሚፈታ ፊደል ለመቀነስ መከራከር ግዕዛዊ ኣይደለም። ትክክለኛዎች ቀለሞች ከሌሉ ወደፊት ኮምፕዩተሩን ማናገር ቀላል ኣይሆንም። ሞክሼዎችን በሚፈልጉና በማይፈልጉ መካከል የሚፈጠሩት ችግሮች ሰዉ ላይ ሥራ ያበዛሉ። ፵. ኆኄያትን መጠበቅ ቅኔ ላይ ትንሽ ችግር ሊፈጥር ይችላል። [965]

፵፩. በቅርቡ በግዕዝ ፊደል መብዛት የተነሳ መዝገበ ቃላትን መጠቀም ኣስቸገረ በማለት ፊደል እንዲቀነስ የሚል መጽሓፍ ተጽፏል። [966] ይህ ጊዜው ያለፈበት ኣስተያየት ነው። ወደፊት ኣንድ የሚፈለግን ቃል ጽፎ ኮምፕዩተር ካለበት ያወጣዋል እንጂ መጽሓፍ ማገላበጥ ኣያስፈልግም። ፵፪. መጥበቅና ኣለመጥበቅ ከሞክሼዎች ጋር እንዳይምታቱ መጠንቀቅ ያስፈልጋል።

በሌላ በኩል የዓማርኛን ሞክሼዎች መወገድ የሚፈልጉ ምክንያቶች ቢኖሯቸውም [967] ኣንዳንዶቹ ከላይ ተጠቃቅሰዋል። ፩. ስድስት ዓይነቶች “ሀ”ዎች ቢኖሩም በሃሌታው “ሀ” እና እንዚራኖቹ ብንጠቀም የእነ “ሐ”፣ “ኀ”፣ “ኈ”፣ “ኸ” እና “ዀ” እንዚራኖች ጭምር ድምፆች ኣንድ ዓይነት በመሆናቸውና ዓማርኛ ውስጥ ስለጠፉም ስለማያስፈልጉ የቀለሞች ቍጥር ይቀንሳል ነው። ፪. ሞክሼዎች ቢቀነሱ ግዕዝን ለመክተብ በሁሉም ቍልፎች መጠቀም ኣያስፈልግም የሚሉ ኣይጠፉም። ፫. የኣለነው ዓለም እየሰለጠነና ነገሮች እየቀለሉ በኣሉበት ዘመን ስለሆነ መቀነስ የምንችላቸው ስለኣሉ መጓተት ኣያስፈልግም የሚሉ ኣሉ። ፬. በግዕዝ ፊደል የሚጠቀሙ የተለያዩ ቋንቋዎች ድምፆችን የሚወክሉት ኣዳዲስ ቀለሞች ተሠርተው ሥራ ላይ ስለዋሉ የማያስፈልጓቸውን ሞክሼዎች ማስወገጃ ጊዜው ኣሁን ነው የሚሉ ኣይጠፉም።

ፓተንት ለማስተካከል

ፓተንት (Patent) ኣንድ ሰው ጥቅም ያለው ኣዲስ ነገር ወይም ግኝት ሲያቀርብ ከመንግሥት ለተወሰነ ጊዜ የሚሰጥ የባለቤትነት መታወቂያ ነው። በፓተንት የተጠበቀን ግኝት ያለባለቤቱ ፈቃድ መሥራት፣ መጠቀምና መሸጥ ክልክል ነው። ምሳሌ፦ እ.ኤ.ኣ. በ1878 የ“ቅውኽርትይ”ን (QWERTY) የእንግሊዝኛ የታይፕ መሣሪያ ለፈጠረው ክሪስቶፈር ሾልስ ቍጥሩ 207,559 የሆነ የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንት ሲሰጠው የእጅ ስልክ በ1973 ለፈጠረው ማርቲን ኩፐር ቍጥሩ 3,906,166 የሆነ የኣሜሪካ ፓተንት ተሰጥቷል። በ2015 ግዕዝ በኮምፕዩተር ለተከተበበት ግኝት ቍጥሩ 9,000,957 [968] የሆነ ለዶክተር ኣበራ ሞላ በዩናይትድ እስቴትስ መንግሥት የባለቤትነት መታወቂያ መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ተሰጥቷል። የፓተንቱ ስም፣ ቍጥር፣ ፈጣሪና የተሰጠበት ቀን ይታተማል። [969] (የኢትዮጵያም ፓተንት ለዶክተሩ በሦስት ወራት ውስጥ እንደሚሰጥ ጥቅምት ፳፱ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም. ተጽፏል።) [970] ይህ ኣብሻ በሚል ስም የታወቀው ግኝት ግዕዝ በኮምፕዩተርና ከመሳሰሉት ከኣንድ ገበታ በኣንድና ሁለት መርገጫዎች እንዲከተብ የኣስቻለ መደብ ነው። ለግዕዝ ፊደልም የመጀመሪያው ፓተንት ነው። [971] [972] ፓተንት ለፈጣሪው የሚሰጠው ዕውቀቱን ለሕዝብ ስለኣሳወቀ ሌሎች ያለፈጣሪው ፈቃድ እንዳይጠቀሙበት መከላከያ ሲሆን የመለያ ቊጥር ይሰጠዋል። ኣንድ ሰው ፓተንት ኣለኝ ሲል በስሙ ወይንም በፓተንቱ ቍጥር በመፈለግ ማረጋገጥ ይቻላል። ምሳሌ እዚህ፦ [973] የግዕዝ ፓተንት ተሰጠ ማለትም ኣሜሪካ ግኝቱን ኣጣርቶ ለዓለም በማሳወቅ ስለግኝቱ ኣተመ እንጂ ፊደሉ ለኣሜሪካ ተሰጠ ማለት ኣይደለም። የግዕዝ ፊደል ቴክኖሎጂ በፓተንት የተጠበቀ ስለሆነ የግኝቱን ፈጣሪ መብት ማክበርና ማስከበር ከሕዝቡና መንግሥት ይጠበቃል።

የግዕዝ ፊደል ሁለተኛ የዩናይትድ እስቴትስ የባለቤትነት ማሳወቂያ በቅርቡ ኣግኝቷል። [974] ዶክተር ኣበራ ሞላ ቍጥሩ ዘጠኝ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰላሳ ሦስት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ ሁለት የሆነ ኣዲስ የዩናይትድ እስቴትስ የባለቤትነት ማሳወቂያ (ፓተንት) ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. ተሰጣቸው። ይህ ኮምፕዩተሮች፣ የእጅ ስልኮችና ተመሳሳይ መሣሪያዎች ውስጥ የእንግሊዝኛ ፊደላት ከሚከትቡበት ኣንዳንድ ዘዴዎች ጋር የተቀራረበ ነው።

በቅርቡ ኣንድ የኤውሮጳ ኩባንያ ከጤፍ ኣጠቃቀም ጋር የተያያዘ ፓተንት ስለኣገኘ ኢትዮጵያውያን ኣልተደሰቱም። [975] [976] ዶ/ር ኣበራ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው በፓተንቶች ባይጠብቋቸው ኖሮ ኢትዮጵያ ከማትወጣበት ጣጣ ትገባ እንደነበረ በሚገባ የተረዱ ምሁራን ኣሉ። የዶክተሩን ግዙፍ ውለታዎች ከግማሽ ደርዘን በላይ የሆኑ ድርጅቶች በሽልማት ሲያበረታቷቸው [977] የኢትዮጵያን ቅርስ፣ ፊደልና ቋንቋዎች በኣዳዲስ ቴክኖሎጂ እንደጠበቁ ዛሬም ያልተገነዘቡ ኣሉ። የዶክተሩ ድካም ኣንዱ ምክንያት የኢትዮጵያውያን በፊደላቸው የመጠቀም መብት እንዳይወሰድባቸው ነው።

ኣንድ ፓተንት የኣለው ፈጣሪ በፈጠራው ላይጠቀም ወይም ውጤቱን ላይሸጥ ይችላል። ቴክኖሎጂ ዓለምን ስለኣቀራረበና በፍጥንት እያደገ ስለሆነ ፓተንት ማግኘት ቀላል ነገር ኣይደለም። በፓተንት የሚጠበቅ ግኝት መጀመሪያ ለመንግሥት እንጂ ለሕዝብ መቅረብ የለበትም። በግዕዝ ፊደል ለብዙ ሺህ ዓመታት ስንጠቀም ስለነበረ ኣጠቃቀሙም ሆነ ፊደሉ ኣዲስ ነገር ኣይደለም። ዶክተሩ የፓተንትን ጥቅም ቀደም ብለው ያውቁ ስለነበረ ቴክኖሎጂው እንደጀመረ በመረዳትና በማበልጸግ የሠሩት በሌሎች እንዳንቀደም ነበር። ቴክኖሎጂውንም የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር እንደሚጋሩም በኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ለመንግሥት በጽሑፍ ቢገለጽም ስላልተባበሩ መብታቸውን ለማስጠብቅ ወደ ኣሜሪካ መንግሥት ስለተመለሱ ኣሜሪካም የኢትዮጵያ ባለውለታ ናት። ዶ/ር ኣበራ የግዕዝ ፓተንት ኣገኙ ማለት ሰዉ በፊደሉ እንዳይጠቀም ተደረገ ማለት ኣይደለም።

ሌላ የፓተንት ጥቅም ሌሎች ዓዋቂዎች ቀደም የኣሉትን እየጠቃቀሱ በማሻሻል ኣዳዲስ ፈጠራዎችን እንዲፈጥሩ ነው። የፓተንቶች በሌሎች መጠቀስ ለግኝቱ ፈጣሪ፣ ኩባንያና ኣገርም ክብር ነው። ለምሳሌ ያህል የዶ/ር ኣበራ ፈጠራዎች ከደርዘን በላይ የዓለም ፓተንቶችና ማመልከቻዎች ውስጥ ተጠቅሰዋል። የፓተንት መረጃዎችም ውስጥ ከግኝቱ ጋር የተያያዙ ጠቃሚ ሥራዎች በፈጣሪዎቹና መርማሪዎች ይጠቀሳሉ። በዶ/ር ኣበራ ሞላ ስምና በብቸኝነት እስከኣሁን (እ.ኤ.ኣ. 2018) የተሰጡዋቸው ፓተንቶች ቍጥር 9 ደርሰዋል። በኣሜሪካ ፓተንት የሚሰጠው ሰው ነዋሪነት (Citizen) እንጂ ዜግነት (Nationality) ኣይመዘገብም። ቍጥሩ 10,067,574 የሆነ ሦስተኛ የዩናይትድ እስቴትስ የግዕዝ ፓተንት በቅርቡ ለዶክተሩ ተሰጥቷል። [978] በቅርቡም ኣራተኛ የዩናይትድ እስቴትስና ሦስት የኢትዮጵያ ፓተንቶች ለዶክተሩ ተስጥተዋል።

ዶክተር ኣበራ ሌሎች ፓተንቶች እንዳሏቸው ቀደም ብሎ ተጠቅሷል። [979] [980] እንዶድ ትላትልን እንደሚገድል በደረሱበት ትልቅ ኣስተዋጽዖዋቸው የኣሜሪካ ፓተንት በማግኘት የታወቁት ሌላው ኢትዮጵያዊ ዶ/ር ኣክሊሉ ለማ ናቸው። የኣሜሪካ ፓተንቶች ያሏቸው ኢትዮጵያውያንም እነዚህ ብቻ ኣይደሉም። የመጀመሪያው የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንት ከተሰጠበት 1790 ኤ.ዲ. ጀምሮ የኣሉት [981] ኢንተርኔት ላይ ይገኛሉ። ፓተንቶቹ ለቀለሞቹ ስለሆኑ ዶክተሩ መብቱን ያስከበሩት ለኢትዮጵያና ኤርትራ ፊደላት ነው። የዶ/ር ኣበራ ሞላ ፓተንቶች የኣማርኛ ታይፕራይተርን ስለማይመለከቱ ከእነሱ ጋር ግንኙነት የላቸውም።

የፓተንትና ኮፒራይት መብቶች የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ ያህል የዶክተሩ የሞዴት የዩናይትድ እስቴትስ ኮፒራይት መብት እዚህ ኣለ። [982] የግዕዝ ፊደል ከተለያዩ መብቶች ጋር በተያያዙ ተጠቃሚዎቹ እንዲጠቀሙ የመብት (Copyright)፣ ንግድ ምልክት (Trademark)፣ ተመዝግቧል ምልክት (Registered)፣ የመሳሰሉትን ፈጥረው በፓተንታቸውም ስለኣስተዋወቁ በዓማርኛ መጠቀም ተጀምሯል። የግዕዝ ፊደል የእጅ ስልክ ትክክለኛ ሳይንሳዊ ቴክኖሎጂ ኣጠቃቀሞች ዘዴዎቹን ለፈጠሩት ለዶ/ር ኣበራ ሞላ ቍጥራቸው 9000957፣ 9733724፣ 10067574 እና 10133362 በሆኑ የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንቶች ተሰጥተዋል። ይቀጥላል...።

የግዕዝ ኣልቦ ኣኃዝ ምልክት ለማስተካከል

ግዕዝን ዲጂታይዝ ሲያደርጉ ዶ/ር ኣበራ ሞላ ለዓለም ከኣበረከቷቸው ግኝቶች መካከል የግዕዝ ኣልቦ ወይም ዜሮ ቍጥር ምልክት (Ethiopic Zero Symbol) መፍጠር ኣንዱ ነበር። [983] [984] [985] በእዚህ ግኝት የተነሳ አንደጥቂት ባለ ኣኃዝ የዓለም ፊደላት ግዕዝ ኣዲስ ባለ ኣሥር ቤት (Base Ten) የኣኃዝ ቀለሞች ኣሉት። [986] [987] [988] [989] እነዚህም ኣዲሱ የኣልቦ ኣኃዝ ምልክትና የሚከተሉት ከኣንድ እስከ ዘጠኝ የኣሉት የግዕዝ ቍጥራዊ ኣኃዞች ናቸው። የዘጠኙ ቍጥሮች መልኮች ከፊደላውያኑ ጋር ኣንድ ዓይነቶች ቢሆኑም የኣሥሮቹ ቍጥራዊ ኣኃዞች ዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጓቸውን ሃያ የግዕዝ ቍጥሮችና በኋላም በዩኒኮድ ዕውቅና ያገኙትን የእነዚህኑ ሃያ ፊደላዊ ቍጥሮቻችን መብቶችና ኣጠቃቀሞች ኣይመለከትም። ኣዲሶቹ ኣሥር ቍጥራዊ ኣኃዞች የዱሮዎቹ ሃያ ቍጥሮች ላይ የተጨመሩ ሆነው በኣጠቃቀማቸው የተለያዩ ናቸው። ግዕዝ ወደ ዩኒኮድ ከመግባቱ በፊት ዘጠኞቹና ኣልቦ በቊጥራዊ ኣኃዝነት ከኣራተኛው ፊደል በዶክተሩ የግዕዝ መክተቢያዎች ሥራ ላይ ውለዋል። የግዕዝ ኣልቦ ኣኃዝ ከሞዴት 480 ቀለሞች ኣንዱ መሆኑና መርገጫው እዚህ ኣሉ። [990]

የኣልቦ ኣኃዝ ዋና ጥቅሞች ሁለት ናቸው። ኣንደኛው በቍጥርነት (Numeric) ሲሆን ሌላው ስፍራ በመያዝ (Positional) ነው። የግዕዝ ኣልቦና ቍጥሮች ኣስፈላጊ ናቸው። ፩. ኣልቦ የታወቀ ቍጥር ስለሆነ የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች በፊደላቸው የማያውቁበት ምክንያት የለም። ፪. የኣልቦ ስፍራ መያዝ ጥቅም በእንግሊዝኛው ዜሮ ለማስረዳት ያህል 2016 እና 201 ሲጻፉ በየተራ (Respectively) ምዕትና ዓሠርቱ ቤቶች ውስጥ ቍጥሮች እንደሌሉ ለማሳየት ነው። 2016 ከ201 የሚለየው በዜሮ ስፍራ ኣያያዝም ነው። ፫. እንደ ግዕዝ የኣሉ የጥንት ፊደላት የኣልቦ ጉዳይ በሚገባ ስለኣልገባቸው የቍጥር ምልክቶችን ከኣንድ ጀምረዋል። [991] [992] የዜሮ ምልክት ጥቅም በሕንዶች ተደርሶበት ከሺህ ዓመታት በላይ ሥራ ላይ ቢውልም ኢትዮጵያውያን እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ሳይጠቀሙበት ቆይተዋል። [993] የማተሚያ መሣሪያ ኢትዮጵያ ውስጥ ለግዕዝ ጥቅም ላይ በዋለባቸው መቶ ዓመታት ውስጥና ከአዚያ በፊትም የእንግሊዝኛውን (ኣረብኛ) ዜሮ ተጠቅመዋል። ፬. ግዕዝ ወደ ኮምፕዩተር ሲገባ እያንዳንዶቹ ቍጥሮቹ የቀረቡት በፊደልነት ስለሆነ ኮምፕዩተር ሁሉንም የግዕዝን ቍጥሮች በኣኃዝነት ኣያውቃቸውም። ፊደሉ በኮምፕዩተሮችንና ተመሳሳይ መሣሪያዎች በሚገባ እንዲጠቀም የጎደለበት የኣልቦ ኣኃዝ ተሠርቶ ከዘጠኞቹ ኣኃዞች ጋር ተገቢ ሥፍራዎች ውስጥ መቅረብ ይኖርባቸዋል። ስለዚህ ኣዲስ ኣሥር ቍጥሮች ስለተጨመሩ ፊደሉ ሠላሳ ኣኃዞች ኣሉት። ዶክተሩ የኣልቦን ቍጥር መልክ የኣቀረቡትም ኣሁን ኣይደለም። [994] [995] የግዕዝ ኣልቦ ሞዴት፣ ኢትዮወርድና ግዕዝኤዲት ፕሮግራሞች ኣራተኛው ፊደል ውስጥ ቀርበዋል። ኣዲሶቹ ኣሥር የግዕዝ ኣኃዛት ሥራ ላይ የሚውሉት በተግባር የእንግሊዝኛው ኣሥር ቍጥሮች ኣማራጭ በመሆን ነው። የኣዲሶቹ ኣሥር ቍጥሮች ኣጠቃቀም ከሃያዎቹ የተለየ ስለሆነ መለየት እንዲቻል ኣዲሶቹን “ኣበራ” ማለት ይቻላል። ኣዲሶቹን በቅርጽም መለየት እንዲቻል ትንሽ ለውጥ ማድረግ ሳይጠቅም ኣይቀርም፦ ምሳሌ ወንበሮቻቸውን ማንሳት።

፭. ግዕዝ ወደ ኮምፕዩተር ሲገባ ከዶ/ሩ ኣሥር ኣኃዛት በስተቀር ኣሥራ ኣንዶቹ የቀረቡት በፊደልነት ነበር። ከኣሥር እስከ መቶ የኣሉትንም የመደቡት የሰባተኛው ፊደል ኣኃዞች መርገጫዎች ላይ በፊደልነት ነበር። ይህ ስንጠቀምባቸው የነበሩትን ፳ የግዕዝ ቊጥሮች ኣጠቃቀሞችንም ኣልቀየረም። በኋላም ሃያዎቹ ወደ ዩኒኮድ የገቡት በፊደልነት ነበር። [996] ፮. የግዕዝ ኣልቦ ኣኃዝ ሥፍራው የቍጥሮች መካከል በመሆን ነው። ከዜሮው በላይ በኣሉት ቍጥሮች ልክ ከዜሮ በታችም ኣሉ። ፯. ዶክተሩ የግዕዝን ዜሮ ፈጥረው የጨመሩት ቍጥሮቹ ኣልቦን ስለሌላቸው እንደሮማ (Roman) ኣኃዛት ለሂሳብ ሥራ ኣይጠቅሙም ተብለው እንዳይዳከሙም ነው። ፮. ኮምፕዩተር የሂሳብና የጽሕፈት መሣሪያ በመሆኑ ግዕዝ ዜሮ ቍጥርን ስለሌለው ፈጥረውለት ዶክተሩና ሞዴት፣ ኢትዮወርድና ግዕዝኤዲት ፕሮግራሞቻቸውን የገዙ ሲጠቀሙበት ቆይተዋል። የቍጥሮችን ስፍራዎች ዩኒኮድ ለእንግሊዝኛ ስለመደበ ግዕዝ ወደ ዩኒኮድ ሲገባ የግዕዝን ኣኃዞች ከላቲኑ ጋር መጠቀም ስለኣልተቻለ የፊደላት ስፍራዎች ተሰጥተዋቸዋል። የግዕዝን ኣልቦ የኣለው የግዕዝ ኣሥር ቊጥራዊ ኣኃዛት ስፍራዎቹን ከእንግሊዝኛ ጋር መጋራት ይችላሉ። ፯. የግዕዝ ዜሮ ስለሌለ የጥንት ኢትዮጵያውያን ሂሳብ ኣያውቁም ወይም ኣይችሉም ማለትም ኣይደለም። የመደመር፣ መቀነስ፣ ማባዛትና ማካፈል ዘዴዎች ምሳሌዎች እዚህ ኣሉ። [997] [998] [999] [1,000] ፰. የግዕዝ ፊደል ኣልቦ ቍጥርን ኣልነበረውም እንጂ ኣስተሳሰቡን ኣልተጠቀምበትም ማለት ኣይደለም። ኣንድ ስንዝር ሲለካ የመነሻው የኣውራ ጣት ስፍራ በቍጥር ሲገለጽ ኣልቦ ነው። የኣልቦ ኣጠቃቀሞች ዘመን መቍጠሪያችን፣ ኮከብ ቆጠራና ሌሎችም ውስጥ ኣሉ።

፱. በግዕዝ ኣልቦ ምልክት መፈጠር የተነሳ ኢትዮጵያ ለዓለም ኣዲስ የቍጥር ኣኃዝ ኣበርክታለች። በግኝቱ መጠቀምና ማስተዋወቅ የኢትዮጵያውያን ኃላፊነት ነው። ከሠላሳ ዓመታት በላይ ሥራ ላይ የዋለ ኣኃዝና ፓተንቶችም ውስጥ የቀረበ በመሆኑ ከማተሚያ ቤት ጎደሎ ፊደሉና የታይፕራተር ቅነሳ ኣስተሳሰብ መላቀቅ ያስፈልጋል። ፲. ዶ/ሩ የግዕዝን ኣልቦ ምልክትና ኣጠቃቀም ስለኣቀረቡ የግዕዝን ሃያ ኣኃዞች የኣጠፉ የሚመስሏቸው ኣሉ። ፲፩. ኣንዳንድ ሰዎች ፊደሉ እንከን የሌለው የእግዚኣብሔር ስጦታ ነውና ኣትነካኩት ይላሉ። የዶክተሩ ገለጻ ሳይንስ [1,001] እንጂ እምነት ኣይደለም። ፲፪. ዶክተሩ የግዕዝን ኣልቦ ከኣቀረቡ ከኣሥር ዓመታት በኋላ ለእኔም ታየኝ የእሚል ኣንድ ኢትዮጵያዊ ዩናይትድ እስቴትስ ኣለ።

፲፫. በኣሁኑ ጊዜ ነፃው፣ የሚሸጠውና የቁሱ ግዕዝኤዲት ውስጥ የኣሉት የግዕዝ ኣልቦና ቍጥሮች በኣኃዝነት ኣይሠሩም። የኣልቦውም ኣቀማመጥ ጊዜያዊ ነው። ፲፬. ኣልቦ ለረቀቁ የሂሳብ ሥራዎችም ኣስፈላጊ ነው። ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፊዚክስ ስማር ኣልቦ ኣልቦ መሆኑን ማረጋገጤን ኣስታውሳለሁ። ፲፭. ግዕዝ ኣገር በቀል ፊደል ሆኖ ሳለ ለቅኝ ተገዥዎቻው ተሰጥተዋል። [1,002] ግዕዝ የኣልቦን ኣኃዝ የኣልነበረው ከኣምስት ግኝቶቹ ኣንዱ ኣኃዝነት ስለነበረ ሳይሆን ኣይቀርም። ፲፮. የጥንት ግብጻውያን በኣኃዞቻቸው ማባዛትን ከኢትዮጵያውያን ሳያገኙ ኣልቀሩም። [1,003]

፲፯. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣደረግን የሚሉትን ኣንዳንድ ዋሾዎች ከኣሳጧቸው መካከል የግዕዝ ኣልቦ ኣለመኖሯቸው ኣንዱ ነው። ምክንያቱም በታይፕራይተር ኣጠቃቀም ሥራ ላይ ማዋል የሚቻለው የላቲኑን ኣኃዞች ብቻ ስለሆነ የዶክተሩን የኣልቦ ኣኃዝ ኣስተሳሰብ ኣልደገፉም። ፲፰. በነገራችን ላይ የመጀመሪያዎቹ የላቲን ካፒታል ቀለሞች የግዕዙን ኣኃዞች የመሰሉት እያንዳንዶቹ ቀንና ደራሲ በሌለው ጽሑፍ ሊያሳምኑን በመፈለግ ምንጩ የግሪክ ሳይሆን ኣይቀርም እንደሚሉት ሳይሆን [1,004] ገልባጮቹ ግሪኮች ሳይሆኑ እንዳልቀረ መረጃ ኣለ። እዚሁ ጽሑፍ ውስጥ መጨረሻ ላይ መቀየሪያ ተብለው የቀረቡ ኣሉ። ሥራው ጥሩ ሆኖ ሳለ የቀረበው የኣረብኛን የኮምፕዩተር ቍጥሮች ወደ ግዕዝና ግዕዙን ወደ ኣረብኛው ያስቀይራል ተብሎ ነው። ዩኒኮድ ውስጥ የኣሉት የግዕዝ ቍጥሮች ፊደል እንጂ በኮምፕዩተር ወግና ኣሠራር ቍጥሮች ስለኣልሆኑ ለኮምፕዩተር ሂሳብ ሥራ የተዘጋጀ ኣለመሆኑ መታወቅ ኣለበት። ኣሁን በኣለው ወግና ኣሠራር ኮምፕዩተር በግዕዝ ኣኃዞች እንዲጠቀም ዶክተሩ ከብዙ ዓመታት በፊት የፈጠሩት የተሻለና ዘለቄታ የኣለው ዘዴ ነው። ፲፱. ግዕዝ ኮምፕዩተራይዝ ከተደረገ በኋላ ለትላልቆቹ ኣኋዞች የተለያዩ ቀለሞች መፍጠር የሞከሩ ኣሉ። ምሳሌ [1,005] ። ቍጥሮችን ከኣልቦ እስከ ዘጠኝ በኣሉ ቀለሞች መጠቀም ሳይንሳዊ ነው። ስለዚህ ኣዲስ ተጨማሪ የግዕዝ ኣኋዞችን መፍጠርን ዶክተሩ ኣያበረታቱም። [1,006] በእዚህ ኣጋጣሚ ዶክተሩ ማሳሰብ የሚፈልጉት ኣንዳንድ ፀሓፊዎች ከሌሎች የኣገኙትን ዋቢ ኣድርጎ የማቅረብ ጥቅምና ኣስፈላጊነት መገንዘብ ነው። ዋቢ የሌለውን ጽሑፍ በዋቢነት መጠቀም ኣስቸጋሪ ነው። ፳. ኣልቦን ጨምሮ የእንግሊዝኛውን የኣኃዞች ኣጠቃቀም በተለይም ኣኃዞች በቃላት ሲገለጹ ጠንቅቆ ማወቅ ለትርጕም ጠቃሚ ነው። [1,007]

፳፩. በዓማርኛ የጽሕፈት ሥርዓት ውስጥ የሒሳብ ምልክቶች ኣለመገኘታቸው ችግር ነው የሚሉ ኣሉ። [1,008] ከሒሳብ ምልክቶቹ ይልቅ የግዕዝ ኣልቦ ኣኃዝ ምልክት ኣለመኖር ነበር ችግሩ። ምንም እንኳ የዜሮ ምልክት በቊጥሩ ስርዓት ውስጥ ባይኖርም፣ የዜሮ ጽንሰ ሐሳብ ግን ለብዙ መቶ ዓመታት አልቦ በሚለው ቃል ውስጥ ተካቶ እናያለን፣ በተለይ የማካፈል ስሌት ውጤቶች ውስጥ። [1,009] ፳፪. የዶክተሩ ኣሥር ኣዳዲስ የግዕዝ ቍጥራዊ (Numeric) ኣኃዞች ከኣንድ እስከ ዘጠኝ ከኣሉት የዩኒኮድ መደብ ውስጥ የገቡት ዘጠኙ ጥንታዊ ፊደላዊ (Alpahbetic) ኣኃዞች እንዲለዩ በቅርቡ ዶክተሩ መቀመጫዎቻቸውን ኣንስተዋል። ይህ ከግዕዝ ቀለሞች ጠባይም ጋር የሚሄድ ነው። ምክንያቱም ቍጥራዊና ፊደላዊ ኣኃዞች ቅርጾች መጋራት ስለሌለባቸውም ነው። ኣልቦው ጥቅም ላይ እንዲውል ዶክተሩ ከ"1" እስከ "9" ተጨማሪም ኣኃዞች በመጨመር የግዕዝን ቍጥሮች ብዛት ከ፳ ወደ ፴ ከፍ ቢያደርጉም ኣሥሮቹን በቊጥርኝት በመቀጠል አንድንጠቀም ኣድርገዋቸዋል። ዶክተሩ ከዩኒኮድ በፊት የፈጠሩት የኣልቦ ቍጥራዊ ኣኃዝ መቀመጫ የኣለው ቀለም ሲሆን ከዩኒኮድ በኋላ በቅርቡ የጨመሯቸው ከኣልቦ እስከ ዘጠኝ የኣሉት መቀመጫ የሌላቸው ኣዳዲስ ኣሥር ቍጥራዊ ኣኃዛት ናቸው። ስለዚህ የዶክተሩ ኣልቦ ኣኃዞች ሁለት ዓይነቶች ናቸው። ሕዝቡ በኣማራጭነት እንዲጠቀምበት የሚፈልጉትም በኣዲሶቹ ኣሥሮቹ ቊጥራዊ ኣኃዞች ነው። እነዚህ ግኝቶችና ኣጠቃቀሞቻቸው በፓተንት ማመልከቻቸውም ተጠቅሰዋል። ዶ/ሩ GeezEdit Amharic P ፊደል ውስጥ የኣቀረቡት የግዕዝ ኣልቦ ዩኒኮዱ ውስጥ እንደኣሉት ኣኃዞች ፊደላዊ ነው። ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ዶክተሩ ከኣረቡ ሌላ ለኣሥሩ ኣኃዛዊ ቍጥሮች ከሰባት በላይ ምርጫዎች ሲኖራቸው ታይፕራይተሩ በኣንድ የእንግሊዝኛ ፊደል ምትክ የቀረበ ቴክኖሎጂ ስለሆነ ለኣንድም ግዕዛዊ ኣኃዝ ስፍራ ኣልነበነውም። የኣማርኛ ታይፕራይተር ኮምፕዩተራይዝድ ሲደረግ ለፊደላት የነበረው 128 ስፍራዎች ብቻ ስለነበሩና ለኣማርኛም በቂ ቦታዎች ስለኣልነበሩት ግዕዝን በታይፕራተር ዲጂታይዝ ኣደረግን የሚሉት ፊደሉንና መጻፊያውን የኣልነበራቸው ዋሾዎች ጭምር ናቸው። ፳፫. ለግዕዙ ግኝት ቀለም ቅርፅ የተጠቀሙት በእንግሊዝኛ እዝባራዊ ኣልቦ (Slashed zero) የሚባለውን ነው። [1,010] ከላቲኑ “o” (“ኦ”) ቀለም እንዲለይ የላቲኑም ኣልቦ ጠበብና ረዘም የተደረገ ስለሆነ ቅርፁ ወደ የግዕዝ ኣራት ቍጥር (“፬”)፣ ዓይኑ “ዐ” እና ፀሓዩ “ፀ” የቀረበ ስለሆነ እንዳያምታቱ ነው። ስለ ዶክተሩ ኣልቦ ኣኃዝ ፈጠራ እስከኣሁንም ከኣልሰሙት መካከል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ይገኙበታል። [1,011] ፳፬. የግዕዝ ቍጥሮች ዩኒኮድ ውስጥ የኣሉት በፊደልነት ቢሆንም እንጠቀምባቸው። ሃያዎቹ የግዕዝ ኣኃዞች ፩/1 ፪/2 ፫/3 ፬/4 ፭/5 ፮/6 ፯/7 ፰/8 ፱/9 ፲/10 ፳/20 ፴/30 ፵/40 ፶/50 ፷/60 ፸/70 ፹/80 ፺/90 ፻/100 ፼/10,000 ናቸው። ምሳሌ፦ ሰኔ 28 ቀን 2012 ዓ.ም. ሰኔ ፳፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም.።

የግዕዝ ምልክቶች ለማስተካከል

የግዕዝ ፊደል ምልክቶቹንም (Symbols) ያጠቃልላል። በኮምፕዩተር ዘመንም ግዕዝ መሣሪያዎቹንና የእጅ ስልክ የመሳሰሉትን በሚገባ እንዲጠቀም ዶክተሩ የላቲኑን ምልክቶች በማውረስ ተጠቅመውባቸዋል። ከእነዚህም ዋናዎቹ ቍልፎች የኣሏቸው 32 ምልክቶች ናቸው። የኮምፕዩተር 42 እንግሊዝኛ ቁጥሮችና ምልክቶች ከግዕዙ ጋር ያቀረቡት ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ለግዕዝ ሥራ እንዲያገለግሉ ወስነው ከግዕዙ ቀለሞች ጋር በተመጣጠነ መልክ መሥራት ስለጀመሩ ኮምፕዩተር ገበታ ላይ ያሉት ኣጠቃቀሞች ለግዕዝም እንዲያገለግሉ ነው። ለምሳሌ ያህል “+”፣ “-”፣ “*” እና “/” የመደመር፣ መቀነስ፣ ማባዛትና ማካፈል የግዕዝ የሂሳብ ምልክቶችና ማስሊያዎችም ናቸው። የግዕዝ ምልክቶች ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ የፈጠሯቸውን ኣሥር የዜማ ምልክቶች ያጠቃልላል። [1,012] ምልክቶቹን ከቀለሞች በላይ መክተብ ከኣስቸገረ ከቀኝ ጎኖቻቸው መክተብ ይቻላል።

እንዲህም ሆኖ የላቲኑን ምልክቶች በግዕዝነት ስንጠቀምባቸው መከተል የኣለብን ኣጠቃቀሞች ኣሉ። ፩. የእንግሊዝኛው የፊደል ገበታ ላይ የኣለው የላቲንን የኮለን (Colon) ምልክት ኮምፕዩተሩ የሚያውቀው በኮለንነት እንጂ መልኩ የግዕዝን ሁለት ነጥብ ምልክት (“፡”) ስለመሰለ በነጥብነት ኣይደለም። ግዕዝ የእራሱ ኮድ የኣለው በኣለ ሁለት ነጥብ የባዶ ስፍራ ምልክት ስለኣለው ኮለንን በባዶ ስፍራ ምትክ መጠቀም ትክክል ኣይደለም። ፪. ሁለት፣ ሁለት ነጥቦች (“፡፡”) (Ethiopic Spaces) የኣራት ነጥብ ምልክት (“።”) (Period) ኣይደሉም። ስለዚህ ሁለት፣ ሁለት ነጥቦች በኣራት ነጥብ ምትክ መጠቀም ትክክል ኣይደለም። ፫. ሁለት ኮለኖችም (Colons) (“::”) የኣራት ነጥብ ምልክት (“።”) ኣይደሉም። ስለዚህ ሁለት ኮለኖችም በኣራት ነጥብ ምትክ መጠቀም ትክክል ኣይደለም። ሁለት፣ ሁለት ነጥቦች በዓማርኛ የመኪና መጻፊያ (ታይፕራይተር) ዘመን በኣራት ነጥብነት ስንጠቀምባቸው የነበረው ዓላማው ጽሑፉን ወረቀት ላይ ኣስፍሮ ማንበብ ብቻ ስለነበረ ነው። በኮምፕዩተር ግን የቀለሙ ኮድ ወይም ቍጥር ስለሚሰፍር ኣጠቃቀሞቹ የተለያዩ ናቸው። ይህን ኣጠቃቀም ኣለማወቅ ኣራት ነጥብ የሌላቸው ጽሑፎችን ያስከትላል። ኣራት ነጥብ የሌሏቸው ጽሑፎችን መተርጐምም ያስቸግራል። ሌሎች የተግዳሮት ምንጮች የዶክተሩን የመርገጫዎች ኣመዳደብ እናሻሽላለን ብለው የላቲኑን የምልክት መርገጫዎች ለግዕዝም ተመሳሳይ ኣጠቃቀሞች የኣቀረቡትንም በመጠኑ ይመለከታል። ስለዚህ ኣንዳንድ ኢትዮጵያውያን ዓማርኛውን ኣራት ነጥብ በሌለው ከመጻፍ እንዲቆጠቡና ኣራት ነጥብ በሌለውም መጻፊያ እየጻፉ ጊዜያቸውን ከማባከን ቢቆጠቡ ይጠቅማል። ፬. ስለ ኣራት ነጥብ የተሳሳተ ኣጠቃቀም ተጨማሪ መረጃ የሁለት ነጥቦቹ ሁለት እየተከፈሉ ግማሾቹ ወደ ኣዲስ መስመር መዞር ነው።

፭. በኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች ኣጠቃቀም ምልክቶች በቀለማት እንጂ በባዶ ስፍራዎች መቀደም የለባቸውም። ፮. ዶክተሩ በእንግሊዝኛው የንግድ ምልክት (“TM”) ምትክ የግዕዝ የንግድ ምልክት (“ንም”) ምልክት ፈጥረው ሲጠቀሙበት ቆይተዋል። ፯. ጮሌ ስልኮችን ወደጎን ኣዙሮ መጠቀም ያፈጥናል። በተለይ ይኸን ኣጠቃቀም እንደእንግሊዝኛው ለማቀላጠፍ ለሳድሳን መዝጊያ ዶክተሩ የ”ዠ“ን መርገጫ ለግራ ኣውራ ጣት እንዲጠቅምም ኣድርገዋል። ፰. የግዕዝ የነቁጥ ምልክት ተረስቶ ዩኒኮድ ውስጥ ስለኣልገባ መጨመር ይኖርብናል። ምክንያቱም ምልክቱ ከሌሎች የቁምፊው ቀለሞች ጋር እንዲሄድ መሠራት ስለኣለበት ነው።

፱. ኣሥሩ የያሬድ ምልክቶች ብዙ ሰዎች ከኣሏቸው የዶክተሩ ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ፊደል ውስጥ ኣሉ። እያንዳንዱም የሚከተበው በሁለት መርገጫዎች ነው። ፲. በተሳሳቱ ኣራት ነጥቦች የተጻፉ ኣስተማማኝ የኣልሆነ ጽሑፎች ኣሉ። ከእዚህ ጽሑፍ ኣንድ ሁለት ኣንቀጾችን ኮፒ ተደርገው http://www.freetyping.geezedit.com ገጽ ላይ ቢለጠፉ ችግሮቹን መመልከት ይቻላል።

ግዕዝና ኦሮምኛ ለማስተካከል

ግዕዝ በዶክተር ኣበራ ሞላ ኮምፕዩተራይዝድ ሆኖ ለዓማርኛ ተመድበው ከተረፉት ሦስት መርገጫዎች ኣንዱ ለኦሮሞ (Oromo) ሲሆን ሌላው ለትግርኛ ተሰጥቶ የቀረው ለኣገው/ቢለን ሥራ ላይ ውለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. የመንግሥት ለውጥ ጊዜ የኣንድ ድርጅት ኦሮሞ ምሁራን ተሰብስበው ከግዕዙ ይልቅ ላቲን ይበጀናል በማለት ግዕዙን (Ethiopic Oromo syllabary) ስለተዉት የሚከተሉትን መጋራት ሳይጠቅም ኣይቀርም። (ለኦሮሞው “ዸ” ፊደል የላቲኑ የመቀነስ ምልክት መርገጫ በዶክተሩ መመደቡን እዚህ ከቀኝ ጎን ከኣሉት ሥዕሎች “ModEth 1989 ሞዴት የፊደል ገበታ ፬፣ ፲፱፻፹፪ ዓ.ም.” የሚለውን ማስተዋል ይጠቅማል። [1,013] [1,014]) ቁቤ ኦሮምኛን በላቲን ፊደል የመክተቢያ ዘዴ ነው።

፩. ጥንትም ቢሆን ፊደላት በእጅ ጽሑፍ ሲጻፉ ላቲን ከግዕዙ በፍጥነት የተከተበበት ጊዜ ኣልነበረም። ምክንያቱም ግዕዝ ኣንድን ድምጽ በኣንድ ቀለም ሲያሰፍር ለኣብዛኛው የላቲን ድምጾች ሁለት ቀለሞች ስለሚያስፈልጉት ነው።

፪. የላቲንና ግዕዝ ቀለሞች (ኦሮምኛውን ግዕዝ ጨምሮ) በማተሚያ መሣሪያዎች ሲከተቡ የሁለቱም ቀለሞች መረጣዎች ኣጠቃቀሞች እኩል ነበር። በእዚህ ዘዴ በግዕዝ ቋንቋ በ1513፣ [1,015] [gallery1/0/] ኦሮምኛ ዓማርኛ መተርጐሚያ (Lexicon) በ1850 ግድም በኣቶ ሓብተ ሥላሴ ታትሟል። [1,016] መጽሓፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ የመተርጐሙንም ሥራ በማስፋፋት ከሌሎች የቋንቋው ተናጋሪዎች ጋር (ዋሬ፣ ሩፎ፣ ሾለን፣ ጀገን እና ገብረሚካኤል) በመተባበር ሙሉውን ኣዲስ ኪዳን ወደ ኦሮምኛ ተርጕመው በሰኔ 1862 ዓ.ም. ኣገባደዱ። ይህም ትርጕማቸው ለኦሮምኛ ሥነጽሑፍ የመጀመሪያው ኣዲስ ኪዳን መሆኑ ነው። ከጥቂት ዓመታት በኋላም ሚስዮኑ ክራጵፍ (J.L. Krapf) በ፲፰፻፸፩ ዓ.ም. በራሱ ስም ያሳተመው ይህንኑ የነኣለቃ ዘነብን ፲፰፻፷፪ ዓ.ም. ሥራ “ቁልቁሎታ መጻፎታ ከኩ ሐረዋ” ነበር። [1,017] ኣለቃ ዘነብ ወደ ፲፰፻፸ ዓ.ም. ግድም የ“ኦሮምኛና ኣገውኛ መዝገበ ቃላት” ጽፈዋል ይባላል። የኣስቴር ጋኖን የትርጕም መጽሓፍ በመጠቀም በ፲፰፻፹፯ ዓ.ም. የታተመም የኦሮምኛ ሓዲስ ኪዳን[1,018] መጫፈ ቁልቁሉ በ፲፰፻፺፱ እ.ኤ.ኣ. (፲፰፻፺፪ ዓ.ም.) በቅዱስ ኦነሲሞስ ነሲብ[1,019] [1,020] እና ከእዚያም ወዲህ እንደነ በሪሳ የኣሉ ጋዜጣዎች በግዕዝ ፊደል በኦሮምኛ ታትመዋል። መጫፈ ቁልቁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በግዕዝ ፊደል በኦሮምኛ ቋንቋ የተጻፈ የምዕራብያኑ King James Version) መጽሓፍ ቅዱስ ትርጕም ነው። ቀደም ብሎም በግዕዝ ፊደል በኦሮምኛ ከቀረቡት መረጃዎች ኣንዱ ጀምስ ብሩስ የወሰደው የ1790 የኦሮምኛ ትርጕምና የኢዘንበርግ ጽሑፍም ኣሉ። [1,021]

፫. በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ የሆነው ግዕዝ እ.ኤ.ኣ. በ1987 ለገበያ ቀርቦ በማተሚያ ቤቶች ፊደላት (ሞዴት ፕሮግራም) መክተብ ስለተጀመረ ምሁራን ደስ ሊላቸውና ሳይንሱንና ቴክኖሎጅውን ማወቅና ማስተዋወቅ በተገባ ነበር። ይህ በኣለመደረጉ እ.ኤ.ኣ. በ1992 [1,022] በፕሮፌሰር ጥላሁን ጋሜታ ወደ ላቲን ለማዞር ከቀረቡት የኣማርኛ የጽሕፈት መኪናን የሚመለከቱት ጊዜ ለኣለፈባቸውና ኮምፕዩተርን የማይመለከቱ ምክንያቶች መልሶችም ነበሩ። [1,023] [1,024] [1,025] ስለዚህ በግዕዝ ፊደል በማተሚያ ፊደላት ሲጻፉ የነበሩት በኮምፕዩተር ስለቀረቡ ቴክኖሎጂው ስለተሻሻለና ስለቀለለ ጉዳዩ ይመለከተናል የኣሉት የኦሮሞ ምሁራን ሊደሰቱ የሚገባ እንጂ ወደ ላቲን የሚያስዞር ኣዲስ ምክንያት ኣልነበረም። በጊዜውም በፕሮፌሰር ባዬ ይማም በዓማርኛ መልስ ቀርቦ ፕሮፌሰር ሚንጋ ነጋሽና ፕሮፌሰር ሳሙኤል ክንዴ ወደ እንግሊዝኛ ተርጕመውታል። [1,026] ለምሳሌ ያህል ወደ ላቲን የተዞረው ብዙ የግዕዝ ፊደላትን ከማስተማር የኣነሱትን ላቲን ማስተማር ይቀልላል የሚሉ ኣሉ። የላቲኑ ፊደል በቍጥር ማነስ ዕድሜ ልክ እስፔሊንግ ማጥናትንና ኣለመጨረስን ኣስከትሏል። የግዕዝ ፊደላት ቤቶች፣ ቅርጾችና ድምጾች በወጉ የተሠሩ ውብና ግሩም ፈጠራዎች ናቸው። ለምሳሌ ያህል የካዕብ ቤት ፊደላትን ድምጾች ለማሰማት ከንፈሮችን ማሞጥሞጥ ሲያስፈልግ በቅርጽ ከግዕዙ የሚለዩት ከቀኝ ጎን መሥመር በማስጨመር ነው። የስምንተኛው ቤት ድምጾች የሚጻፉት ከግዕዙ ወይም ራብዕ ግርጌ ወይም ኣናት ላይ መስመር በመጨመር ዓይነት ነው። [1,027]

፬. ላቲን የእራሱ ችግሮች የኣሉት ፊደል ነው። [1,028] [1,029] [1,030] [1,031] በዶክተሩ ግኝት እያንዳንዱን የግዕዝ ቀለም በሁለት መርገጫዎች መክተብ ተችሏል። ላቲን ይኸን እየኣንዳንዱን የግዕዝ ቀለም በሁለት መርገጫዎች የመክተብ ችሎታ ስለሌለው ግዕዝን በግዕዝ ፊደል መክተብ ብልጫ ኣገኘ። ስለዚህ ኦሮምኛን በላቲን ፊደል መክተብ (ቁቤ) መሻሻል ኣይደለም።

፭. የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል ከሌሎቹ የግዕዝ ቀለሞች ጋር በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ [1,032] ለኣለፉት ፴፪ ዓመታት በኮምፕዩተር ቀርቦ በኋላም በዩኒኮድ ዕውቅና ቢያገኝም [1,033] ሁሉም ባይሆኑ ኦሮሞዎች ግዕዙን እርግፍ ኣድርገው ጥለው ወደ ላቲኑ ስለዞሩ የተፈጠሩት ችግሮች ቀጥለዋል። ለምሳሌ ያህል ላቲን እራሱን የሚገልጸው የኮምፕዩተሩ ገበታ ላይ በኣሉት ቀለሞች ብቻ ኣይደለም።

፮. በእጅ የጽሕፈት መሣሪያ ዘመን ታይፕራይተር ዓማርኛንና ኦሮምኛን ለማስጻፍ ስለኣልቻለ ላቲን ብልጫ ነበረው። የዶክተሩ ግኝት ለእውሸቱ (የፈጠራ) የታይፕራይተር የኣማርኛ ነገሮችና ለትክክለኛዎቹ የማተሚያ ቤቶች ፊደላት ኣጠቃቀሞች እጅግ ትልቅ ፈውስ (Breakthrough) ነበር። የታይፕራይተር ፊደል ለታይፕራይተር ሲባል የተሠራ በፍፁም ትክክለኛ በኣለመሆኑና ለብዙ ምዕት ዓመታትም በእጅ ስንጽፈው የነበረው ከኣለመሆኑም ሌላ የማተሚያ ቤት ፊደላችንም ስለኣልሆነ ከቁርጥራጮች የሚሠራውን ብጥስጥስ ዶ/ር ኣበራ የእውሸት ፊደል ይሉታል። ስለ ታይፕራይተሩ ድክመት ዶክተሩ እ.ኤ.ኣ. በ1991 [1,034] [1,035] ስለኣቀረቡ መሣሪያው ወደ ቁቤ ለመዞር ምክንያት መሆን ኣልነበረበትም። በታይፕራይተር በመቀጣጠል “ዸ”ን እና እርባታዎቹን መጻፍም ከአማርኛው የተለየ ችግር ኣልነበረውም። ቀደም ብሎም የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ሲጠቀሙቸው የነበሩት የኦሮሞ የግዕዝ ቀለሞች እየኣሉና ከእዚያም ወዲህ በኮምፕዩተር የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል በዶክተሩ መከተብ መቻልና የተጠቃሚዎች መኖር ግንዛቤ ውስጥ ሳይገቡ በንቀት ብዙ ዓመታት ባክነዋል። ቴክኖሎጂ የችግር መፍቻ እንጂ ከችግር መሸሽያ ኣይደለም። ለቴክኖሎጂ ተብሎ ፊደል መቀየርና መቀነስም ነውር ነው። ለምሳሌ ያህል እንደ እንግሊዝኛው ላቲን ዓይነቶቹ የተጻፉት ቃላት የማይነበቡበት (ለምሳሌ ይህል Write) ሳይቀነሱ ኣሉ።

፯. ቁቤ በላቲን ዋየሎች ከሚጠቀምባቸው በተሻለ ኦሮምኛ በግዕዙ ሊጠቀም ይችላል። ኦሮምኛን በፊደል ለመክተብ ከላቲኑ ቁቤ የግዕዝ ፊደል ይጠቅማል። [1,036] [1,037] [1,038]

፰. መጽሓፍ ቅዱስ በከፊል እ.ኤ.ኣ. በ1841 በኦሮሞ ቋንቋ በግዕዝ ፊደል ተጽፏል። [1,039] [1,040] እንዲሁም እ.ኤ.ኣ. በ1875 የኦሮሞ ሓዲስ ኪዳን በግዕዝ ፊደል ታትሟል። [1,041] [1,042] [1,043]

፱. በልሳነ ግእዝና በኣፋን ኦሮሞ (ግእዚፊ ኣፋን ኦሮሞቲን - Giiiziifi Afaan Oromootiin) የተዘጋጀው መጽሓፈ ቅዳሴ - ክታበ ቅዳሴ - Kitaaba Qiddaasee መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓ.ም. በኢሊሌ ሆቴል ተመርቋል። የትርጐማና የኣርትኦት ሥራው 10 ዓመታት የወሰደው ባለ ሦስት ዓምዱ ክታበ ቅዳሴ፦ የመጀመርያው ረድፍ በግእዝ ቋንቋ፣ ሁለተኛው ረድፍ በኦሮምኛ ሆኖ በግእዝ ፊደል፣ ሦስተኛው ረድፍ በኦሮምኛ ሆኖ በቁቤ ፊደል ተጽፏል ይላል ሪፖርተር ጋዜጣ። [1,044] ይህ የግዕዝ ፊደል ኦሮምኛን ኣይጽፍም ለሚሉት ማፈሪያ ነው። ስለዚህ ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን ግዕዝ ኦሮምኛን ኣይጽፍም በማለት ከጀመሩት የእውሸት ዘመቻዎቻቸውና ሕዝቡን ከማጣላትና ከመለያየት መቆጠብ ይኖርባቸዋል። ከእነዚህ ተርጓሚዎች ሌላ ለግዕዝ እድገት የሠሩ የኦሮሞ ሊቃውንት ኣሉን። [1,045]

፲. መጽሓፍ ቅዱስ ሙሉዉን ወይም በከፊል ከ፲፭፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ በግዕዝ ቀለሞች በማተሚያ ቤቶች ከታተሙባቸው ቋንቋዎች መካከል የግዕዝ ቋንቋ (ግዕዝኛ)፣ ዓማርኛትግርኛኦሮምኛ[1,046] [1,047] [1,048] [1,049] ሃዲያ[1,050] ሲዳሞ[1,051] ከንባታ[1,052] ወላይታ [1,053] እና ጌዴኦ [1,054] ይገኙበታል። መጽሓፍ ቅዱስ በሌሎች የኢትዮጵያ ቋንቋዎችም ተተርጕሟል። ለምሳሌ ጋሞ ጎፋና ዳውሮ። ስለዚህ ለዓመታት በማተሚያ ቤቶች የግዕዝ ፊደላት ሲከተብ የነበረው ኦሮምኛ ኮምፕዩተራይዝድ ሆኖ ዛሬ ሥራ ላይ እየዋለ ግዕዝ ኦሮምኛን ኣይጽፍም ማለት ሳይንስ ኣይደለም።

፲፩. በኣነሱ የኆኄያት ግድፈቶች (Spellings / እስፔሊንጎች) እና ስፍራዎች (Spaces) ማስከተብ ብልጫዎች የነበረው የግዕዝ ፊደል በዶ/ር ኣበራ ግኝቶች የተነሳ የግዕዝ ፊደል ሓሳብን በኣነሱ ጊዜያት (Times)፣ መርገጫዎች (Keystrokes) እና ገበታዎች (Keyboards) በኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች በማስከተብ ብልጫዎቹ ወደ ኣምስት ዓይነቶች ከፍ ብለዋል። ለምሳሌ ያህል “ዘ ኲክ ብራውን ፎክስ ጃምፕስ ኦቨር ዘ ሌይዚ ዶግ።” የሚለውን ዓረፍተ ነገር ላቲን በ36 ቀለሞችና በቁቤ በ45 ቀለሞች ከመክተብ ይልቅ በግዕዝ ፊደል በ24 ቀለሞች መክተብ የተሻለ ነው። ስለዚህ ግዕዝ እንኳን ከላቲኑ ቁቤ ከላቲኑ እንግሊዝኛ የተሻለ ነው።

፲፪. የቁቤ ሥርዓት እ.ኤ.ኣ. በ1992 ገደማ የተመሠረተው ኣንዱ ቀለም ኣንድን ድምጽ በመወከል ነው ተብሏል። የላቲንም ሆነ የቁቤ ቀለሞች ኣንድን ድምጽ በኣንድ ቀለም ከሚወክለው የግዕዝ ፊደል ጋር የመወዳደር ችሎታ የላቸውም። ላቲን ኣንዳንድ ድምጾችን የሚከትበው በሁለት ቀለሞች ስለሆነ ሁሉም ቀለሞች ለየብቻቸው ኣንድ ድምጽ እንዲወክሉ እንኳን ተደርጎ መጠቀም ኣይቻልም። ለምሳሌ ያህል “d” እና “h” የ“ዽ” እስፔሊንግ ስለሆኑ “ዲ” እና “ኤች”ን በሁለት ቀለምነት ጎን ለጎን ኣስቀምጦ በ“d” እና “h” ድምጽ ሰጪነት መጠቀም ኣይቻልም። ይህ ምሳሌ የሚያሳየው ቁቤ የተመሠረተው በጥቂት የኦሮሞ ምሁራን ማምታታትም ላይ መመርኰዙን ነው። ሌላ ምሳሌ ግዕዝ ዋየልና ማጥበቂያ (Long Vowels / Germination) የለውም የሚባለው ነው። [1,055] ለግዕዝ ዋየል ስለማያስፈልገውና ስለሌለው ዋየል ባያስፈልገውም መዘርዘር ይቻላል። ኣንድ ቀለም የሚበቃውን የግዕዝ ማጥበቂያ ትቶ ለኣልተሟላ ማጥበቅ ሲባል ወደ ላቲን ዋየሎች መዞር ኣያታርፍም። ለላቲን የሚያስፈልጉትን ረዣዥም ዋየሎች ግዕዝ ስለሌለው ኦሮምኛን በላቲን ለመክተብ መረጥን ለሚሉት ሰበቡ ሳይንሳዊ ስለኣልሆነና ግዕዝ ሥርዓተ ንባብ (ማንሳት፣ መጣል፣ ማጥበቅ፣ ማላላት፣ ማናበብ፣ አለማናበብ፣ መዋጥና መቍጠር) ስለኣለው [1,056] ሊታሰብበት ይገባል ይላሉ ዶክተር ኣበራ። የግዕዝ ፊደል በብዛቱ እየተወቀሰ ከእዚያ በበዙ ቀለምች መተካት ትክክል አይደለም። ቁቤ ሁሉንም የላቲን ዋየሎችንና እንዚራን (Accents) ኣልተጠቀመም። ጥናት ላይ ተመርኵዞም ኦሮምኛ ሁሉንም የዓማርኛ ቀለሞች የኣለመጠቀምም መብት ኣለው። የተለያዩ ምክንያቶች በማቅረብ የግዕዝ ፊደል ኦሮምኛን ኣይጽፍም የኣሉትን እንደተሳሳቱ ሳይጠቅሱ ኣሁንም መጥቀስ ስለጉዳዩ ኣሁንም የሚጽፉት ጥቂት ምሁራን እራሳቸውን ማረም እንዳልቻሉ ያሳያል። [1,057] [1,058] የ“መ” እና “ማ”ን እስፔሊንግ “ma” እና “maa” ማድረግ መካሰር ነው። ወደ ላቲን የተዞረው ያለበቂ ጥናትና ሕዝቡ ሳያውቅና ሳይመርጥ በእውሸት ሕዝብ መረጠው ተብሎ ነው።

፲፫. ማንኛውንም የኦሮሞ ፊደል በሦስት መርገጫዎች መክተብ ነውር ነው። ማንኛውንም የኦሮምኛ ድምጽ በሦስት መርገጫዎች መክተብ ነውር ነው። ምክንያቱም ግዕዝ በኮምፕዩተር ኣይጻፍም ተብሎ የኣማርኛ ታይፕራይተር ማጓጓዝ እንደችግር በቀረበበት ጊዜ እያንዳንዱ የኦሮምኛ የግዕዝ ቀለም በኮምፕዩተር በሁለት መርገጫዎች በዶክተሩ እየተከተበ ነበር። ምንም እንኳን ግዕዝ እንከን የማይወጣለት ፊደል ነው ማለት ባይቻልም ለኣንድ ድምጽ ኣንድ ቀለም ለመመደብና ኣንድን ቀለም ለኣንድ ድምጽ ለመመደብ የተፈጠረ ነው ማለት ይቻላል። ግዕዝ በኮምፕዩተር እየተጻፈ በፊደላዊ ፊደል በላቲን ኦሮምኛውን በበዙ መርገጫዎች መክተብ ኣሁንም ሳይንሳዊና የተሻለ ነው ማለት ለቴክኖሎጂ ሲባል እራስን ዝቅ ማድረግና ኣርቆ ኣለማስተዋል ነው። [1,059]

፲፬. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን ዓማርኛ የማጥበቂያ ምልክት የለውም የሚሏቸውን ስሕተቶች ቀጥለውበታል። ዓማርኛ መጥበቅ የኣለበትን ቃል ከማይጠብቀው የሚለይበት ዘዴዎች ኣሉት። ከእነዚህ ኣንዱ ከሚጠብቀው ቀለም ኣናት በላይ ኣንድ ነጥብ መክተብ ሲሆን ምሳሌውም በ፲፮፻፺ ዓ.ም. ላቲንና ዓማርኛ መተርጐሚያ መጽሓፍ ውስጥ ታትሟል። ለምሳሌ ያህል “ላላ‘” እና “አላላ‘” ገጽ 1 እና “መነ‘ሣት” ገጽ 50 ላይ ቀርበዋል። [1,060] ይኸንንም ኣጠቃቀም ሓዲስ ዓለማየሁ [1,061] https://en.wikipedia.org/wiki/Hiob_Ludolf] [በ“ፍቅር እስከ መቃብር” መጽሓፋቸው ኣስፋፍተውታል። [1,062]] በኣዲስ ቅርጽ ለኮምፕዩተር እንዲስማማ መጥበቅ ከኣለበት ቀለም ኋላም እንዲከተብ ተደርጎ ማጥበቂያና ማላልያ በዶክተር ኣበራ ፓተንትም ውስጥ ኣ.ኤ.ኣ. በ2009 ተጠቅሰዋል። [1,063]

፲፭. የቁቤ ዋየሎች “ኤ”፣ “ኢ”፣ “ኣይ”፣ “ኦ” እና “ዩ” (“a”፣ “e”፣ “i”፣ “o” እና “u”) ስለሆኑ በቁቤ “ክታበ”ን ከ“ኪታባ” የመለየትና ማጥበቅ/ማላላት ችግሮች ቢኖሩትም ስለ ቁቤ ማጥበቅ፣ ማላላት፣ ማስረዘምና ማሳጠር የሚጽፉም ኣሉ። ይህ በኣዲስ ፊደልነት የቀረበውንም በብዛት ከግዕዝ ፊደል የበለጠውንም [1,064] ይመለከታል። ግዕዝ ሰባት እንዚራን ሲኖረው ኦሮምኛ 10 ያስፈልጉታል የተባለው ትክክል ከኣለመሆኑም ሌላ ቍጥሩን ወደ 13 መጨመርም ስለኣላዋጣም ኣልቀጠለም። [1,065] ትክክለኛው የግዕዝ ኣጻጻፍ “ኣፋን” እንጂ “አፋን“ ኣይደለም። ኣንዳንዱ “ድ“ን በ“d“ ሌላው በ“di“ ይጽፋል።

፲፮. ይህ ግዕዝና ኦሮምኛ ሳይንሳዊ ጽሑፍ ስለ ፊደላቱ እንጂ ቋንቋዎቹን ኣይመለከትም። የኦሮሞ ቋንቋችን መዳከም ስለሌለበት ስለ ፊደል ስንወያይ ሰለ ቋንቋና ሰለኣልፈጠርናቸው ኦሮሞነት መቀላቀል ሳይንስ ኣይደለም። የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል ከሌሎቹ የግዕዝ ቀለሞች ጋር በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ ስለሆነ ለኣለፉት ፴፪ ዓመታት በኮምፕዩተር ቀርቦ [1,066] በኋላም በዩኒኮድ፣ ዩናይትድ እስቴትስና የኢትዮጵያ መንግሥታት ዕውቅና ቢያገኝም ዛሬም ሶፍትዌር ውስጥ የሉም ብለው የሚጽፉ ኣሉ። ምሳሌ፦ “በዻኔ” [1,067]

፲፯. እነ “ሸ”፣ “ቸ”፣ “ኘ”፣ “ዸ”፣ “ጠ”፣ “ጨ”፣ “ጰ”፣ እንዚራኖቹንና ሌሎች ቀለሞች የኣሉትን ለኦሮምኛ የሚያስፈልጉትን ቀለሞች ትቶ እነዚህን ወደ የሌሉት የላቲን ፊደል መዞር ሳይንስ ኣይደለም። [1,068] የእነ“ጨ”፣ “ⶸ” እና “ꬠ” እንዚራን በቁቤ መለየት ቀላል ኣይሆንም።

፲፰. የኦሮምኛ ድምጾችንና እርባታዎችን የሚወክል የፊደል ገበታ (ከኣማርኛ ታይፕራይተር፣ ዓረብኛላቲን) ለጊዜው የተሻለው ላቲን ነው በማለት በስሕተት የቁቤ ኣጻጻፍ ሥራ ላይ ዋለ። ይህ ለዓማርኛው በኣለመደረጉ ዶክተሩ በመፍትሔው የደረሱለት ለኦሮምኛው ፊደል ጭምርም ነበርና ነውም። ምክንያቱም ዓማርኛና ኦሮምኛ በትክክለኛው የግዕዝ ፊደል ለብዙ ምዕት ዓመታት ተጠቅመውበታል። [1,069] የጄምስ ብሩስና ሌሎች መረጃዎችም ኣሉ። [1,070] ስለዚህ ዓማርኛውንም ሆነ ሌሎችን ቋንቋዎቻችንን ለማይጽፈው የዓማርኛ ታይፕራይተር ሲባል ፊደሉን የተዉት ቋንቋዎች በኣንዳንድ ተናጋሪዎች ስሕተት እንጂ በግዕዝ ፊደል ሲጠቀሙ በነበሩ ኢትዮጵያውያን ስሕተት ኣልነበረም።

፲፱. በዶክተሩ ግኝቶች ከ“አ” እና “ኸ” መርገጫዎች ፲፬ የግዕዝ ቀለሞች እየተከተቡ ናቸው። [1,071] [1,072]

፳. ቁቤ በ“a”፣ “e”፣ “i”፣ “o” እና “u” በተጠቀመው ዓይነት በ“ኣ”፣ “ኤ”፣ “ኢ”፣ “ኦ” እና “ኡ” የግዕዝ ቀለሞች መጠቀም ይችል ነበር። ኣንዳንድ ኦሮሞዎች “ቢራ” በላቲን ኦሮምኛ "biirraa" ተብሎ የሚጻፈው ግዕዝ ስለማይችለውም ነው ይላሉ። በ“biirraa” ምትክ “ብኢኢርርኣኣ” ተብሎ በግዕዝ ፊደል መጻፍ ይቻላል። ስለዚህ ቁቤ የተመሠረተው ሳይንሳዊ ጥቅም ላይ ኣይደለም። “ቢ” እና “ራ” ቀለሞችን ዓማርኛ በኣራት ዓይነቶች ማለትም “ቢራ”፣ “ቢ'ራ”፣ “ቢራ'” እና “ቢ'ራ'” መጠቀም ይችላል። “ብኢርኣ” ወይም “ቢርራ”ም ኣለ። ለምሳሌ ያህል “ለቆ” የሚለውን ቃል “ለቅቆ” ወይም “ለቆ'” ዓይነቶች መክተብና ማላልያና ማጥበቂያዎች መጨመርም ይቻላል። ቁቤ ዋየሎችን ከመደራረብ በ“ዓ”፣ “ዔ”፣ “ዒ”፣ “ዖ” እና “ዑ” የግዕዝ ቀለሞች ኣጠቃቀም ምሳሌዎች ጊዜ፣ ሥፍራና ጉልበት መቆጠብ ይችል ነበር። ከኣምስት የላቲን ዋየሎች የግዕዙ “አ”፣ “ዐ” እና ሰባት እንዚራኖቻቸው የተሻለ ገላጮችና ሥፍራ ቆጣቢዎች ናችው። እዚህ የቀረቡትም መረጃዎች ዋሾ የኦሮሞ ምሁሮችን ስለሚያሳፍሩ ዝም እያሉ የተጃጃሉት እነዚያኑ ጥያቄዎች ደጋግመው ይጠይቃሉ።

፳፩. ኣንዳንድ የኦሮሞ ምሁራን ግዕዝ የኦሮምኛ ቃላትን ኣይጽፍም በማለቱ በኣለማወቅ በስሕተቱ ገፍተውበታል። ጎዸቱ፣ ቶኮፋዸ፣ ዹፌ፣ ዹጉማ፣ ጀዺ፣ ዻባ፣ ዻራርቱ፣ ባዻዻ፣ ዻዻ፣ ጄዼ፣ ዼራ፣ ዽባፍ፣ ዽባ፣ ነንዾከዼስ፣ ዿ የእንዚራኑ ምሳሌዎች ናቸው። ዓማርኛው ላይ የተጨመሩት ስምንቱ የኦሮሞ ቀለሞች “ዸ”፣ “ዹ”፣ “ዺ”፣ “ዻ”፣ “ዼ”፣ “ዽ”፣ “ዾ” እና “ዿ” ናቸው። የኦሮሞውም ላይ የተጨመረ የምኢን የግዕዝ “ⶍ” ቀለምም ኣለ።

፳፪. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን “ዻ” የግዕዝ ኦሮምኛ ቀለም በኣንድ ቀለም በሁለት መርገጫዎች ከመክተብ ይልቅ “dha” በማለት በሦስት ቀለሞችና በሦስት መርገጫዎች በኦሮምኛ መክተብ የተሻለ ሳይንስ ይመስላቸዋል። ኣንዳንድ የግዕዝ ቀለሞችን በላቲን ለመለየት ሦስትና ከሦስት በላይ ቀለሞችን መደርደር ያስፈልጋል። ግዕዝ ለኣዳዲስ ድምጾች ፊደል ሲፈጥር ቁቤ ለኣለው ፊደል ሌላ ድምጽና እስፔሊንግ በመጨመር መሻሻል ስለሚፈልግ ችግሩን ያባብሳል። ግዕዝን በላቲን እስፔሊንግ ለመጻፍ የሞከሩትም ጥቂቶቹን እስከኣሁን የኣዋጣቸው የሕዝቡ ስለቴክኖሎጂው በሚገ'ባ ኣለመረዳት ነው።

፳፫. በሚገባ ሳይታሰብበት የግዕዝ ቀለሞች በላጭነትና ጥቅሞች ሳይገለጹ ታልፈዋል። ምሳሌ፦ ግዕዝ ችግር የለውም ማለት ሳይሆን የላቲንን ቃላት እስፔሊንጎች ዕድሜ ልክ ቢማሩትም ማስታወስ ኣይቻልም። በእዚህ ላይ “ኦሮሞ” የሚለው ቃል እስፔሊንግ በላቲን “Oromo” በኦሮምኛ ቁቤ የኣለ በቂ ምክንያት “Oromoo” ነው። [1,073] [1,074] የቁቤ ላቲንና የላቲንን እንግሊዝኛ ተደራራቢ እስፔሊንጎች ማስታወስ ኣስቸጋሪነት የተነሳ ትክክለኛዎቹን ማስተማርና ማስታወስ ሳያስቸግር ኣይቀርም። ግዕዝ ኣዳዲስ ቀለሞችን እየፈጠረ ሲያድግ ቁቤ በኣሉት የላቲን ቀለሞች ላይ እስፔሊንግ መጨመር ስለኣለበት ለሁሉም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች እየጠቀመ ማደጉ ኣጠራጣሪ ነው። ምክንያቱም በሁሉም የግዕዝ ቀለሞቻችን ለመክተብ ከቁቤው የበዙ ልዩ የፊደል መክተቢያ እስፔሊንጎች መማር ሊያስፈልግ ነው። ስለዚህ ቁቤ የኣናሳ ተጠቃሚዎች በመሆን ኦሮምኛን፣ ኦሮሞውንና ኢትዮጵያን ሊያቈረቍዝ ይችላል።

፳፬. በኣጠቃቀም የላቲን ፊደል ከግዕዝ ሳድሳን ቀለሞች ጋር ኣንድ ዓይነት ነው። ግዕዝ እንዚራኑን በኣንዳንድ ቀለሞች ሲወክል ላቲን ዋየሎቹን ሳድሳኑ ጎን ማስከተብ ስለኣለበት ከሰባት ጊዜ በላይ እጥፍ ስፍራዎችን ያስባክናል። ይኸንን የግዕዝ ምሳሌ የ“ገ” 11 እንዚራን በላቲን ጠብቆና ሳይጠብቅ በመክተብ ልዩነቱን መመልከት ይቻላል።

፳፭. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን በስሕተት ኦሮምኛ 10 እንዚራን ሲያስፈልገው ግዕዝ ሰባት ብቻ ኣለው ይላሉ። ላቲን ኣምስት ዋየሎች ኣሉት ተብሎ ኣምስቱኑ ዋየሎች እየደራረቡ ኦሮምኛ ኣሥር ዋየሎች ኣሉት ማለት ኦሮምኛውን መሳደብ ነው። ዋየል መደራረብም ትርፉ ስፍራ ማባከን ነው። የላቲን ዋየሎች ኣምስት ናቸው ቢባል እንኳን ለኦሮምኛ ኣምስት ዋየሎች በቂ ኣይደሉም። የቁቤ ዋየሎች ኣምስት ከሆኑ ከኣምስት በላይ እንዚራን ለኣላቸው የግዕዝ ቀለሞች ለመጠቀም ከላቲኑ ቁቤ የበዙ የእስፔሊንግ ችግሮች ይፈጥራሉ። [1,075] ለምሳሌ ያህል “ዸ”ን በስምንት ዋየሎቹ ለመክተብ ለቁቤ ላቲን ከ20 በላይ ቀለሞች ሲያስፈልጉት ለግዕዙ ፯ በቂ ናቸው።

፳፮. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን በስሕተት ላቲን 26 ቀለሞች ሲኖሩት [1,076] የግዕዙ ብዙ ናቸው ይላሉ። የላቲን "a" ዓይነቶች ከ26 በላይ ናቸው። ዋናዎቹ 26 የላቲን ቀለሞች እንደግዕዙ 37 የተሟሉ ኣይደሉም። የግዕዝ ፊደላት በ37 የግዕዝ ቤት ተከፋፍለው እንዚራኖቹ በድምጽና በቅርጽ በወጉ የተደረደሩ ስለሆነ ሕጻናትን ማስተማር እንደ “abcd” ቢሆንም የግዕዝ ተማሪ የሚማረው እስፔሊንግ እንዳያስታውስ እንጂ ዕድሜ ልኩን እስፔሊንጎች እንዲፈልግ ኣይደለም። ለምሳሌ ያህል የካዕብ ቤቶቹ ቀለሞች የሚከተቡት በግዕዞቹ ላይ ከቀኝ ጎን መስመር በመጨመር ሲሆን ድምጾቻቸው እንዲሰሙ ከንፈሮችን ማሞጥሞጥ ያስፈልጋል። ላቲን እራሱን ለማሻሻል ኣዳዲስ ፊደላትን እየቀረጸ ሲሆን ቁቤ ሊጠቀምባቸው ኣልተዘጋጀም። የቻይና ሥዕላዊ [1,077] ፊደላት ብዙ ሺህ ናቸው። [1,078]

፳፯. ግዕዝ በእጅ ኣይጻፍ ይመስል ስለላቲኑ የእጅ ጽሑፍ (Cursive) የሚያነሱም ኣሉ። ዶክተሩ ኦሮምኛን በግዕዝ ፊደል በኮምፕዩተር ለመክተብ የሚያስፈልጉትን ከሠሩ በኋላ ለ24 ተነባቢና 10 ዋየሎቹ የኦሮምኛ ፊደላቱ 34 ቀለሞችን መፍጠር ስለሚያስቸግርና ኣስፈላጊ ኣይደለም ተብሎ ወደ ላቲን ዞርን ከቀረቡት ምክንያቶች ኣንዱ ነበር።

፳፰. ግዕዝ እንደኦሮምኛና ሲዳምኛ የኣሉትን (ኩሻዊ) ቋንቋዎችን [1,079] [1,080] ጥሩ ኣድርጎ ኣይጽፍም የሚለው ወይም የግዕዝ ኣንድን ድምጽ በኣንድ ቀለም መወከል እንደችግር ተቆጥሮ ወደ ላቲን ለመዞር የቀረቡት ምክንያቶች ወደ እውነት የተጠጉ ኣልነበሩም። ግዕዝ ለኣንድ ድምጽ ኣንድ ቀለምና ኣንድን ቀለም ለኣንድ ድምጽ በማድረግ የተራቀቀ ፊደል ነው።

፳፱. በግዕዝና በላቲን የሚጠቀሙ ኢትዮጵያውያን ስለማይግባቡ በየእለቱ እየተራራቁ ናቸው። ኣንድ ሕዝብ [1,081] በተለያዩ ፊደላትና ቋንቋዎች እንዲጠቀም ማስገደድ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ነበር። ኦሮሞው ዓማርኛና ፊደሉን እንዳይማር ተወስኖ የፌዴራል ሥራ እንዳያገኝ ሆኗል። እንደኦሮሞው ኣያያዝ በላቲን ፊደል የሚጠቀሙ ሌሎች ኢትዮጵያውያንም ኣሉ።

፴. ኣይርላንዳዊው በርናርድ ሿው ግዕዝን ዓውቆ ቢሆን ኖሮ ላቲን ቦታ ኣይኖረውም ነበር የሚል ጽሑፍ በሰይፉ ኣዳነች ቢሻው እዚህ ቀርቧል። [1,082] የላቲን ፊደል ለእያንዳንዱ ድምጽ ኣንድ ቀለም እንዲኖረው ተመኝተው ነበር። ላቲን የኣልተሟላና ኣክሳሪ ፊደል መሆኑንም ሿው ገልጸዋል። [1,083] ስለዚህ ባለቤቱ የጠላውን ኦሮሞው ኣዲስ ኣግበስባሽ መሆን የለበትም።

፴፩. ላቲን ማወቅ ኦሮሞዎችን ከፊደሉ ተጠቃሚዎች ያቀራርባል ተብሎ እንደምክንያት ቀርቧል። ኢትዮጵያውያን የላቲንን ፊደል ስለሚማሩ ኣልተጎዱም።

፴፪. በግዕዝ እንደኣስፈላጊነቱ መጠቀም እንዲቻል የማላልያ (Stretch) ምልክት ለመጀመሪያ ጊዜ ስለፈጠሩ የዶክተሩ ፓተንትም ውስጥ ተጠቅሷል። [1,084] የዩኒኮድ ግዕዝ መደብም ውስጥ ኣለ። ግዕዝ ኣንድን ቀለም ባለማጥብቅ፣ በማጥበቅና በማላላት ያስከትባል ይላሉ ዶክተሩ። [1,085] ቁቤ የሚረዝሙ ድምጸ ልሳናትን የሚወክልበት ምልክት የለውም። ኤ (a) ሾርት ዋየል እና ኤኤ (aa) ሎንግ ዋየል ናቸው ተብለው ዋየል፣ ማጥበቂያና ማላሊያም ሊሆኑ ኣይችሉም። ስለዚህ ላቲን ከግዕዙ ጋር ሲወዳደር ለቋንቋው የሚያስፈልጉትን እንዚራን በመቀነስ ኦሮምኛውን ጎዳው እንጂ ኣልጠቀመውም። [1,086] የኦሮምኛን “ዽ” ድምጽ “dh” እንጂ ግዕዝ ኣይጽፈውም በማለት ማታለል የኦሮሞው ትግል ምክንያትም ይሁን ውጤት ኣይደለም።

፴፫. ኣንዳኣንድ የኦሮሞ ምሁራን ላቲንም ሆነ ቁቤ ከውጪ የተገኙ ናቸው በማለት ግዕዝ የሳባ ፊደል ነው ማለቱን ኣክርረውበታል። ግዕዝ ኢትዮጵያዊ ፊደል ነው። [1,087] [1,088]

፴፬. ዶክተሩ ለግዕዝና እንግሊዝኛ ፊደል የሚጠቅሙ ግኝቶችን በማቅረቡ ገፍተውበታል። [1,089] የቁቤ ተከታዮች የኦሮሞ ምሁራን ላቲን እራሱን የኣሻሻለበትን ዘዴዎች እንኳን ሳይጠቀሙ ከግዕዙ ኣጠቃቀም እራሳቸውን ስለኣገለሉ ኢትዮጵያንና ዓለምን በመስኩ እንዳይጠቅሙ እየተደረገ ነው።

፴፭. በዓማርኛ “መሣሣት"ና “መሳሳት" እንዲሁም “ዓለማቀፍ"ና “ኣለማቀፍ" የመሳሰሉት ኣንድ ኣይደሉም።

፴፮. የግዕዝ ፊደል የኦሮምኛው ፊደል ውስጥ ያለውን “ዸ” እና ሰባት እንዚራን ቀለሞቹን ያጠቃልላል። [1,090] ስለዚህ እንደ “በዻዻ” የኣሉትን ቃላት በ“በዳዳ” ወይም “ዻራርቱ"ን በ“ደራርቱ” መክተብ ግድፈት ነው። የ“ዸ” እንዚራን የግዕዝ ፊደላት ውስጥ መኖርን በመካድ ኣንዳንድ የኦሮሞ ምሁራን ኦሮሞውን ሲያጃጅሉት ፴ ዓመታት ኣልፈዋል። ለምሳሌ ያህል “በዻዻ” የሚለውን ሦስት ድምጾች የኣሉትን ቃል በሦስት ቀለሞች በስድስት መርገጫዎች በግዕዝ ከመክተብ ይልቅ በላቲን በስምንት ቀለሞች በዘጠኝ መርገጫዎች መክተብ ዓይነት የተሻለ መሆኑን ሕዝቡ መርጧል የሚሉ ኣሉ። [1,091]

፴፯. ኦሮምኛን በግዕዝ ፊደል ማስተማር እንዲጀመር ሓሳብ ቀርቧል። [1,092] [1,093] [1,094] [1,095] [1,096] [1,097] [1,098] ይህ ሌሎች ኦሮምኛውን እንዲማሩም ያበረታታል።

፴፰. ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን በምክንያቶች ስለተሸነፉ ስሕተቶቹን ተቀብለው እንደመታረም ኣዳዲስ ምክንያቶችን እያቀረቡ በማወናበዱ ቀጥለውብታል። ለምሳሌ ያህል የኣማርኛ ታይፕራይተርም ይሁን የግዕዝ ማተሚያ ቤቶች የኣረቡን ኣኃዞች ሲጠቀሙባቸው ስለነበረ እንደኣዲስ ነገር ግዕዝ የኣልቦ ኣኃዝ ስለሌለው ፊደሉ ለሂሳብ ኣይጠቅምም ብለው ወደ ላቲን ለመዞር እንደምክንያት ማቅረብ የሚሞክሩ ኣሉ። ቁቤ ወደ ላቲን የዞረው በኣኃዞቹ ምክንያት ስለኣልነበረና ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ የግዕዝ ዜሮ ቀለምን ፈጥረው ስለነበረ ቁቤ ተቀባይነት እንዲያገኝ ሊመሠረት የሚፈለ'ገው በኣዲስ ቅጥፈት ላይ መሆን የለበትም። [1,099] [1,100]

፴፱. በቅርቡ በኣንድ ፀሓፊ “ተማሪ” የሚለውን ቃል በግዕዝ ቀለሞች ለማስቀመጥ ኣሥራ ሁለት ባይትስ (Bytes) ሲያስፈልገው በቁቤ “tamaarii” ስምንት ባይትስ ይበቃዋል በማለት የላቲንን ብልጫ ለማሳየት ተሞክሯል። ሁለቱም የሚወስዱት ስምንት ባይትስ ነው። (ይህ ቀለሞቹ ፊታችን በኮምፕዩተር እስክሪን ወይም ወረቀት ላይ ሲታዩ ማለት ኣይደለም።)

፵. ግዕዙ ላይ ከተጨመሩት የተለዩ የእራሳቸው ፊደላት ከኣሏቸው 13 የፊደል ዓይነቶች ሌላ ወደፊት ለኣፍሪቃና ሌሎች ቋንቋዎች ኣዳዲስ ፊደላት ሲጨመሩ በየስሞቻቸው ይቀርባሉ። በፊደሉ መጠቀምንና ኣለመጠቀምን ዶክተሩ ኣያስገድዱም።

፵፩. “የኦሮሞ ሊቃውንት ባደረጉት ጥናት መሠረት ለኦሮምኛ የሚስማማውን ፊደል (ላቲንን) መርጠውለታል፤ ይህ ያለቀ፥ የደቀቀ ጉዳይ ነው፤ ኦሮሞ ያልሆኑትን የሚገዳቸው ጉዳይ አይደለም። ጉዳዩ የሚገድደው ኦሮሞዎችን ብቻ ከሆነና ኦሮሞዎች ከተስማሙበት በጥላቻ ላይ የተመሠረተ ምርጫ ሊያደርጉ ይችላሉ። ኦሮምኛ ብሔራዊ ቋንቋ እንዲሆን ከታሰበ ግን፥ ጉዳዩ ብሔራዊ እንጂ ኦሮሞዎች ብቻቸውን የሚወስኑበት የኦሮሞዎች ጉልማ ሊሆን አይችልም። ጥያቄውም ከሌሎቹ ቋንቋዎች ይልቅ በኦሮምኛ ላይ የሚነሣው በዚህ ምክንያት ነው።” ይላሉ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ። [1,101] ግዕዝ ለኦሮምኛ እንደሚበጅ የሚቀርቡ ጽሑፎች ቀጥለዋል። [1,102] [1,103] [1,104] [1,105] [1,106] [1,107] [1,108] [1,109] [1,110] [1,111] [1,112] የፖለቲካን ችግር ሳይንስ ማድረግ መሞከር ተገቢ ኣይደለም።

፵፪. ኣንዳንድ ሰዎች “ዱ” ፊደል ሆኖ ቀለበቱ መካከል መስመር የኣለውን ቀለም (“ꬉ”) የኦሮምኛው የግዕዝ ፊደል ነው ይላሉ። ይህ ስሕተት ነው። እነ“ꬉ” የጋሞ ጎፋ፣ ዳውሮና ባስኬቶ ፊደላት ናቸው።

፵፫. በግዕዝ ፊደል ድምጽን ከፍና ዝቅ ማድረግ (Tone) ለመለየት የሚያስችሉ ምልክቶችን መፍጠር ይቻላል። ይህ ለኦሮምኛው ኣስፈላጊ ኣይደለም። ዶ/ር ኣማረ ተግባሩ ኃይሌ ፊዳ በሚለው በ፳፻፲ ዓ.ም. በታተመው መጽሓፋቸው ገጽ 101 ላይ "የግዕዙ ፊደል ድክመቶቹን ለማስወገድ የሚያስችል ቅጥያዎች ከተደረጉለት ኣፋን ኦሮሞውን በግዕዝ ፊደል መጻፍ እንደሚቻል ዶ/ር ኃይሌ መናገራቸውን መመስከር እችላለሁ" ይላሉ።

ግዕዝና ዓማርኛ ለማስተካከል

ይህ ጽሑፍ ዓማርኛን የተመለከተ ስለ ፊደሉ [1,113] (እንደ ኦሮምኛው) የዶክተሩ ኣስተዋጽዖ እንጂ ስለ ቋንቋው ኣይደለም። ስለ ቋንቋው በየሺሓሳብ ኣበራ እዚህ [1,114][1,115] [1,116] [1,117] [1,118] ጥሩ ቀርቧል።

የግዕዝን ፊደል በኮምፕዩተር መጠቀም ኣዲስ ቴክኖሎጂ ስለሆነ የተጠቃሚው መሠረታዊ ሕጎችንና ወጎችን ማወቅ ኣስፍላጊ ናቸው። ቴክኖሎጂ ጠቃሚ ነው። [1,119] እነዚህ ታውቀው በኢትዮጵያውያን ትጋት ብዙ ሚሊዮን ጽሑፎች በኣለፉት ፴፪ ዓመታት ቀርበዋል። የፊደሉ እድገት ለወዳጆቹ ትልቅ እርካታ ነው። ለምሳሌ ያህል ዶ/ር ዓለሙ ቢፍቱ በሞዴት፣ ዶ/ር ለይኩን ብርሃኑ በኢትዮወርድ መጽሓፎች ጽፈው ኣሳትመዋል። በቅርቡም ዶ/ር ኣክሊሉ ሃብቴ ግዕዝኤዲትንና ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ፊደሉን ተጠቅመዋል። [1,120] የመጀመሪያው የግዕዝ ትሩታይፕ ፊደላችን እንደኣስፈላጊነቱ እየታረመ የዩኒኮድ ፊደል የሆነው ትክክከኛ ቅርጾች እዚህ ጎን ከኣለው የኣቶ ኣብርሃም ያየህ የ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. መጽሓፍ ማሳሰቢያ ገጽ ሥዕል መመልከት ይቻላል። በዶክተሩ ፈጠራ ምክንያት መጽሓፎቻቸውን ጽፈው ለማሳተም የቻሉ ብዙ ኢትዮጵያውያን ኣሉ። ከእነዚህም መካከል እ.ኤ.ኣ. በ1994 የዶክተሩን ፕሮግራም በመጠቀም ከ25 ዓመታት በኋላ ምስጋና የለገሷቸው ኣንዱ ዶ/ር ኣማረ ተግባሩ ናቸው። [1,121] [ የዶ/ር ኣበራ ሞላ እና ጋሼ አበራ ሞላ (ስለሺ ደምሴ) ግንኙነትም እዚህ ኣለ። [1,122]

ይህ በእንዲህ እንዳለ [1,123] በኣለማወቅ በተለይ ዓማርኛ ላይ ብዙ ችግሮች የኣደረሱ ኣሉ። ከግዕዝ ፊደል ተጠቃሚዎች ዓማርኛ ዋነኛውና ወሳኝ ነው።

፩. የኮምፕዩተር፣ እጅ ስልክና የመሳሰሉት የቴክኖሎጂ ግኝቶች በብዙ ቢሊዮን ዶላር ወጪ፣ በብዙ ሰዎች ድካም፣ ፓተንቶችና ምርምሮች የተገኙ ስለሆኑ ሶፍትዌር እንደማንኛውም ነገር የሚገዙ እንጂ ኣንዳንዶቹ እንደሚያደርጉት ሰርቆ መጠቀም ነውር ነው። ብዙ ኢትዮጵያውን እነዚህን ሁሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች ሳንከፍልባቸው በማግኘታችን እንደማመስገንና ለግዕዝ የሚያስፈልጉትን ገዝቶ [1,124] ከመጠቀም ይልቅ ፊደሉ የእራሱ ገበታ እንዳይኖረው የሚፈልጉትን ጭምር ዓውቀውም ሆነ ሳያውቁ እየረዱ ናቸው። ፪. የግዕዝ መክተቢያ ሁሉንም ተጠቃሚ ቋንቋዎች ለማስተናገድ የሚችል መሆን ይኖርበታል። ችሎታውን ከኣለው ለዓማርኛው ብቻ ማቅረብ ሲቻል ዓማርኛ ብቻ የሚያስጽፍ ግን ዓማርኛውን ኣደጋ ላይ የሚጥል ነው። ለምሳሌ ያህል “ቜ”ን በ6 መርገጫዎች የሚከትብና “ⷄ”ን ለመክተብ ከ6 በላይ ተጨማሪ መርገጫዎች የሚያስፈልጉት ኣለ። እየኣንኣንዱን ቀለም በሁለት መርገጫዎች መክተብ ሲቻል የ“ጬ”፣ “ⶼ”፣ “ꬤ” እና “ⶐ” ኣከታተብ ለመለየት የመክተቢያ እስፔሊንግ ማስታወስ ወይም መዝገብ (መዝገበ ፊደል) ያስፈልጋል። ፫. ዓማርኛ የማያስጽፍ መጻፊያ ይጽፋል ተብሎ ኢንተርኔት ላይ ለዓመታት ተቀምጧል። በዶክተሩም የፓተንት ማመልከቻዎች ቀርበዋል። ይኸን የሚያስተውልና የሚቃወም የተማረ ኢትዮጵያዊ ኣለመኖር የሚያሳዝንና የሚያሳፍር ነውና ይታሰብበት። ምሳሌ፦ “ትዝታ”፣ “ድድ”፣ “ህህ”፣ እና “ሏ”ን የማያስጽፉ ኣሉ። ምክንያቱም ሕዝቡ ትናንሽ ችግሮችን እየተመለከተ መቃወም ከኣልቻለ እራሱን ከከባድ ችግሮች ለመከላከል ኣለመዘጋጀቱን ስለሚያሳይ ነው። [1,125] [1,126] ይኸን ኣጻጻፍ የወደዱ ከመቶ ሺህ በላይ ተጠቃሚ ኢትዮጵያውያንን ምን እንደነካቸው ማስገረም ቀጥሏል። ምክንያቱም ጥቂት የኦሮሞ ምሁራን ግዕዙን ለመጥላት መጥላት ምክንያት ሊሆን ሲችል የኣንዳንድ የዓማርኛ ፊደል ተጠቃሚዎች በኣምታታቾች መጃጃል ምክንያቱ ኣልተገኘም። ላቲን እስፔሊንግ የሚጠቀመው ለቃላት ሲሆን የኣንዳንድ ኢትዮጵያውያን ፊደሎቻቸው ቃላት ይመስሉ በላቲን እስፔሊንግ መክተብ ምን ይባላል? ፬. ኣንዳንድ ኢትዮጵያውያን ለብዙ ዓመታት ዓማርኛውን በእንግሊዝኛ ፊደል በተገኘው እስፔሊንግ ሲጽፉ ቆይተዋል። [1,127] እንደ ፓልቶክ የኣሉ ፕሮግራሞች ምሳሌዎች ናቸው። በፓልቶክ ለመሳተፍ ከተቻለ እንደ ግዕዝኤዲት የኣሉትንም የዓማርኛ መክተቢያ መጠቀም ስለሚቻል ኣንዳንድ ዓማርኛ ተናጋሪዎች ዓማርኛውን በኣለመጠቀም እያዳከሙት ናቸው። በዓማርኛ እያወሩ በላቲን መጻፍ ከቀጠለ ነገ ዓማርኛውን መጻፍ የሚችሉ ላይኖሩ ይችላሉ። ይህ የብዙ ሺህ ዓመታት ታሪክ ከኣለው ሕዝብ ትውልድ ኣይጠበቅም። [1,128][1,129] [1,130]

፭. ኣንድ የዓማርኛ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት ሲጀመር ኣስተያየት በእንግሊዝኛ የሚሰጡ ኣሉ። በእንግሊዝኛ የሚጽፉት ዓማርኛውን ለማዳከም ሊሆን ስለሚችል በተለይ ስማቸውን እየደበቁና እየተሳደቡ የኣሉትን የድረገጾቹ ኣቅራቢዎች ማንሳት ይገባቸዋል። ፮. ኣንድ የዓማርኛ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይት ሲጀመር ኣስተያየት በእንግሊዝኛ የሚሰጡ ምሁራን ኣሉ። በዓማርኛ መጻፍ የማይችሉት ስለጉዳዮቹም ላይገባቸው ስለሚችል በኣለማስተዋል ዓማርኛውን እያዳከሙ ናቸው። ዓማርኛ የሚያነቡ እንጂ የማይጽፉ የቋንቋው ምሁራን በእንግሊዝኛ ሲጽፉ ኣንባቢዎቹንም ላይገባቸው ይችላል። ፯. ኣንዳንድ ምሁራን ዶክተሩ እየተጠቀሙበት የኣለውን ፊደል ስለሌላቸው ስለቅርጾቹ የሚያነቡትን ባይረ'ዱ ኣያስገርምም። ምክንያቱም ጽሑፉን የሚጽፉትና የሚያነቡት መሣሪያው ላይ በኣለ ፊደል ስለሆነ ነው። ለምሳሌ ያህል ሦስት ቀለበቶች የኣሉት ኃምሱ እንጂ ግዕዙ “ጨ” ኣይደለም። [1,131] ስለዚህ ኣንድ ኣንባቢ ወይም ፀሓፊ ሦስት ቀለበቶች የኣለውን ግዕዝ “ጨ” ከኣየ የሚጠቀመው በተሳሳተ ፊደል ነው። ፰. በኮምፕዩተር ዘመን ስለኣለን ጽሑፎችን ለማቅረብ ወርቃማ ጊዜ ውስጥ ነን። ሶፍትዌራችንን እየገዙ የኣሉት ዓማርኛ ተናጋሪዎች ስለሆኑ እናመሰግናለን። [1,132]

፱. በግዕዝ ኮምፕዩተር መክተቢያ ከኮምፕዩተሩ ጋር ስለማይመጣ መክተቢያ መግዛት ያስፈልጋል። የኮምፕዩተርም ዋና ጥቅም የተጻፈን ነገር ማስቀመጥ ስለሆነ ማስቀመጥ ጠቃሚ ነው። በተጨማሪም ኣንድን ጽሑፍ እንደፌስቡክ ከኣሉ ገጾች ውስጥ ወስዶ ማስቀመጥ ብቻ በቂ ኣይደለም። በቋንቋዎቻችን የተጻፉ መረጃዎች እንደሌሎች ቋንቋዎች በብዛት እንዲኖሩ በእጥፍ ብዛት መጻፍና ማስቀመጥ ይጠበቅብናል። በኣለፉት ጥቂት ዓመታት ብዙ ጽሑፎች በኢትዮጵያውያን ትጋት ስለቀረቡ በኮምፕዩተር እንግሊዝኛውን ወደ ዓማርኛና ዓማርኛውን ወደ እንግሊዝኛ መተርጐም ተጀምሯል። ፲. የዓማርኛ ትክክለኛዎቹ ኆኄያት "ዓማርኛ" ናቸው። ሌሎች ምሳሌዎችም “ኃይል”፣ “ሕዝብ” እና “ዓቢይ” ናቸው። ለምሳሌ ያህል “አቢይ”፣ “ኣቢይ”፣ “ዐቢይ”፣ ወይም “ዓብይ” ትክክል ኣይመስለኝም ይላሉ ዶክተሩ። ምሳሌ [1,133] የፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ባሕረ ሓሳብ መጽሓፍ ገጽ 47 እና 48 ስለ ዓቢይ ጾምና ዓቢይ ቀመር ቀርበዋል። ፲፩. በኣጠቃላይ በኣለፉት 45 ዓመታት የኢትዮጵያውያን የዕውቀትና የዓማርኛ ቋንቋዎች ችሎታዎች ኣቆልቍለዋል። በተለይ በእዚህ ዕድሜ ክልል ውስጥ የኣሉ ምሁራን ዓማርኛ ሲናገሩ እንግሊዝኛ [1,134] እንዳይቀላቅሉ ሊያስተውሉ ይገባል። ፲፪. ኣንዳንድ ዓማርኛ ተናጋሪዎች “Torture” በሚለው ቃል ምትክ “Torch” የሚለውን ይጠቀማሉ። መዝገበ ቃላት መጠቀም ሳይጠቅም ኣይቀርም። [1,135] [1,136] ፊደል በሚገባ ስለ ኣልቆጠሩ በ“ነው” ምትክ “ነዉ" ይጠቀማሉ።

፲፫. ኣንዳንድ ዓማርኛ ፀሓፊዎች በነጠላ ሰረዝ ምትክ የላቲኑን ኮማ (Comma) እንዲሁም በድርብ ሰረዝ ምትክ የላቲኑን ሰሚ ኮለን (Semi-colon) መጠቀም ስለጀመሩ ዶክተሩ እየተቃወሙ ናቸው። ፲፬. ኣንዳንድ ዓማርኛ ፀሓፊዎች መጽሓፎች ሲያሳትሙ ገጾቹን ለየብቻቸው እያተሙ ይጠርዛሉ። የመጽሓፍና መጽሔት ገጾች ሲታጠፉ ቍጥሮቹና ርዕሶቹ መሣሣም ይገባቸዋል። ለምሳሌ ያህል ገጽ ኣንድ ከግራ ግርጌ ግራ ማዕዘን ላይ ከሆነ ገጽ ሁለት ከቀኝ ግርጌ ቀኝ ማዕዘን ላይ መሆን ይኖርበታል። ፲፭. ኣንዳንድ ምሁራን ለዓማርኛ ቃለ ምልልስ ሲቀርቡ በዓማርኛ መናገር እንዳለባቸው ኣስቀድሞ ማስጠንቀቅ ያስፈልጋል። እንግሊዝኛ እየቀላቀሉ የሚያስቸግሩትን በማረም የኣሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ጥሩ ሥራ ይዟል። ፲፮. ኣንዳንድ ኢትዮጵያውያን ዓማርኛውን ኣራት ነጥብ በሌለው ከመጻፍ እንዲቆጠቡና ኣራት ነጥብ በሌለውም መጻፊያ እየጻፉ ጊዜያቸውን ከማባከን ቢቆጠቡ ይጠቅማል።

፲፯. ኣንዳንድ ፀሓፊዎች ሞክሼዎች የሚሏቸውን ቀለሞች በሌሏቸው ዓማርኛውን እየጻፉ ችግሮች እየፈጠሩ ናቸው። ለምሳሌ ያህል “መሳሳት“ና “መሣሣት" ኣንድ ኣይደሉም። “ምሥር“ አና “ምስር“ ኣንድ ኣይደሉም። ፲፰. ኣንድ የግዕዝ ፊደል በሁለት መርገጫዎች እንደተከተበ ከዶክተሩ ፈጠራ ጋር ከነማስረጃዎቹ ከቀረቡ ፴፪ ዓመታት ኣልፈዋል። ማንኛውንም የግዕዝ ፊደል ዛሬ በሦስትና ከእዚያ በላይ መርገጫዎች መክተብ ከተማረ ሕዝብ ኣይጠበቅም። ኣንድን የዓማርኛ ቀለም በ5 መርገጫዎች መክተብ ኣንዳንዶቹን የሌሎች ቋንቋዎች ቀለሞች ለመክተብ እስከ ስምንት መርገጫዎች መጠቀም ያስፈልጋል። ፊደል ለመክተብ ቃላት ይመስል እስፔሊንግ ማስታወስ የለብንም። ፲፱. ኣንድ የግዕዝ ፊደል በኣንድ ወይም ሁለት መርገጫዎች ከተከተበ በኋላ ልክ እንደላቲኑ ሌላ ፊደል ኣጠገቡ ስለተከተበ ኣይቀየርም። ሌላ ፊደል ወይም መርገጫ የሚቀይረው ከሆነ መጀመሪያውኑ ቀለሙ ኣልተከተበም ማለት ነው። እነዚህ ከነማስረጃዎቹ ከቀረቡ በኋላ በእንደዚህ ዓይነት መክተቢያዎች መጠቀምና የኣልተጻፉትን ማንበብ ሊያበቃ ይገባል። ፳. ኢትዮጵያ የእራሳቸው ፊደል ከኣሏቸው ጥንታዊ ጥቂት ኣገራት ኣንዷ ሆና ሳለ እንደሌሎቹ ቴክኖሎጅውን ማሳደግ ሲገባ የሶፍትዌር መብት በሚገባ የማይከበርባት ኣገር ሆናለች። ይህ የኢትዮጵያን እድገት ማቀጨጩን ይቀጥላል። የሌላውን መብት የማያከብርን መንግሥትና ሕዝብ ማሰልጠንና መብት ማስጠበቅ ኣስቸጋሪ ነው።

፳፩. ዓማርኛ የተናጋሪዎቹ የነበረና የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጽሑፍ ቋንቋ የሆነ ነው። [1,137] ፳፪. በኣሁኑ ጊዜ ዓማርኛ ኢንተርኔት ላይ ብዙ እድገት እያሳየ ነው። እንደነ ጉግልና ፌስቡክ የኣሉ ድርጅቶች ሥራዎቻቸውን በዓማርኛ ሲያቀርቡ ኢትዮጵያውያን እየተራዱ ከኣሉት መካከል ናቸው። ይህ ጥሩ ሥራ ሆኖ ሳለ በቂ ዕውቀት የሌሏቸው እየገቡበት ስሕተቶችን እያስፋፉ ናቸው። ለምሳሌ ያህል “Days” የሚለውን ቃል “ቀናቶች” በማለት የሚያቀርቡ ኣሉ። ትርጕሙ “ቀናት” ወይም “ቀኖች” እንጂ “ቀናቶች” የሚባል ነገር የለም። ፳፫. ግዕዝ ለመጀመሪያ ጊዜ በኮምፕዩተር በዶ/ር ኣበራ ግኝት እስከሚቀርብ ድረስ ቴክኖሎጂው ስለኣልነበረም ከእርሳቸው ዘዴም ውጪ በግዕዝ መጻፍ ኣይቻልም ነበር። ዝምታው ስለቀጠለ ቴክኖሎጅውን ቀድመው ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣደረግን የሚሉ ዋሾዎችም ኣሉ። ፳፬. የግዕዝ ፊደል ሌሎች እንዲጠቀሙበት ቀለሞች እንደመጨመር በስሕተት ዓማርኛው ኣይፈልጋቸውም እያሉ በተቀነሱ ፊደላት የሚጠቀሙ ኣሉ። ባለቤቱ የኣላከበረውን ፊደል ጎረቤት ኣይፈልገውም።

፳፭. የግዕዝ ፊደል ለሁሉም ተጠቃሚ ቋንቋዎች የሚያስፈልጉትን በኣንድና ሁለት መርገጫዎች በዶክተሩ ግኝት መክተብ ተችሏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የተቀነሱ የዓማርኛ ፊደላትን እንኳን ከሦስትና ከእዚያም በላይ መርገጫዎች የሚከትቡ የእንግሊዝኛ እስፔሊንግ የመክተቢያ ዘዴዎች የኣለተቃውሞ እየተስፋፉ ናቸው። እነዚህ ኣከታተቦች ሌሎች የኣናሳ ተጠቃሚዎች ቋንቋዎች ቀለሞች በበዙ መርገጫዎች እንዲከተቡ ያስገድዳሉ። ዓማርኛ በበዙ መርገጫዎች በሌሎቹ ቋንቋዎች ምትክ ለመጠቀም ከኣልተዘጋጀ በዘዴዎቹ መጠቀም የለበትም። ፳፮. ኦሮምኛን በላቲን መክተብ (ቁቤ) ከኣሰከተሉት ችግሮች ኣንዱ የማያስፈልጉ ብዙ መርገጫዎችን መነካካት ነው። ዓማርኛን በላቲን እስፔሊንግ መክተብ ተቀራራቢ ችግሮችን ስለሚፈጥር የዘዴው የግዕዝ ተጠቃሚዎች ሌሎችን በእዚህ ለመውቀስ ብቃት የላቸውም። ፳፯. የግዕዝ ፊደል አንዲቀነስ የሚያቀነቅኑ ኣሉ። [1,138] ፳፰. ኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ የኣላት ኣገር መሆኗ እየተረሳ ወሬና ፖለቲካ ላይ ማተኰር በዝቷል። በግዕዝ እንዲከትብ የኣደረገለትን ለማመስገንም የማያውቅ ሕዝብ ወደመሆኑ ስለተጠጋ ፈጣሪን ማመስገን ኣይጎዳም። ግዕዝ ኮምፕዩተራይዝድ ሆኖ በኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች እየተጠቀምንበት ይህን ግኝት የፈጠሩልን ዶ/ር ኣበራ ሞላ [1,139] መሆናቸውን የማያውቁ ብዙ ናቸው። ፈረንጁ ኣዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ፈጥረው ዓለምን በቴክኖሎጂ የቀየሩትን ፓተንቶች የኣሏቸውን እነ ቶማስ ኤዲሶን፣ ግራሃም ቤል [1,140]፣ እስቲቭ ጆብስ [1,141] ፣ ቢል ጌትስ [1,142] የመሳሰሉትን ሲያከብርና ሲያበረታታ ኢትዮጵያዊውን ሳይንቲስት ሶፍትዌሩን በፓተንቶች ጠብቀው ሲያቀርቡ [1,143] ለመግዛትና ሥራውን ለማስተዋወቅ እንኳን የሚፈልጉ ብዙ ኣይደሉም። [1,144] በኮምፕዩተር መጻፍ ኣለመቻል የዘመኑ መኃይምነት ነው።

፳፱. ኣንድ ደራሲ ስለኣንድ ነገር ሲጽፍ የእራሱ ሥራ ከኣልሆነ ዋቢ ማቅረብ ተገቢ ነው። ዋቢ የሌለው ሥራ የደራሲው ብቻ ነው ማለት ነው። ፴. ኣንድ ደራሲ ትክክለኛ የቃላት ቀለሞችን ከዘነጋ መዝገበ ቃላት መመልከት ጠቃሚ ነው። ምሳሌ፦ [1,145] መዝገበ ቃላት እያሉ [1,146] Archived ሴፕቴምበር 12, 2023 at the Wayback Machine ፊደል በሚገባ የኣልቈጠሩ ጸፀሓፊዎችን በመከተል በ “ው” እንጂ በ “ዉ” የማይጻፉትን እየጻፉ ቋንቋ ማበላሸት ከኣንዳንድ የተማሩ ሰዎች ኣይጠበቅም። መኃይም የማይሠራውን ስሕተት የተማረው ሲሠራው ኣሳፋሪ ነው። ለምሳሌ ያህል እዚህ ጽሑፍ ውስጥ ከ፬፻ በላይ ግድፈቶች ኣሉ። [1,147] አዚህ ውስጥ የለም። [1,148] ፴፩. “ፊደላቱ የሚሰጡትን ድምጽና ትርጉም ኣውቆ የኣንዱ ፊደል መውጣት መሻሻል ለረዥም ዘመናት የተጻፉ መጻሕፍት የሓሳብ፣ የትርጕም፣ የቅርስ ጥፋት እንደሚያመጡ ማወቅ ይሻል። ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ዳግም ጥያቄ በማያስነሳ መልኩ ትክክለኛውን ነገር ሊያስቀምጡና ጥናት በማጥናት ምላሻቸውን ሊሰጡ ይገባል። ከእዚህም በላይ ደግሞ ባለድርሻ የሆነችው ቅደስት ቤተ ክርስትያን ምላሿን ማሳወቅ እንደሚገባት የጥያቄው መብዛት ኣፋጣኝ እንደሆነ ያመላክታል” ይላል ማኅበረ ቅዱሳን። [1,149] እንዲህም ሆኖ ጽሑፋቸውን በዓማርኛ እንዲጽፉ ያስቻላቸውን እግዜር ይስጥልኝ ለማለት እንኳን የዶክተሩን ስም ሰምተው ላያውቁ ይችላሉ። ፴፪. በተሳሳተ መክተቢያ የተጻፈ በመሆኑ ኣስተማማኝ የኣልሆነ ጽሑፍ ምሳሌ እዚህ ኣለ። [1,150] ከእዚህ ጽሑፍ ኣንድ ሁለት ኣንቀጾችን ኮፒ ተደርገው http://www.freetyping.geezedit.com ወይም http://ethiopic.com ገጽ ላይ ቢለጠፉ ችግሮቹን መመልከት ይቻላል።

፴፫. ግዕዝ በዶክተሩ ኮምፕዩተራይዝድ ሆኖ ተገቢውን ዕውቅና ኣግኝቷል። የማይጽፉና የኣልተሟሉ መክተቢያዎች እየተጠቀሙ ኣንዳንድ የዓማርኛ ምሁራን እራሳቸውን እያዋረዱ ናቸው። ለምሳሌ ያህል ያልተሟሉ የመክተቢያ ዘዴዎች ኣሉ። ሕዝቡን እያወናበዱ የኣሉት ወደ ኦሮምኛው የላቲን ቁቤ ኣከታተብ ዓይነት በብዙ መርገጫዎች የሚያስከትቡ ኣሉ። ፴፬. ኣንዳንድ የዓማርኛ ደራስያን በተሳሳቱ መጻፊያዎችና ፊደላት እየተጠቀሙ እራሳቸውን እየጎዱ ናቸው። በጊዜ መንቃት ስለኣልቻሉ ኣንዳንዶቹ እንደኦሮሞዎቹ መጃጃልን እያስፋፉ ናቸው። ፴፭. በቂ የኢንተርኔት ኣገልግሎት ኢትዮጵያ ውስጥ ስለሌለ የዶክተሩን ሥራዎች የማያውቁ በተወሰነው ዕውቀታቸው የሚያቀርቧቸው ኢትዮጵያን እየጎዱ ስለሆነ ኣንባቢው ይሀን ከግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል። ምሳሌዎች፦ ይህ [1,151] Archived ዲሴምበር 28, 2019 at the Wayback Machine ስለ [1,152] እና [1,153] ያልሰማ ይመስላል። ስለ ጋብርኤላ፣ ስለ ዶ/ር ኣየለና ካማራ የዶ/ሩ ሥራዎች ውስጥ ተጠቅሰው ስለኣሉ ከሁሉም ቀድሞ የነበሩትን ሥራዎች ኣንዳቸውም ኣልጠቀሱም። በዶክተሩ በተፈጠረው ቴክኖሎጂ እየተጠቀመ የማያመስግነው ቍጥር ስፍር ስለሌለው ከተለመደው መደበቅ ታልፎ ስድብ ተጀምሯል። ፴፮. የዓማርኛውን ፊደል ከ“ሀ” እስከ “ፐ” በቃል የማይደረድሩ ምሁራን ኣሉ ይባላል። [1,154] ይህ ኣሳፋሪ ነውና ይታሰብበት።

ፊደል ቅነሳ ለማስተካከል

ስለ ፊደል ቅነሳ እዚህ ገጽ በየቦታው የቀረቡ ቢኖሩም እንደገና ማንሳቱ ኣይጎዳም።

፩. የግዕዝ ፊደል ከ1513 ዓ.ም. ጀምሮ እስከኣሁን ድረስ በማተሚያ መሣሪያዎች በሚገባ እየተጠቀመ ስለሆነ የብቃት ችግር የለውም። መጽሓፍት በማተሚያ ቤቶች ሲታተሙ ስሕተቶቹ ብዙ ኣልነበሩም። ፊደል መቀነስ የተጀመውረው በሚሲዮናውያን ነው። [1,155] በዐፄ በካፋ ዘመነ መንግሥት ሃሌታውን “ሀ” ከሐመሩ “ሐ” ንጉሡን “ሠ” ከእሳቱ “ሰ” ፥ ጻድቁን “ጸ” ከፀሐዩ “ፀ” ለይቶ በሥፍራቸው ያልጻፈ፤ ፊደል አዛውሮ የተገኘ ጸሐፊ እጁን ይቆረጥ እንደ ነበረ የጽሑፍ መረጃዎች ይጠቁማሉ። [1,156] ፪. የመቀነሱም ነገር ብዙዎቹ ሲከራከሩ እንደነበሩት ዓማርኛውን ብቻ የተመለከተ ኣይደለም። ፫. ከዳግማዊ ምኒልክ ጀምሮ ብዙ ኢትዮጵያውያን ሊቆች፣ ሚኒስትሮችና ደራስያን የእንግሊዝኛውን የታይፕ መጻፊያ ለዓማርኛ መክተቢያ እንዲያገለግል ወደ ሰማንያ ዓመታት ግድም ሲመራመሩ ቆይተው ኣልተሳካላቸውም። ፬. ኢ/ር ኣያና ብሩና ኢ/ር ተረፈ ራስወርቅ የዓማርኛውን ፊደላት በመቀነስና ቆርጦ በመቀጠል ኣማርኛ በመሰሉ የፈጠራ ቅርጾች የኣቀረቧቸው ሥራ ላይ ውለዋል። እነዚህ ቍርጥራጮች ግን የዓማርኛ ፊደሎች ኣይደሉም። ለእነዚህ ከመቶ በኣነሱ መቀጣጠያዎች የሚሠሩ የፈጠራ የኣማርኛ ነገሮች የሚያስፈልጋቸው ኣንድ የእንግሊዝኛ የፊደል ገበታ ስለሆነ በኣንዱ ገበታ ምትክ ብቻ የቀረቡ ናቸው። የዓማርኛ ቀለሞች ብዛት ከ200 በላይ ስለሆነ 100 ስፍራዎች ኣይበቁትም።

፭. ኆኄያቸውን የጠበቁ የግዕዝና ዓማርኛ ጽሑፎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለብዙ ዘመናት ተጽፈዋል። ፮. በእጅ ጽሑፍም ወረቀት ላይ መክተብ ለኢትዮጵያ ሕዝብና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ጠቅሟል። [1,157] ፯. ፊደል መቀነስ ትኩረት የኣገኘው “ፍቅር እስከ መቃብር” መጽሓፍ በተቀነሱ ፊደላት በ፲፱፻፶፪ ዓ.ም. ከታተመ በኋላ ነበር። እዚህ ላይ ተደርቦ ለታይፕራይተር ቴክኖሎጂ እንዲመች የፊደል ቅነሳ ክርክር ተጀምሮ በመጨረሻው ውድቅ ሆነ። ፰. የኢትዮጵያ ቋንቋዎች መርሐ ልሳን [ኣካዴሚ] በ1973 ዓ.ም. ካወጣው የአጻጻፍ ሥርዓት ውሳኔ በስተቀር ሌላ ወሳኝ ጥናት ባለመደረጉ፣ ለዚህ ጉዳይ ተጠያቂ ሊሆን የሚችሉ መምህራንንም ስለዚህ ጉዳይ ሆን ብሎ ያስተማራቸው ሰው ባለመኖሩ እነሱ ራሳቸው በዘፈቀደ ስለሚጽፉ ተማሪዎቻቸውም የነሱን ፈለግ በመከተል በዘፈቀደ ይጽፋሉ፤ የሚሉት ዶ/ር አምሳሉ አክሊሉ "የአማርኛን ሞክሼን ሆሄያት ጠንቅቆ ያለመጻፍ ችግርና መፍትሔ" የሚባል መጽሓፍም ጽፈዋል። ሃሌታው “ሀ”፣ ሓመሩ “ሐ”፣ ብዙኃኑ “ኀ”፣ ንጉሡ “ሠ”፣ እሳቱ “ሰ”፣ ኣልፋው “አ”፣ “ዓይኑ” “ዐ”፣ ጸሎቱ “ጸ”፣ ፀሐዩ “ፀ” የተባሉትን በማጥበቅና በማላላት ብቻ ለመግለጽ ኣስቸጋሪ ነው።

እንደ ዶ/ር ኣምሳሉ ተፈራ ኣገላለጽ "ከፊደላት ጋር የሚከሰቱ ችግሮችን ኣስመልክቶም በዓማርኛ ፊደል ገበታ ላይ ተመሳሳይ ድምጽ ያላቸው ስለሚገኙ፤ በኣጻጻፍ ረገድ በርካታ ልዩነቶች መኖራቸው፤ ራብዕ ድምፅ ያላቸው ከግዕዙ ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው ፊደላት መኖራቸው፤ ሳድስና ሳልስን እያቀያየሩ መጠቀም፣ ዲቃላዎችንና ፍንጽቅ ፈደላትን በዝርዝር የመጠቀም ዝንባሌ፣ በመሠረታዊ ቃሉ ላይ የሌለውን ቃል መጨመር፣ የኣናባቢዎች ቅጥል ኣለመለየት ችግሩን ይበልጥ እንዳሰፋው ጠቁመዋል። [1,158] (የእነዚህም ምሳሌዎች በቅደም ተከተል “ሀ" እና “ኀ"፤ “ሃገር" እና “ኣገር"፣ “አ" እና “ኣ"፣ “ግዜ" እና “ጊዜ"፣ “ፏፏቴን"ን በ“ፍዋፍዋቴ"፣ “ኈ"ን በ“ሆ"፣ “መምህራንን" በ“መምህራኖች" እና “ዮ"ን በ“ዬ" ዓይነቶች ናቸው በማለት በኣጠቃላይ ግን ችግሩ ከፊደሉ ሳይሆን ከተጠቃሚው ነው ይላሉ ዶ/ር ኣበራ።) ይህ ችግር በምሁራን ዘንድ ሞክሼ ቃላት ይቀነሱ፤ አይቀነሱ የሚለው ሐሳብ ዛሬም ድረስ እያከራከረ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ኣማራጮችንም በተመለከተ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ኣካዳሚ በ1973 ዓ.ም. ተመሳሳይ ድምፅ ያላቸው ፊደሎች ከገበታው ላይ ተቀንሰው በኣንድ ፊደል ብቻ ይወከሉ የሚል ሲሆን፣ የቤተ ክሕነት ሊቃውንት ኣቋም ደግሞ ፊደላት የፈጣሪን ቸርነት የሚገልጹ እና ከእሱ የተገኙ ስለሆኑ ሁሉም ጠንቅቆ ሊጽፋቸው ይገባል እንጂ በፍጹም ሊቀነሱ አይገባም ነው። ፊደላቱ በሙሉ መንፈሳዊ፣ ተፈጥሯዊና ሙያዊ ትርጓሜ ስላላቸው ያንን ያጣሉ በማለት" ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ ይገልጻሉ። የኣብነት (ቄስ) ትምህርት ቤቶች ትኩርት መነፈግንም የሚጠቅሱ ኣሉ። [1,159] Archived ጃንዩዌሪ 18, 2022 at the Wayback Machine

፱. ከ1980 ዓ.ም. ወዲህም እነዚሁ ቀለሞች በዶ/ር ኣበራ ወደ ኮምፕዩተር ስለገቡ የግዕዝ ፊደላችንን የኣጋጠመው ችግር የለም። ይህ በእንዲህ እንዳለ የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል በተቀነሱና በተቀነጠሱ ፊደላት “ኣማርኛ መዝገበ ቃላት” በ፲፱፻፺፫ ዓ.ም. እንዲሁም “ክብረ ነገስት ግእዝና ኣማርኛ” መጽሓፍት በ፲፱፻፺፬ ዓ.ም. ኣትሟል። በመጽሓፎቹ ርዕሶች “ኣማርኛ”፣ “ነገስት”ና “ግእዝ” ተብለው የቀረቡት “ዓ”፣ “ሥ” እና “ዕ” ከተቀነሱት ቀለሞቻቸው ውስጥ የተካተቱ በመሆናቸው ነው። እነዚህ ቍርጥራጮች ግን የዓማርኛ ፊደሎች ኣይደሉም። ክርክሩ በኣይቀነስ ባዮች ምክንያታዊ ኣሸናፊነት ማለቅ ሲገባው እንደቀጠለ ኣለ። [1,160] [1,161] [1,162] [1,163] [1,164] Archived ኤፕሪል 12, 2019 at the Wayback Machine [1,165] Archived ሴፕቴምበር 14, 2021 at the Wayback Machine [1,166] [1,167] ይህ ሁሉ ሲደረግ የዩኒኮድ ዓማርኛ ቀለሞች ኣልተቀነሱም። ፲. ለብዙ መቶ ዓመታት በውጭ ኣገራትና ኢትዮጵያ ውስጥ በግዕዝ ፊደላችን ሲጠቀሙ የነበሩ ማተሚያ ቤቶች ፊደል ሲቀንሱ ኣልሰማንም። ፲፩. ይህ የተዛባ የቅነሳ ኣጠቃቀም የመንግሥትም ፍላጎት ይመስላል። ምክንያቱም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዓይነት ተቋማት ፊደል መቀጠሉን ተዉት እንጂ በመቀነሱ ስለቀጠሉበት ነው። የግዕዝ ፊደል ትክክለኛ ኣጠቃቀም እያለ በተቀነሱና በተቈራረጡ ነገሮች መጠቀም መቀጠል በኮምፕዩተር ዘመን የሚያስከትለው ኪሳራ ቀላል ኣይደለም። ለምሳሌ ያህል በታይፕራይተር ዘመንና ይኸንኑ መሣሪያ ኮምፕዩተራይዝ የኣደረጉት ኣራት ነጥብን ሲከትቡ የነበሩት ሁለት ባለ ሁለት ነጥቦችን በመጠቀም ነበር። ዶ/ር ኣበራ ግን ለኣራት ነጥብ ከመነሻውም ኣንድ ስፍራ ስለመደቡለት ከዩኒኮድ በፊትም ይሁን በኋላ ፊደሉ የእራሱ የኮምፕዩተር ቍጥር ወይም ኮድ ኣለው። [1,168] ጥቂት ኣዳዲስ ፊደል ቀናሾች ወይም የግዕዝ መክተቢያ ኣቅራቢዎች ኣራት ነጥብን ከሁለት ባለ ሁለት ቀለሞች ማስከተብ ስለጀመሩ ጽሑፎቹ ኣራት ነጥብ የላቸውም። በኣሁኑ ጊዜ በብዙ ሚሊዮን የሚቈጠሩ ኢንተርኔት ላይ የኣሉ ኣራት ነጥብ የሌላቸው ጽሑፎች ማለቂያ የሌላቸው ናቸው። (የማለቂያን ቅኔነት የሚገባቸው ያውቁታል።) እነዚህን ስሕተቶች እየተከታተሉ ማረም ኣስቸጋሪ ስለሆነ ስሕተቶቹ እንዳይቀጥሉ ሁላችንም መረባረብ ይኖርብናል። ሁለት ነጥቦች መካክል ተገብቶ ሁለቱን ብቻ በኣንድ መርገጫ መሰረዝ ከተቻለ መክተቢያውን ሆነ ፊደሉን ኣለመጠቀም ያዋጣል። ኣራት ነጥብ በሌላቸው ቀለሞች የተጻፉ ብዙ መጽሓፍትም ስለኣሉ ሰዉ በኣወናባጆች ወደኋላ እየተመለሰ ነው። ይህ የምልክት ቅነሳ ያስከተለው ችግር ነው። የግዕዝ ፊደላችን እንደ ቻይናው ሥዕሎች የሚሳሉበት ስለኣልሆነ [1,169] በሺዎች የሚቈጠሩ ኣይደለም። [1,170] ፲፪. ፊደል መቀነስ ፊደላችን ላይ የተቃጣ ዘመቻ ነው። [1,171] [1,172] Archived ኤፕሪል 4, 2023 at the Wayback Machine

፲፫. ቀደም ብለው በዶክተሩ ለዩኒኮድ የተለገሰውን ፊደል [1,173] ኣስጥለው የተቈራረጡ የአማርኛ ፊደል [1,174] ለዩኒኮድ የኣቀረቡት ተሸንፈዋል። ቀደም ብለው በዶክተሩ ለዩኒኮድ የተለገሰውን ፊደል ኣስጥለው የተቀነሱ ፊደላትን [1,175] ለመቀጣጠል ለዩኒኮድ ለማቅረብ የኣቀዱት በሁለተኛ ዙር ጥፋት የኣቀዱትም ተሸንፈዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ቀደም ብሎ ለአማርኛ ታይፕራይተር ሲባል ፊደል ይቀነስ የተባለውን ክርክር የቀጠሉበት ስለ ዶክተር ኣበራ ሥራ ያልሰሙት እንደእነ የኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ ተቋም የኣሉት ነበሩ። [1,176] ወደፊት ኮምፕዩተሩ ዓረፍተ ነገርን በማረም ትክክለኛውን ሆኄ እንዲያስቀምጥ እናደርጋለን። መጻፍ የማይፈግጉ ለኮምፕዩተሩ ነግረውት ይጽፋል። ፲፬. "ቋንቋ"ን በ"ቁዋንቁዋ" መጻፍ ኮምፕዩተሩ ቀለሞቹን የሚያስቀምጥባቸውን ሥፍራዎች ከማስጨመር ሌላ ወረቀትንና ጊዜ ያስባክናል። "ቋንቋ"ን "ቁዋንቁዋ" በሚመስል ድምጽ ማንበብ እንኳን የፊደሉና የዓማርኛ ቋንቋ ሥርዓት ኣይደሉም። "ቁዋ" እንደ "ቋ" እንዲጻፍና እንዲነበብ ማስገድድ የኣምባገነኖች ፍላጎት እንጂ የፊደሉና የቋንቋው ኣይደሉም። ፲፭. ዶክተር ኣበራ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው ፓተንቶች ሲያገኙባቸው ቴክኖሎጅው በዓዋቂዎች ተጠንቶና ተፈትሾ ነው። ከእዚሁ ጋር የተያያዙ ኣዳዲስ ኣጠቃቀሞች ለግዕዙ ቀርበዋል። ለምሳሌ ያህል "ቋንቋ" የሚለው ቃል እንዲፈለግ ለኢንተርኔት ሲቀርብ ብዙ ቃላቱን የያዙ ጽሑፎችን ማግኘት ሲቻል ቃሉን በ"ቁዋንቁዋ" የሚጽፉ ከኣሉ ፍለጋው ሁለቴ እንዲደረግ ያስገድዳል። ስለዚህ ለታይፕራይተር ሲባል የቀረበ ክርክር ከኋላቀር መሣሪያው ጋር መቅረት ኣለበት። ዶ/ር ኣበራ ሞላ ከታዋቂ የዓለም ሳይንቲስቶች ኣንዱ ናቸው። [1,177]

የግዕዝ ቁምፊዎች ለማስተካከል

ቁምፊ (Typeface) ኣንድ ዓይነት ቅርጽ የኣሏቸው የፊደል ቀለም (Font) ቤተሰብ ነው።

ድንጋይ፣ ብራናና ወረቀት ላይ በእጅ ሲጻፉ የነበሩት የግዕዝ ቀለሞች በማተሚያ መሣሪያዎች እ.ኤ.ኣ. ከ1513 ጀምሮ ሲጠቀሙ ቆይተዋል። [1,178] [1,179] በ፲፱፻፳፭ ዓ. ም. ግድም የጽሕፈት መሣሪያ ተፈጥሮ ለቢሮ ሥራዎች ጠቅሟል። ግዕዝ ወደ ኮምፕዩተር ሳይገባ ለኢትዮጵያ ጽሑፍ መበልጸግ ትልቁን ድርሻ የኣበረከተው የማተሚያ መሣሪያ ሳይሆን ኣልቀረም። የግዕዝ ወደ ኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ በፊደሉ መግባት በተለይ የዓማርኛ ጽሑፎችን እንዲስፋፉ ጠቅሟል። ፊደሉ ከቴክኖሎጅው ጋር እንዲራመድ መገንዘብ ስለኣለብን ኣንዳንድ ነጥቦች ከእዚህ በታች ቀርበዋል።

፩. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ዶክተሩ የቁምፊውን መጠን በግምት ኣስቀመጡት እንጂ መደብ ኣላወጡለትም። ፪. በኣሁኑ ጊዜ ሕዝቡ በግዕዝ ፊደል በብዛት መጽሓፍት እየጻፈ ስለሆነ እየተደሰትን ነው። ሆኖም ጽሑፎች እየታተሙባቸው የኣሉት ቁምፊዎች መልኮች የተለያዩና ኣብዛኛዎቹ የተሳሳቱ ስለሆኑ መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ከግዕዝኤዲት ፕሮግራሞች ጋር እየተሸጠ የኣለው የዶ/ር ኣበራ ሞላ ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ (GeezEdit Unicode) ቁምፊ ወደ ትክክለኛው የቀረበ ነው። [1,180] ይኸን ቁምፊ ከተጠቀሙበት መካከል ዶ/ር ኣክሊሉ ሃብቴ በ፳፻፱ ዓ.ም. ያሳተሙት ባለ 629 ገጾች "የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ታሪክ" መጽሓፍ ኣንዱ ነው። [1,181] በፊደሉ ለብዙ ዓመታት እየተጠቀሙበት የኣሉት የኣቶ ኣብርሃ በላይ ኢትዮሚዲያ ገጾችም ኣሉ። [1,182] በ፳፻፲፩ ዓ.ም. ሰይፉ ኣዳነች ብሻው በግዕዝኤዲት ፕሮግራም በመጠቀም "የምኒልክ ጥላ" መጽሓፍ ጽፈዋል። በጽሑፋቸውም ዶክተር ኣበራ ስለ ሆኄያት መልኮች በተለይ የ"ጨ" ባለሁለት እግርነት እውነታ ተቀብለዋል። ፫. መጽሓፍ በኮምፕዩተር ሲታተም ቁምፊውን ኣስቀድሞ መወሰን ይጠቅማል። ምክንያቱም በኣንዳንድ ኣስቀያሚና የተሳሳቱ የፊደል መልኮች የተጻፉ ጽሑፎች ማንበብ ኣያጓጓም። [1,183] Archived ዲሴምበር 22, 2017 at the Wayback Machine ፬. ኣንድ የግዕዝ ዩኒኮድ ቁምፊ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች እንደኣሉት ማጣራት የደራሲው ሥራ ነው። ምክንያቱም ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው የማተሚያ ቤቶቹን ኃላፊነት ለደራሲዎች ስለሰጡ ኣዲሱን ቴክኖሎጂ መማር ኣስፈላጊ ስለሆነ ነው።

፭. ኣንድ በግዕዝ ዩኒኮድ ቁምፊ የሚጠቀም ደራሲ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች መክተብ መቻሉን ማጣራት የደራሲ ሥራ ነው። ምክንያቱም ዶክተሩ ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው የማተሚያ ቤቶቹን ኃላፊነት ለደራሲዎች ስለሰጡ ኣዲሱን ቴክኖሎጂ መማር ኣስፈላጊ ስለሆነ ነው። ፮. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ሲያደርጉ ዶክተሩ በመደበኛነት (Standard) የተጠቀሙት የኢትዮጵያ ቍጥር ፩ ፊደል ነው። እ.ኤ.ኣ. በ1988 በዶክተሩ ከፖስትእስክሪፕት (Postscript) ፊደላቸው የተሠራ የመጀመሪያው ትሩታይፕ (TrueType) የግዕዝ ፊደልና ፊደላቸው ነው። ለሥራቸው መሳካት የኮሎራዶው ኩባንያዎች ከዶክተሩ ባለውለታዎች ዋነኞቹ ናቸው። ይህ እነ ብርሃንና ሰላምና የመሰሉ የኢትዮጵያ ማተሚያ ቤቶች ሲጠቀሙበት የነበረው ቁምፊ ወደ ታይምስ ሮማን (Times Roman) የእንግሊዝኛ ቁምፊ የቀረበና ተመሳሳይ ቢሆንም ከላቲኑ ጋር ሲወዳደር የግዕዝ ፊደል ተለቅና ደመቅ የኣለ ነው። [1,184] ኣብዛኛዎቹ የዓማርኛና እንግሊዝኛ መጽሓፍት ሲጻፉ የነበሩት በእነዚህ ቁምፊዎች ነበር። ይህ የግዕዝ ቁምፊ መልክ ወደጎን ቀጠን ብሎ ወደታች የወፈረ ነው። በማተሚያ ቤቶቹና ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ሲታተሙ የነበሩት መጽሓፎች የፊደል መጠን (Points) ከ10 እስከ 12 ነበር። ፰. ኣንድ የግዕዝ ቁምፊ ቢያንስ ከኣንድ ተመጣጣኝ የእንግሊዝኛ ቁምፊ ጋር መቅረብ ይኖርበታል።

፱. ኮምፕዩተሮችና የእጅ ስልኮች ላይ በቀላሉ ማየት እንዲቻል የሚቀርቡ ጽሑፎች ደቦልቦል በኣሉ ቁምፊዎች ነው። እነዚህን ለመጽሓፎችና ለመሳሰሉት መጠቀም ኣስፈላጊ ኣይደለም። ምክንያቱም ትላልቅ ስለሆኑ በዛ የኣሉ ስፍራዎችንና ወረቀቶችን ስለሚያስባክኑና ጥቅማቸው ለኅትመት ስለኣልሆነ ነው። ፲. ኣንዳኣንድ ሰዎች ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ማድረግ ፊደሉን መሥራትና ማቅረብ ይመስላቸዋል። ይህ ከኣለማወቅ የመጣ ስሕተት ነው። በፓተንት የሚጠበቀው ኣዲስ የሆነውና ፊደሉን በኮምፕዩተር መጠቀም የኣስቻለውን ቀደም ብሎ ያልነበረውን ዘዴ ነው እንጂ ከዘዴው ጋር ለሚቀርቡት ፊደላት ኣይደለም። ፲፩. ኣንዳኣንድ ሰዎች ግዕዝን ኣሜሪካ ፓተንት ማድረግ ፓተንቱን ወይም ፊደሉን ለኣሜሪካ መስጠት ይመስላቸዋል። ይህ ከኣለማወቅ የመጣ የፈጠራ ወሬ ነው። ፲፪. ግዕዝን ኮምፕዩተራይዝ ኣድርገው ከትክክለኛው ቁምፊ ጋር ዶክተሩ ከኣቀረቡ በኋላ ከአማርኛው ቅጥልጥል ፊደል እስከኣልተሟሉና የተሳሳቱ ቀለሞች የኣሉዋቸውን ቁምፊዎች በነፃና በሽያጭ የሚያቀርቡ ኣሉ። ይኸንን መረዳትና ማስተዋል የተጠቃሚው ኃላፊነት ሲሆን ኣንባቢው ስሕተቶችን እያየ ዝም ማለቱ ደረጃቸው ለኣዘቀጡ በኮምፕዩተር ለቀረቡ ጽሑፎች ኣስተዋጽዖ እያበረከተ ነው።

፲፫. ኣንድ ኣንባቢ ኮምፕዩተር፣ የእጅ ስልክና የመሳሰሉት ላይ የሚመለከተው የግዕዝ ዩኒኮድ ፊደል መሣሪያው ላይ በኣለው ፊደል ነው። ፊደሉ ትክክል ከኣልሆነ ትክክል ኣለመሆኑንንም ላይረዳ ይችላል። ለምሳሌ ያህል የ"ጨ" ቀለበቶች ሁለት ናቸው ሲባልና ቢያነብ ባለ ሁለት ቀለበቶች ትክክለኛ ፊደል ከሌለው ፊደሉን የሚያነበው ሦስት ቀለበቶች በኣሉት የተሳሳተ ፊደል ነው። የዶክተሩ የግዕዝ ቁምፊ ከኣሥር ዓመታት በላይ እዚህ የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንትና ማመልከቻው ውስጥ ኣሉ። [1,185] ፲፬. ኣንድ በቅርቡ የተለቀቀ ቁምፊ ውስጥ የዓይኑ "ዓ" ፊደል መልክ ወደ ኣረቡ ዘጠኝ (9) የቀረበ ሲሆን የሌላው "ፃ" መስመሩ የኣለው በ"ዓ" ክብ ውስጥ ነው። ፲፭. ዶክተር ኣበራ ሞላ ከዓለም ፊደል ሠሪዎች ኣንዱ ናቸው። [1,186] ፲፮. በማተሚያ ቤቶች ከታተሙ የግዕዝ ቁምፊዎች የሚከተሉት ይገኙበታል። [1,187]

፲፯. በተሳሳተ ፊደል የተጻፈ በመሆኑ ኣስተማማኝ የኣልሆነ ጽሑፍ ምሳሌ እዚህ ኣለ። [1,188] ከእዚህ ጽሑፍ ኣንድ ሁለት ኣንቀጾች ኮፒ ተደርገው http://www.freetyping.geezedit.com ገጽ ላይ ቢለጠፉ ችግሮቹን መመልከት ይቻላል። ፲፰. ኣንድ ቆንጆ የቁም ፊደል አጣጣል እዚህ ኣለ። [1,189] ፲፱. በግዕዝ ፊደል ወግ ስምንተኛው ፊደል የሚቀርበው ግዕዙ ወይም ራብዑ ላይ መስመር በመጨመር ነው ። "ፏ" የተሠራው መስመሩን "ፋ" ኣንገት ላይ በመጨመር ነው። በኣሁኑ ጊዜ ብዙዎቹ ቅጣዩን በስሕተት ከታች ሲያቀርቡ ኣንዱ በቅርቡ "ፍ" ላይ ኣድርጎታል። መሳሳታቸውን ከቆዩ ጽሑፎች ውስጥ ማየት ይቻላል። እንዲህ ዓይነቶችን ስሕተቶች ስር ሳይሰዱ ማረም ከኣልተቻለ ዛሬ "ኣበበ"ን እሞታታለሁ እንጂ በ"አበበ" ከኣልሆነ ኣልጽፍም እንደሚሉት ጥቂቶቹ በኋላ በትምህርት ማቃናት ሊያስቸግር ይችላል። ፳. ኣንድ የግዕዝ ቁምፊ ቢያንስ ኣንድ ኣብሮት የኣለ የእንግሊዝኛ ፊደል ጋር መቅረብ ይኖርበታል። ስለዚህ ለሰው የሚቀርበው የላቲን ፊደልም እንደግዕዙ የፊደል ሠሪው መሆን ይገባዋል። የግዕዙና የላቲኑም ፊደላት ቅርጾች የተቀራረቡ መሆን ይኖርባቸዋል።

፳፩. ዩኒኮድ ለፊደላቱ መደብ ሰጠ እንጂ ፊደል ኣላቀረበም። የግዕዙ ፊደል ኮምፕዩተርና የእጅ ስልክ ላይ ከሌለ የግዕዝ ፊደል ኣይታይም። የሚታየውም እንደፊደሉ ሊለያይ ይችላል። ስለዚህ ኣንድ ተጠቃሚ የሚጠቀምበትን መሣሪያ ላይ ያለውን የፊደል ስምና መልክ ማወቅ ኣለበት። ፳፪. ኣንድ የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚ ሁሉንም የግዕዝ ቀለሞች ቅርጾች ማወቅ ይጠበቅበታል። በኣሁኑ ጊዜ ግን ሁሉንም የዓማርኛ ቀለሞች እንኳን የማይለዩ ኣሉ። ፳፫. ከእዚህ በፊት ተዉ እያልናቸው በታይፕራይተር ዓይነት ፊደል ተታልለው መጽሓፍት ሲጽፉ ከርመው የተበሳጩ ኣሉ። ኣሁንም በተሣሣቱ የዩኒኮድ ፊደሎችና የዓማርኛ መጻፊያዎች እየተጠቀሙ እራሳቸውንና ዓማርኛውን እየጎዱ የኣሉ ኣሉና ይታሰብበት። ፳፬. የግዕዝ ፊደል ቅርጾችና ምንነት ምሳሌዎች የሚከተሉት ናቸው። [1,190] Archived ጁን 6, 2023 at the Wayback Machine

፳፭. የግዕዝ ኣኃዞች እያንዳንዳቸው ከላይና ከታች ሰረዞች ኣሏቸው። የኮምፕዩተሩ እስክሪን ላይ የሚታየውና የሚታተመው ኣንድ ፊደል ነው። የፊደሉ መጠን በኣነሰ ቍጥር ጥራቱ እየቀነሰ መስመሮቹ ኣንድ መስለው ይታያሉ። ፊደሉ የዶክተሩ GeezEdit Unicode ከሆነ ጽሑፉን ከእዚህ ወስዶ ወርድ ላይ ለጥፎ በማሳደግ ማረጋገጥ ይቻላል። እንዲህም ሆኖ ቍጥሮቹ ጎን ለጎን ሲሆኑ ሰረዞቹ እንዲገናኙ የተሠሩና የሚቀጣጠሉ በነፃ የሚታደሉ የተሣሣቱ ፊደሎች ኣሉ። ለእዚህ ነው በነፃ የሚታደሉትን ሁሉ መጠቀም የማያዋጣው። ፳፮. ኣንድን የግዕዝ ፊደል ጽሑፍ እንደወርድ የኣሉ ቁሶች ውስጥ ኣቅልሞ GeezEdit Unicode የሚለውን ፊደል በመምረጥ ወደ ፊደሉ መቀየር ይቻላል። ይህ እንግሊዝኛውንም ወደ ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ፊደል ያስቀይራል። ፳፯. ለዊንደውስንና ኣይፎን የሚሸጡት ግዕዝኤዲት ፕሮግራሞች የሚጠቀሙት ኣንድ ዓይነት በሆነው ግዕዝኤዲት ዩኒኮድ ፊደል ነው። ይህ ፊደል እ.ኤ.ኣ. በ1989 ግድም ለዩኒኮድ የተለገሰው የመጀመሪያ የግዕዝ ትሩታይፕ ፊደል ነው። ፳፰. የግዕዝ ሳልስ፣ ኃምስና ስምንተኛ ቀለሞች ቅጥያዎች የ"ጨ" ሦስተኛው ባዶ እግር ላይ ይቀጠላሉ እንጂ የሌሉትን ቀለበቶች ኣያስፈቱም።

፳፱. የ"ጠ" እና "ጨ" ቤቶች እርባታ ቀለሞች ልዩነቶች በሁለት ቀለበቶች መኖር ብቻ ነው።

ትርጕሞች ለማስተካከል

 
ግዕዝ በኮምፕዩተር በዶ/ር ኣበራ ሞላ፣ ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. Ethiopic Computerization by Dr. Aberra Molla, Ethiopian Review Magazine, Page 25, Jan, 1991
 
ግዕዝ ዩኒኮድ (Unicode) ፲፱፻፺፭ ዓ.ም.
 
ኣንገነጠልም፣ ፲፱፻፹፯ ዓ.ም.
 
የኣክሱም ሓውልት፣ ፳፻፩ ዓ.ም.
 
ኢምዩን ደፊሸንሲ ፈውስ ፲፱፻፷፱ ዓ.ም.
 
ኣንዳንዶቹን ከ፲፱፻፹ ዓ.ም. ጀምሮ
 
መድኅን መመርመሪያ፣ ፲፱፻፸፰ ዓ.ም. https://patents.google.com/patent/US4501816A/en?oq=4501816+
 
የሞዴት ፊደል ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. (ModEth Ethiopic TrueType Typeface) Ethiopian Review, 1991
 
አቡጊዳ ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. (Ebugida Sorting Order) Ethiopian Review, 1991
 
ዶ/ር ኣበራ ሞላ ፲፺፻፹፭/1992 ፩ https://www.facebook.com/GeezEdit/videos/433568700036371/UzpfSTEzMjAwNTEwNjg1OTQwMDoyNDk2MTU0MzAwNDQ0NDU3/
 
ዶ/ር ኣበራ ሞላ ፲፺፻፹፭/1992 ፪ https://www.facebook.com/GeezEdit/videos/433568700036371/
 
ግዕዝ በኳርክኤክስፕሬስ ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. Ethiopic in QuarkeXPress, 1994
 
GeezEdit Online 2011 ግዕዝኤዲት ፳፻፬ ዓ.ም. http://freetyping.geezedit.com
 
GeezEdit 2014 (iPhone 6) ግዕዝኤዲት (ለእጅ ስልክ) ፳፻፯ ዓ.ም.
 
Amharic Tips 2015 ቅምሻዎች ፳፻፯ ዓ.ም.
 
Amharic Tips 2015 ቅምሻዎች ፳፻፯ ዓ.ም.
 
ModEth 1989 ሞዴት የፊደል ገበታ ፬፣ ፲፱፻፹፪ ዓ.ም.
 
የ"አ" ቀለም ድምጽ እንደ "አረ"፣ "ኑአር" እና "አርዝ" (Earth) ነው።
 
ModEth Ad 1990 ሞዴት ማስታወቂያ
 
Ethiopic Language Character Sets 2006 የግዕዝ ፊደል ተጠቃሚ ቋንቋዎች ምሳሌ ፲፱፻፺፱ ዓ.ም.
 
Type Geez with one and two keystrokes. US20090179778 Patent Application, 2009 ፳፻፪ ዓ.ም.
 
ModEth Ethiopic First Typeface, March, 1989. ሞዴት የመጀመሪያው ግዕዝ ፊደል፣ ሰምና ወርቅ መጽሔት፣ የካቲት፣ ፲፱፻፹፩ ዓ.ም.
 
የግዕዝ ኣሥር ቤት ቍጥሮች ከ፲፱፻፹ ዓ.ም. ጀምሮ Ethiopic Base Ten Numerals, 1987
 
የ“ኣብሻ” ሥርዓት ኣከታተብ “ABSHA System” USA Patent Numbers 9,000,957 and 9,733,724
 
የፊደል ቅርጽ ይከበር! Ethiopian Review, 1991
 
በስሕተት ትርጕም ኣናበላሽ! ፳፻፱ ዓ.ም. 2017
 
መጫፈ ቁልቁሉ ኣፋን ኦሮሞ፣ © የኢትዮጵያ መጽሓፍ ቅዱስ ማኅበር፣ ፲፱፻፹፬ ዓ.ም.፣ (ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ፩) Genesis 1, Ethiopic Oromo Bible, (© The Bible Society of Ethiopia, 1993)
 
ModEth 1988 Keys. ሞዴት የፊደል ቍልፎች ዓማርኛ የጽሕፈት መኪና ኣጠቃቀም ለሚያውቁ፣ ፲፱፻፹፩ ዓ.ም.
 
Ethiopic Zero, 1988. የግዕዝ ኣልቦ፣ ፲፱፻፹፩ ዓ.ም.
 
ኢትዮወርድ፣ ፲፱፻፹፰ ዓ.ም. የኮምፕዩተር ገጽ ሥዕል EthioWord, 1995. Acknowledgement Screenshot
 
ኢትዮወርድ፣ ፲፱፻፹፰ ዓ.ም. በኮምፕዩተር የታተመ ገጽ ሥዕል EthioWord, 1995. Acknowledgement Page Printout
 
ግዕዝ ተራጽሑፍ Ethiopic Text
 
ሁለተኛው የሞዴት ፊደል First Ethiopic TrueType ModEth Typeface
 
“የኤርትራ ህዝብ ትግል ከየት ወዴት!” መጽሓፍ። The book was typed with EthioEdit and typeset by Fettan Graphics Corp.
 
የኢትዮጵያ መሥሪያ ቤቶች የእውሸት የኣማርኛ ፊደል-፲፱፻፹፪ ዓ.ም. Printout of the fake Amharic typewriter glyphs in 1990 G.C.
 
ትክክለኛዎቹ የጨ፣ ጩ፣ ጪ፣ ጫ፣ ጬ፣ ጭ፣ ጮ እና ጯ ቀለሞች The Ethiopic "Che" orders
 
ግዕዝ Ethiopic, the ancient Ethiopian alphabet
 
“ዓቢይ” እንጂ “አቢይ”፣ “ኣቢይ”፣ “ዐቢይ”፣ ወይም “ዓብይ” ትክክል ኣይደለም።
 
Dr. Aberra Molla 2018 ዶ/ር ኣበራ ሞላ ፳፻፲ ዓ. ም. ከኢሳት ምናላቸው ስማቸው ጋር። https://ethsat.com/2018/05/esat-tikuret-minalachew-simachew-with-dr-abera-mola/
 
Dr. Aberra Molla 2019 ዶ/ር ኣበራ ሞላ ፳፻፲፩ ዓ. ም. ከJTV ዮሴፍ ገብሩ ጋር። https://www.youtube.com/watch?v=3IlHQfmr2H0&feature=youtu.be
 
Dr. Aberra Molla with Ethiopian Broadcasting Corporation, 1-31-2019 ዶ/ር ኣበራ ሞላ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር፣ https://www.facebook.com/watch/?v=386895698538690
 
2019 ዶ/ር ኣበራ ሞላ ፳፻፲፩ ዓ. ም. ከJTV ዮሴፍ ገብሩ ጋር። Jossy in Z House SHOW interview with Dr. Aberra Molla https://www.youtube.com/watch?v=7jLq0ZgpG_Y
 
2019 ፳፻፲፩ ዓ. ም. ከJTV ዮሴፍ ገብሩ ጋር። 'ኣንድን ከብት የመጣል ሥልጣን ያለው የእንስሳት ሃኪም ብቻ ነው' ዶ/ር አበራ ሞላ https://www.youtube.com/watch?v=aHs5y73qRK8&feature=youtu.be
 
2018 HON. MIKE COFFMAN of US Congress CONGRATULATING DR. ABERRA MOLLA ዕውቅና ፳፻፩ ዓ.ም. https://www.congress.gov/congressional-record/2018/08/24/extensions-of-remarks-section/article/E1177-3
 
የዶ/ር ኣበራ ሞላ የኢትዮጵያ ፓተንቶች ምሳሌ ቊጥር ፻፳፫፣ ጥር ፩ ቀን ፳፻፲፩ ዓ.ም. An Example Ethiopian Patent No. 193 to Dr. Aberra Molla, December 20, 2018
 
መጀመሪያው የሞዴት ኮምፕዩተር መስኮት ላይ የግዕዝ ፊደል፣ ፲፱፻፹ ዓ.ም. The First ModEth Amharic Ethiopic Computer Screen Font, MS DOS 1987
 
ከዩኒኮድ መደብ በኋላ የዶ/ር ኣበራ የግዕዝ ኣሥር ቤት ኣኃዞች። Post Unicode Ethiopic Base Ten Numerals
 
ከዶ/ር ኣበራ ሞላ የዩናይትድ እስቴትስ ፓተንቶች ኣንዱ - 10133362። An example of Dr. Aberra Molla's patents - USA Patent Number 10133362
 
ኢትዮጵያ ETHIOPIA (ፊደልህን ኣስተውል።)
 
የግዕዝ ቍጥሮች ዩኒኮድ ውስጥ የኣሉት በፊደልነት ቢሆንም እንጠቀምባቸው።
 
ኣዲሶቹ ኣሥሩ የግዕዝ ኣኃዞች፣ The Novel Ten Ethiopic Digits
 
"ስመኘው ፏፏቴ" እና "ዓቢይ ሓይቅ"፣ ሓምሌ ፳፻፲፪ ዓ.ም. "Semegnew Falls" and "Abiy Lake", July 28, 2020
 
"ክትባት" ኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ ክትባት መሥራት ኣለባት። 4-27-2021
 
ዓማርኛ በነፃ መክተቢያ ድረገጽ Patented Free Amharic Typing Page http://ethiopic.com

የውጭ መያያዣዎች ለማስተካከል

ዋቢ ለማስተካከል

  1. ^ "GeezEdit". Geezedit.com. Archived from the original on 2020-12-04. በ2016-01-05 የተወሰደ.
  2. ^ እንግሊዝኛ አማርኛ መዝገበ ቃላት 1972
  3. ^ ፍቅር እስከ መቃብር