ግዕዝ ፡ በአፍሪካ ቀንድ ፡ በኢትዮጵያና ፡ በኤርትራ ፡ በጥንት ፡ የተመሠረተና ፡ ሲያገለግል ፡ የቆየ ፡ ቋንቋ ነው። የግዕዝ ፡ አመጣጥ ፡ በግምት ፡ የዛሬ ፡ ፫ ፡ ሺህ ፡ ዓመት ፡ ከየመን ፡ እና ፡ ደቡብ ፡ አረቢያ ፡ በመነሣትና ፡ ቀይ ፡ ባሕርን ፡ በመሻገር ፡ በኤርትራ ፡ እና፡ ሰሜን ፡ ኢትዮጵያ ፡ ውስጥ ፡ ከሰፈሩ ፡ የተለያዩ ፡ የሳባውያን ፡ ነገዶች ፡ ቋንቋና ፡ በጊዜው ፡ ሰሜን ፡ ኢትዮጵያ ፡ ይነገሩ ፡ በነበሩ ፡ ቋንቋዎች ፡ ዘገምተኛ ፡ ውኅደት ፡ ነው።[1]አክሱም ፡ መንግሥትና ፡ በኢትዮጵያ ፡ መንግሥት ፡ መደበኛ ፡ ቋንቋ ፡ ነበር።

ኦሪት ፡ ዘፍጥረት ፡ ፳፱ ፡ በግዕዝ ፡ መጽሐፍ ፡ ቅዱስ

ግዕዝ ፡ ከአማርኛና ፡ ሌሎች ፡ ኢትዮ-ሴማዊ ፡ ቋንቋዎች ፡ ጋር ፡ ሲወዳደር ፡ «ንጹሕ» ፡ ሴማዊ ፡ ቋንቋ ፡ ነው።[1] ግዕዝ ፡ እስከ ፡ ፲ኛው ፡ ክፍለ-ዘመን ፡ መጀመሪያ ፡ ድረስ ፡ ዋነኛ ፡ የመግባቢያ ፡ ቋንቋና ፡ ልሳነ ፡ ንጉሥ ፡ ነበር።[1] ከ ፲፫ኛው ፡ ክፍለ ፡ ዘመን ፡ ጀምሮ ፡ ግን ፡ ሙሉ ፡ በሙሉ ፡ መነገር ፡ አቁሞ ፡ በሰሜን ፡ ኢትዮጵያ ፡ በትግርኛ ፡ እንዲሁም ፡ በማዕከላዊው ፡ ክፍል ፡ ደግሞ ፡ በአማርኛ ፡ ተተካ።[1] ዛሬ ፡ በኢትዮጵያ ፡ ኦርቶዶክስ ፡ ተዋሕዶ ፡ ቤተክርስቲያን ፡ ሥነ-ስርዓት ፡ እንዲሁም ፡ በኤርትራ ፡ ኦርቶዶክስ ፡ ተዋሕዶ ፡ ቤተክርስቲያን ፣ በኢትዮጵያ ፡ ካቶሊክ ፡ ቤተክርስቲያን እና ፡ በቤተ-እስራኤል ፡ ሥነ-ስርዓቶች ፡ ይሰማል። በሰሜን፡ ኤርትራ ፡ የሚገኘ ፡ ትግረ ፡ የሚባል ፡ ቋንቋ ፡ ከሁላቸዉ፡ የሰሜን ፡ኢትዮጵያ ፡ቋንቋዎች፡ ለግእዝ ፡ በቅርብ ፡ ይዛመዳል ፡ እና። ትግረ ፡ ፸ በመቶ ፡ ግእዝ ፡ ነዉ ፡ እና ፡ በመቀጠል ፡ ትግርኛ ፡ እና ኣማርኛ።

ቋንቋው ፡ የሴማዊ ፡ ቋንቋዎች ፡ አባል ፡ እየሆነ ፡ በደቡብ ፡ ሴማዊ ፡ ቅርንጫፍ ፡ ውስጥ ፡ ይካተታል። ደቡብ ፡ ሴማዊ ፡ በመባሉ ፡ ግዕዝ ፡ የሣባ ፡ ቋንቋ ፡ ቅርብ ፡ ዘመድ ፡ ነው። ግዕዝ ፡ የተጻፈው ፡ በግዕዝ ፡ ፊደልአቡጊዳ ፡ ነው። ይህም ፡ ፊደል ፡ ደግሞ ፡ ዛሬ ፡ ለአማርኛ ፣ ለትግርኛ ፡ እና ፡ ለሌሎችም ፡ ቋንቋዎች ፡ ይጠቀማል። በመላውም ፡ የአፍሪቃ ፡ አህጉር ፡ ውስጥ ፡ የመጀመሪያውና ፡ ብቸኛ ፡ አፍሪቃዊ ፡ የራሱን ፡ ፊደላት ፡ የያዘ ፡ ቋንቋ ፡ ሲሆን ፣ በዓለምም ፡ ላይ ፡ ዋናና ፡ የስልጣኔ ፡ አራማጅ ፡ ከሚባሉት ፡ ቋንቋዎች ፡ አንዱ ፡ ነው።

በግዕዝ ፡ ጽሕፈት ፡ ፳፮ ፡ ፊደላት ፡ ብቻ ፡ ይጠቀሙ ፡ ነበር ፤ እነርሱም፦

ናቸው።

ሊቁ ፡ ሪቻርድ ፓንኩርስት ፡ እንደሚጽፍ ፣ አንድ ፡ ተማሪ ፡ በመጀመርያው ፡ አመት ፡ ፊደሉን ፡ ከተማረ ፡ በኋለ ፣ በሚከተለው ፡ አመት ፡ መጀመሪያይቱ ፡ የሐዋርያው ፡ የዮሐንስ ፡ መልእክትን ፡ ከአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግዕዝ ፡ ከትዝታ ፡ ለመጻፍ ፡ መማር ፡ ነበረበት። በሦስተኛው ፡ ደረጃ ፡ የሐዋርያት ፡ ሥራ ፡ በአራተኛውም ፡ መዝሙረ ፡ ዳዊት ፡ በግዕዝ ፡ ማስታወስ ፡ ነበረበት። ይህንን ፡ ከጨረሰ ፡ ታላቅ ፡ ግብዣ ፡ ይደረግና ፡ ልጁ ፡ ጸሐፊ ፡ ይሆን ፡ ነበር።

ብሪቲሽ ፡ ቤተ-መጻሕፍት ፡ (የእንግሊዝ ፡ አገር ፡ ብሔራዊ ፡ ቤተ-መጻሕፍት) ፡ ውስጥ ፡ ፰፻ ፡ የሚያሕሉ ፡ የድሮ ፡ ግዕዝ ፡ ብራናዎች ፡ አሉ።

በኢ.ኦ.ተ.ቤ. ፡ ትምህርቶች ፡ ዘንድ ፣ ግዕዝ ፡ የአዳምና ፡ የሕይዋን ፡ ቋንቋ ፡ ነበር። ፊደሉን ፡ የፈጠረው ፡ ከማየ አይኅ ፡ አስቀድሞ ፡ የሴት ፡ ልጅ ፡ ሄኖስ ፡ ነበረ። ከባቢሎን ፡ ግንብ ፡ ውድቀት ፡ በኳላ ፣ ከአርፋክስድ ፡ ወገን ፡ የዮቅጣን ፡ ልጆች ፡ ቋንቋውን ፡ እንደ ፡ ጠበቁት ፡ ይባላል። የዮቅጣን ፡ ልጅ ፡ ሣባ ፡ ነገዶች ፡ ከዚያ ፡ ቀይ ፡ ባሕርን ፡ አሻግረው ፡ ወደ ፡ ዛሬው ፡ ኢትዮጵያ ፡ ያስገቡት ፡ ይታመናል። እንዲሁም ፡ ካዕብ ፡ እስከ ፡ ሳብዕ ፡ (አናባቢዎችን ፡ ለመለየት) ፡ ወደ ፡ ፊደል ፡ የተጨመረበት ፡ ወቅት ፡ በንጉሥ ፡ ኤዛና ፡ ዘመን ፡ እንደ ፡ ነበር ፡ ይባላል።

ጀመረ ለማስተካከል

 
አንድ ፡ የግዕዝ ፡ ሰነድ ፡ ውዳሴ ፡ ማርያም (፲፰፻፷፯ (1867) ዓ.ም. ፡ ገደማ)

ግሥ ለማስተካከል

  • ግዕዝ - አማርኛ
  • ነገረ - ነገረ(ተናገረ)
  • ነገረት - ነገረች
  • ነገርከ - ነገርክ
  • ነገርኪ - ነገርሽ
  • ነገርኩ - ነገርሁ
  • ነገሩ - ነገሩ
  • ነገራ - ነገሩ (ሴ)
  • ነገርክሙ - ነገራችሁ
  • ነገርክን - ነገራችሁ(ሴ0
  • ነገርነ - ነገርን
  • ይነግር - ይነግራል
  • ትነግር - ትነግራለች
  • ትነግር - ትነግራለህ
  • ትነግሪ - ትነግሪያለሽ
  • እነግር - እነግራለሁ
  • ይነግሩ - ይነግራሉ
  • ይነግራ - ይነግራሉ
  • ትነግሩ - ትነግራላችሁ
  • ትነግራ - ትነግራላችሁ(ቅ.ሴ)
  • ንነግር - እንነግራለን
  • የእግዚአብሔር ስጦታ

የቱ

ምሳሌ ለማስተካከል

«ቃለ ፡ በረከት ፡ ዘሄኖክ ፡ ዘከመ ፡ ባረከ ፡ ኅሩያነ ፡ ወጻድቃነ ፡ እለ፡ ሀለው፡ ይኩኑ ፡ በዕለተ ፡ ምንዳቤ ፡ ለአሰስሎ ፡ ኲሉ ፡ እኩያን ፡ ወረሲዓን።» (መጽሐፈ ፡ ሄኖክ ፩ ፡ ፩)

ሄኖክ ፡ መጀመርያ ፡ ቃሎች ፡ በጽሕፈት ፡ በግዕዝ ፡ የጻፈ ፡ እንደ ፡ ነበር ፡ ስለሚባል ፣ ይህ ፡ ቃል ፡ በማንኛውም ፡ የሰው ፡ ልጅ ፡ ቋንቋ ፡ ከሁሉ ፡ አስቀድሞ ፡ የተጻፈ ፡ መሆኑ ፡ በብዙዎች ፡ የኢትዮጵያ ፡ ሊቃውንት ፡ ይታመናል።

ደግሞ ፡ ለማስተካከል

  • ኣበራ ፡ ሞላ - ከቅርብ ፡ ጊዜ ፡ ወዲህም ፡ እዚህ ፡ ገጽ ፡ ላይ ፡ እንደሚታየው ፡ ግዕዝን ፡ በኮምፕዩተር ፡ መጻፍ ፡ ተችሏል።

የውጭ ፡ መያያዣዎች ለማስተካከል

ማጣቀሻዎች ለማስተካከል

  1. ^ ዶ/ር ፡ አንበሴ ፡ ተፈራ ፣ «የኢትዮጵያ ፡ ብሔረሰቦችና ፡ ቋንቋዎቻቸው ፡ አጭር ፡ ቅኝት Archived ጁን 17, 2012 at the Wayback Machine»