ኮሮናቫይረስ

የቫይረስ ዐይነተ-ዐባል

ኮሮናቫይረሶች በአጥቢዎች እና በአዕዋፍ ላይ በሽታ የሚያስከትሉ የቫይረሶች ስብስብ ናቸው። ኮሮናቫይረሶች በሰዎች ላይ እንደጉንፋን ያሉ ቀለል ያሉ የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን እንዲከሰት ሲያደርጉ አንድ አንድ ጊዜ ደግሞ እስከ ሞት የሚያደርሱ እንደ ሳርስ ፣ መርስ ፣ እና ኮቪድ-19 ዓይነት ከባድ በሽታዎችን ሊያስከትሉ ይችላሉ። የሚያስከትሉት የበሽታ ምልክቶች በሌሎች እንስሶች ላይ የተለያዩ ናቸው። በዶሮዎች ላይ ለምሣሌ የመተንፈሻ አካላት በሽታ ሲያስከትሉ በላሞች እና አሳሞች ላይ ተቅማጥን ያስከትላሉ። እስካሁን ድረስ ሰዎችን የሚያጠቁትን ኮሮናቫይረሶችን የሚከላከሉ ወይም የሚያከሙ ክትባት ወይም የጸረ-ቫይረስ መድኃኒቶች የሉም።

ግኝት ለማስተካከል

ኮሮናቫይረሶች ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኙት እ.ኤ.አ 1960ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ነው።[1] መጀመሪያ የተገኙት በዶሮዎች ላይ ተላላፊ የብሮንካይቲስ ቫይረሶች እና በሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉንፋን የሚያስከትሉ ቫይረሶች ነበሩ። [2] ከዚያም በመቀጠል እ.ኤ.አ. 2003 እንደ SARS-CoV ፣ በእ.ኤ.አ. 2004 HCoV NL63 ፣ በእ.ኤ.አ. 2005 HKU1 ፣ በእ.ኤ.አ. 2012 MERS-CoV ፣ እናም በእ.ኤ.አ. 2019 SARS-CoV-2 (ወይም በቀድሞ አጠራሩ 2019-nCoV) ዓይነት ያሉ ተመሳሳይ ቫይረሶች ተገኝተዋል። ከነዚህም አብዛኛዎቹ ከባድ የመተንፈሻ አካላት ኢንፌክሽን አስከትለዋል።

ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል

  1. ^ Kahn, Jeffrey; McIntosh, Kenneth (November 2005), "History and recent advances in coronavirus discovery", Pediatric Infectious Disease Journal 24 (11): s223-s227, doi:10.1097/01.inf.0000188166.17324.60, https://journals.lww.com/pidj/Fulltext/2005/11001/History_and_Recent_Advances_in_Coronavirus.12.aspx 
  2. ^ "Human coronaviruses: insights into environmental resistance and its influence on the development of new antiseptic strategies". Viruses 4 (11): 3044–68. November 2012. doi:10.3390/v4113044.