ጉራጌ
ጉራጌ የኢትዮጵያ ብሔር ነው። ቋንቋቸው ጉራግኛ ከሴማዊ ቋንቋ የሚመደብ ሲሆን ብዛት ያላቸው የጉራጌ ብሔሮች አሉ። እነሱም፦ መስቃን፣ ሶዶ፣ ወለኔ፣ ሰባትቤት፣ ቀቤና፣ ዶቢ፣ እና ሌሎችም ይኖራሉ። አማርኛ ግን ለሁሉም መግባቢያቸው ነው። አንዳንድ የታሪክ አዋቂዎች ጉራጌ ከሰሜን ኢትዮጵያ " ጉራ" አካለጉዛይ፣ ኤርትራ ከሚባል ቦታ ለም መሬት ፍለጋ ወደ መሃል ኢትዮጵያ የፈለሰ ሕዝብ እንደሆነ ይናገራሉ፤ "ጉራጌ " የሚለው ስያሜም ከዚህ የተወሰደ ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ።
ጉራጌኛ የሚጻፈው በግዕዝ ፊደል ነው።
ታዋቂ ጉራጌዎችን ለመጥቀስ ያህል፡ ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ (የኢትዮጵያ የጦር ሚኒስቴር የነበሩ)፣ ዶ/ር [ፕሮፌሰር[ብርሃኑ ነጋ]]፣ አርቲስት መሐሙድ አህመድ፣ ደጅአዝማች በቀለ ወያ፣ አትሌት አሰፋ መዝገቡ፣[አለምፀሀይ ወዳጆ]፣ቴዲ አፍሮ፣አብረሃም ወልዴ ጎሳዬ ተስፋዬ አብነት አጎናፍር አበባ ደሳለኝ ዶ/ር ያኡቆብ ወልደማርያም ፕሮፌሰር ባኣሩ ዘውዴ ሜ/ጀ ተስፋዬ ወ/ማርያም እስከ1996 ድረስ የኢትዮጵያ አየር አይል ኮማንዶ አዛዥ ራስ ደስታ ዳምጠው ቀኝ አዝማች ገብረማርያም ጌር ዮሴፍ ገብረ፣ባልቻ አባ ነፍሶ(አባ መላ) ፊት አውራር ዳምጠው ቀጠና የ አጼ ሚሊሊክ ዲፕሎማሲ ቀኝ እጅ በአድዋ የተሰዋ ከብዙ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ::