ሰኔ
የሰኔ ቀናት | ||||||
1 | 2 | 3 | 4 | 5 | 6 | 7 |
8 | 9 | 10 | 11 | 12 | 13 | 14 |
15 | 16 | 17 | 18 | 19 | 20 | 21 |
22 | 23 | 24 | 25 | 26 | 27 | 28 |
29 | 30 |
ሠኔ የወር ስም ኾኖ በግንቦት እና በሐምሌ ወራት መኻል የሚገኝ ከዐሥራ ሦስቱ ኢትዮጵያ የወራት አቆጣጠር ውስጥ አሥረኛው የወር ስም ነው። «ሠኔ» ከግዕዙ «ሠነየ» ከሚለው ቃል የተባዛ ሲኾን አስጊያጭ፥አሳማሪ ማለት ነው።[1] የሠኔ ወር የክረምት የመጀመሪያው ወር ሲኾን ከግንቦት ደረቃማነት በኋላ በዝናም ርጥበት መሬቷ በአረንጓዴ የምታምርበት ወቅት ነው።
በሠኔ ወር ነጻነታቸውን የተቀዳጁ የአፍሪቃ አገሮች
በሠኔ ወር በጠቅላላው ዐሥራ ኹለት የቅኝ ግዛት አገሮች ነጻነታቸውን አግኝተዋል። ከነዚህም ዐምስቱ በፈረንሳይ፤ ሦስቱ በብሪታንያ፤ ሦስቱ በቤልጂግ እና አንድ በኢጣልያ አስተዳደር ሥር ነበሩ።
- ሰኔ ፳፱ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ/ም የቆሞሮስ ደሴቶች ከፈረንሳይ
ዘመን
NOTOC
ሳይንስ
ወደ ሳይንስ ክፍል እንኳን ደህና መጡ!
| ||
|
ሳይንስ ከተጨባጩ ዓለም በሥርዓት መረጃ የሚሰበስብ፤ ከተሰበሰበው መረጃ ተነስቶ ዕውቀት የሚገነባ እና በተመክሮ ቢፈተኑ ጸንተው ሊቆሙ የሚችሉ ትንቢቶችንና ማብራሪያዎችን የሚያስገኝ የዕውቀት ዓይነት ነው። በፍልስፍና አስገዳጅ ዕውነት (የአምክንዮ ዕውነት) እና አጋጣሚ ዕውነት (ሓቅ) የተባሉ ሁለት ዓይነት ዕውነቶች አሉ። የሳይንስ ዕውቀቶች በአጋጣሚ ዕውነቶች (ሓቆች)ላይ የተመሰረቱ ናቸው። ይህም ሲባል ለሓቆች እንዲህ ሆኖ መገኘትና፣ እንደዚያ ሆኖ አለመገኘት አስገዳጅ አመክንዮ የለም። ለምሳሌ መሬት በላይዋ ላይ ያለን ማንኛውንም ቁስ ትስባለች፣ ይህ ግን ያለንበት ዓለም ዕውነታ ነው እንጂ መሬት ማንንም ባትስብ ምንም የአመክንዮ መጣረስ አይኖርም። በሌላ አነጋገር፣ አንድ ሰው ከ ጥሩ መሪ ሃሳቦች ተነስቶ፣ በጥሩ አመክንዮ፣ «የመሬት ስበት የለም» እሚል ድምዳሜ ላይ ሊደርስ ይችላል። ድምዳሜው ስህተት መሆኑን በምንም ዓይነት በአመክንዮ ብቻ ማዎቅ አይቻልም ምክንያቱም የአመክንዮ መጣረስ ስለማይፈጥር። በአጠቃላይ መልኩ፣ ሓቆች በአዕምሮ ፍልስፍና ብቻ ሊደረስባቸው አይቻልም። ሳይንስ በአመክንዮ ብቻ ሳይሆን በተጨባጩ አለም ውስጥ በመሞከር፣ ከተሞክሮውም ዕውነትና ውሸቱ እየጠራና እየተመዘገበ በሂደት እየተሻሻለ የሚሄድ የዕውቀት አይነት ነው። የመሬትን ስበት ሓቅነት ለመገንዘብ እሚፈልግ በማሰብ ብቻ ሳይሆን ዘሎ መሬትን ለማምለጥ በመሞከር ሊያውቅ ይችላል። ለዚህና ለመሳሰሉት ስራዎች፣ ዘመናዊው ሳይንስ የሳይንሳዊ ዘዴን ይጠቀማል። ዘመናዊው ሳይንስ ፣ ሰፊ ዕውቀትን በመሰብሰብ ብቻ ሳይሆን ይህን ዕውቀት በሥራ ላይ በማዋል ያለተወዳዳሪ የሰውን ልጅ ህይወት በማሻሻል ላይ ይገኛል። በሽተኞች መታከማቸው፣ የእርሻ ምርት መትረፍረፍ፣ የመገናኛ ብዙሃን መፈጠርና ማደግ፣ ወዘተ...እነዚህ ሁሉ የዚህን ዕውቅት ሥኬት የሚያሳዩ ናቸው። |
ለዕለቱ የተመረጠ የሳይንስ ጽሑፍ
ብርሃን ነገሮች በዓይን እንዲታዩ የሚያደርግ የተፈጥሮ ሞገድ ነው። የብርሃን ሞገድ ከኤሌክትሪክ እና ከመግነጢስ የተሰራ ስለሆነ ሞገዱ የ ኤሌክትሮመግነጢስ ጨረራ ይባላል። ይሁንና፣ የኤሌክትሮመግነጢስ ጨረራ ብርሃንን ብቻ ሳይሆን የብርሃንን ታናናሽና ታላላቅ ወንድሞች ሳይቀር ያፈልቃል። ከብርሃን ታናናሽ ወንድሞች፣ ሬዲዮ፣ ራዳር እና ታህታይ ቀይ ይገኙበታል። ታላላቅ ወንድሞቹ ቢባል፣ ላዕላይ ወይን ጠጅ፣ ኤክስ ሬይ፣ ጋማ ጨረር ይገኛሉ። እነዚህ የብርሃን ወንድሞች በተፈጥሯቸው ከብርሃን ጋር አንድ ቢሆኑም ፣ የሰው ዓይን ሊያያቸው ስለማይችል ብርሃን አይባሉም። ሆኖም ግን አንድ አንድ እንስሳት እነዚህን ሞገዶች መመልከት ይችላላሉ። ለምሳሌ ታህታይ ቀይ የሚባለው የብርሃን ታናሽ ወንድም፣ ለሰዎች እንደ ብርሃን ሳይሆን እንደ ሙቀት ሆኖ ይሰማል። ለምሳሌ የፀሐይ መሞቅ ከምትተፋው የታህታይ ቀይ ጨረራ ይመነጫል። በበረሃ የሚንከላዎሱ እባቦች ይህን ሞገድ በአይናቸው መመልከት ስለሚችሉ፣ ሙቀት ያለውን ማንኛውንም ነገር በጭለማ ሳይቀር ማየት ይችላሉ። ንቦች በተቃራኒ፣ የሰው ልጅ እማያየውን ላዕላልይ ወይን ጠጅ ሞገድ በዓይናቸው ማየት ስለሚችሉ፣ አበቦች ለንቦች ከሰው ልጅ የተለየ መልክና መልዕክት ያስተላልፋሉ። ብርሃን ሞገድ ብቻ ሳይሆን፣ እንደሌሎቹ ጨረራዎች የሞገድና እኑስ ሁለትዮሽተፈጥሮን አዋህዶ የያዘ ነው። ስለዚህና ስለመሳስሉት መሰረታዊ የብርሃን ባህርያት የሚያጠናው የዕውቀት ዘርፍ ሥነ ብርሃን (ኦፕቲክስ) በመባል ይታወቃል። የተፈጥሮ ህግጋት ጥናት (ፊዚክስ) ምርምር ዋና ክፍል ነው። የበለጠ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ ... |
ይጻፉ! ይሳተፉ!አዲስ የሳይንስ ጽሑፍ ለማቅረብ እሚከተለው ሳጥን ውስጥ ርዕሱን ያስቀምጡ!
|
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |
ዋቢ ምንጮች
- (እንግሊዝኛ) http://ethiopic.org/Calendars/ Archived ማርች 31, 2014 at the Wayback Machine The Ethiopic Calendar
- ^ [http:// http://gzamargna.net/html/gs.html]
ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |