ሱመር (አካድኛሹመርግብጽኛሳንጋርዕብራይስጥሰናዖር) በጥንታዊ መካከለኛ ምሥራቅ አለም በቅድሚያ ሥልጣኔ የሚባል ኹኔታ የደረሰለት አገር ነበር። ዘመኑ ከታሪካዊ መዝገቦች መነሻ ጀምሮ ይታወቃል። 'ሱመራዊ' ማለት ሱመርኛ የቻሉ ወገኖች ሁሉ ነው። ከጥንታዊ ግብፅ እና ከሕንዶስ ወንዝ ሸለቆ ሥልጣኔ ጋራ ከሁሉ መጀመርያ ሥልጣኔ ካሳዩት አገሮች አንዱ ነው ይባላል።

የሱመር ዙሪያ

ስም ለማስተካከል

ሹመሩ የሚለው ስም በጎረቤቶቻቸው በአካድ ሰዎችም ሲጠራ ሕዝቡ ለራሳቸው የነበራቸው ስም ሳግ-ጊ-ጋ (ጥቁር ራስ ያላቸው) ነበር። አገራቸውንም ኪ-ኤን-ጊር ይሉት ነበር። በተረፈ በኬጢያውያን መዝገቦች አገሩ ሳንሃር፣ በግብጽ አማርና ደብዳቤዎች ሳንጋር፣ በመጽሐፍ ቅዱስሰናዖር ይባላል።

ታሪክ ለማስተካከል

ጽሕፈት በመፍጠሩ የታሪክ መጋረጃ ሲከፈት፣ ሱመራውያን በደቡብ መስጴጦምያ (ከጤግሮስኤፍራጥስ ወንዞች መኃል፣ የዛሬው ኢራቅ) ይገኙ ነበር።

ጥንታዊው የሱመራውያን ነገሥታት ዝርዝር የያንዳንዱን ከተማ ሥርወ መንግሥት ይዘርዝራል። ከነዚህም በመግቢያው ያላቸው ነገሥታት ከማየ አይህ በፊት እንደ ነገሡ ይላል። እነዚህ ስሞች ትውፊታዊ ሊሆኑ ይችላል። ከሌላ አፈ ታሪክ ምንጭ የታወቀው በዝርዝሩ የተገኘ ስም የኪሽ ንጉሥ ኤታና ነው። ከዚያ በኋላ የኡሩክ መጀመርያ ነገሥታት ኤንመርካርሉጋልባንዳዱሙዚድጊልጋመሽ ሁላቸው ከሌሎች ትውፊቶች ይታወቃሉ። ከሥነ ቅርስ የታወቀው መጀመርያ ስም ኤላምን ያሸነፈው የኪሽ ንጉሥ ኤንመባራገሲ ነው። እሱ ደግሞ የጊልጋሜሽ ትውፊት በተባለ ጽሑፍ ስለሚገኝ ይህ ለጊልጋሜሽ ታሪካዊ ሕልውና ምናልባትነት መስጠቱ ይታመናል።

ከዚህ በኋላ የኡር ንጉስ መስ-አኔ-ፓዳ ኡሩክንና ኪሽንም አሸንፎ «የኪሽ ንጉሥ» የሚልን ስያሜ ወሰደ። በሚከተለውም ዘመን የሱመር ላዕላይነት ከኡር ወደ አዋን (ኤላም)፣ ከአዋንም ወደ ኪሽ፣ ከኪሽም ወደ ሐማዚ በመፈራረቅ ይዛወር እንደ ነበር መዘገቦች ይሉናል።

የኡሩክ ንጉሥ ኤንሻኩሻና ሐማዚን፣ አካድን፣ ኪሽንና ኒፑርን በማሸነፉ መጀመርያ 'የሱመርና የአካድ ንጉሥ' የተባለ ነበረ። ከዚህ ቀጥሎ የላጋሽ ንጉሥ ኤ-አና-ቱም ሱመርን ሁሉ ኤላምንም በከፊል አሸነፈ። ከተገኙ ጽላቶች መሠረት፣ የሱ መንግሥት አደራረግ ተገዥ ወገኖችን ማስፈራራትና ግፍ መሆኑን ልንገምት እንችላለን። እሱ እንደ ሞተ፣ ግዛቱ ለጊዜው በየከተማው ተከፋፈለ።

በኋላ የአዳብ ንጉሥ ሉጋል-አኔ-ሙንዱ በዘመቻ እስከ ሜዲቴራኔያን እና እስከ ጣውሮስ ተራሮች (ትንሹ እስያ) ና እስከ ዛግሮስ ተራራዎች (ፋርስ) ድረስ እንዳቀና ይመዘገባል። ይህም ማርቱሊባኖስሹቡርኤላምጉታውያን የጠቀለለ ነው። የሱም ግዛት በመሞቱ እንደ ከተሞቹ ብዛት ተሰባበረ።

ላዕላይነቱ አሁን እንደ «ቅዱስ የሮማ መንግሥት ንጉስ» የመሰለ ማዕረግ ሆኖ ነበር። ከከተማ-አገሮቹ የማሪ ንጉስ ማዕረጉን ከያዘ፣ ከዚህ ወደ አክሻክ ንጉሥ ተዛወረ። የአክሻክ ንጉስ ፑዙር-ኒራሕ ክፉ ሆኖ፣ የሱመር ቄሳውንት መንግሥቱን ለአንዲት ሴት ባለ ጠጅ ቤት ለኩግ-ባው ንግሥት ሆና እንዳሸለሙላት የሚል ሰነድ አለ። በዚህም ዘመን በላጋሽ፣ ከአንድ ክፉ ንጉሥ ሉጋላንዳ በኋላ፣ የላጋሽ ንጉሥ ኡሩካጊና የራሱን ሕገጋት አውጥቶ ለድኆች ማሻሻል አደረገ፤ በተጨማሪ 1 ሚስት ቀድሞ ብዙ ባሎችን የምታገባበትን ልማድ ከለከለ።

 
የሉጋል-ዛገ-ሲ መንግሥት (ቀይ)

በኡሩካጊና ዘመን መጨረሻ፣ የኡማ ንጉሥ ሉጋል-ዛገ-ሲ ላጋሽን አገለበጠውና ዋና ከተማውን በኡሩክ አድርጎ መንግስቱን ከፋርስ ወሽመጥ እስከ ሜዲቴራኔያን ድረስ እንደ አስፋፋ በጽላቶች ተቀርጿል።

ከሉጋል-ዛገ-ሲ ላይኛነቱን የያዘ ሱመራዊ ሰው ሳይሆን የአካድ ንጉሥ ታላቁ ሳርጎን ነበር። የአካድ ሰዎች ሴማዊ ቋንቋአካድኛ ይናገሩ ነበር። ቋንቋቸውን በሱመር እንዲሁም በኤላም ይፋዊ በግድ አደረጉ። በጽላት ዜና መዋዕል መዝገቦች መሠረት፣ ሳርጎን የባቢሎንን ሥፍራ ወደ አካድ ዙሪያ አዛወረ።

የአካድ መንግሥት በጉታውያን ዕጅ ከወደቀ በኋላ የላጋሽ ንጉሥ ጉዴአ ተነሣ። ከዚያ በኋላ የኡር ንጉስ ኡር-ናሙ ላጋሽን አሸንፎ ላይኛነቱን ያዘ። እሱ በተለይ የኡር-ናሙ ሕገጋት ስለ ተባለው ፍትኅ ይታወሳል። በዚህ ወቅት ብዙ ሴማዊ ቋንቋ ያላችው አሞራውያን ወገኖች ወደ መስጴጦምያ ስለ ገቡ፣ የሱመርኛ ጥቅም ቀስ በቀስ ቀነሰ። ሆኖም ሱመርኛ በትምህርት ቤትና በሃይማኖት ረገድ ይቀጠል ነበር።

ይህ የኡር መንግሥት እስከ 1879 ዓክልበ. ግድም (ኡልትራ አጭር አቆጣጠር) ኤላማውያን እስከ ወረሩት ድረስ ቆየ። የዚያ ውጤት አሞራውያን ለራሳቸው ከተሞች ያዙና የሱመር ሃይል ጠፋ። ከነዚህ ከተሞች መካከል ባቢሎን በንጉስዋ ሃሙራቢ ወቅት ላይኛነቱን ለረጅም ወራት መሰረተች።