ሥልጣኔ ማለት የሠለጠነ ባህል ወይም ኅብረተሠብ ነው። ይህም ምን ማለት እንደ ሆነ ለመግለጽ በታሪክ ልዩ ልዩ ሀሣቦች ቀርበዋል። ባጠቃላይ የሠለጠነ ትርጉም በአማርኛ በጥበብ፣ በባለሙያነት ወይም በዕውቀት የተመጠነ የተለመደ ማለት ነው። የስልጣኔ ተቃራኒ አንትረቢ፣ አውሬነት ወይም ነውር ተብሏል።

አልቤርት ሽቫይፀር1915 ዓም በጻፈው «የሥልጣኔ ፍልስፍና» (ዘ ፊሎሶፊ ኦቭ ሲቪላይዜሽን)፦ «በያንዳንዱ ሙያ፣ ከያንዳንዱም አስተያየት፣ በሰው ልጅ የተደረገው እርምጃ ሁሉ ድምር ነው፣ ድምሩ የእርምጃ ሁሉ እርምጃ ሆኖ ወደ ግለሠቡ መንፈሳዊ ፍጻሜ እስከሚረዳው ድረስ።» በማለት «ስልጣኔ»ን አስተርጒሟል። በአጭሩ፣ ወደ መንፈሳዊ ፍጻሜ የሚመራው የሰው ልጅ እርምጃ ሁሉ ድምሩ ሥልጣኔ ሊባል ይችላል።

ላለፉት ጊዜዎች እርምጃ፣ ብዙ ጊዜ «ስልጣኔ» እንደ «ባህል» ወይም «ኅብረተሠብ» በመለዋወጥ ለማናቸውም ሊወከል ይችላል፤ ለምሳሌ «የማልታ-ቡረት ሥልጣኔ» በቅድመ ታሪክሳይቤሪያ ተገኘ፤ ወይም የማያ ሥልጣኔ ከ2000 ዓክልበ. እስከ 1690 ዓም ድረስ በዩካታንሜክሲኮ አካባቢ ቆየ።