የዔድን ገነት (ዕብራይስጥ፦ גַּן עֵדֶן /ገን ዐድን/) በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት እግዚአብሔርሰው ልጅ መጀመርያ ቅድመ ታሪክምድር የተከለ ገነት ነበረ። ይህ ገነት በተለይ የሚገለጸው በኦሪት ዘፍጥረት 2 እና 3፣ እንዲሁም በመጽሐፈ ኩፋሌ 4 እና 5 ነው፤ ደግሞ በትንቢተ ሕዝቅያስ 28 ይጠቀሳል። አንዳንዴ በመሳሳት «ዔድን» ሳይሆን የ«ኤዶም» ገነት ተብሏል፤ ኤዶም ግን በትክክል የያዕቆብ ወንድም ዔሳው የመሠረተው ሀገር ነበረ።

1500 ዓም አካባቢ እንደ ተሳለ

መጽሐፈ ኩፋሌ 4:14, 16 እንደሚያብራራልን፣ መጀመርዮቹ ሰዎች አዳም እና ሔዋን በገነት የቆዩበት ዘመን ሰባት አመታት ያህል ነበር። በመጽሐፈ ኩፋሌ አቆጣጠር አስርቱ ቃላት እስከ ተሰጡበት ዓመት ድረስ 2410 ዓመታት ስለሚቆጠር፣ እነዚህ ቅድመ ታሪካዊ ሰባት አመታት ከ4071 እስከ 4064 ዓክልበ. ያህል እንደ ነበሩ መረዳት ይቻላል። ሌሎች ግን በሌሎች ዘዴዎች በኩል ሌሎችን ፍቾች አገኝተዋል። አዳም ከተፈጠረበት ከሥነ-ፍጥረት 6ኛው ቀን ጀምሮ በአዳም 40ኛው ቀን ወደ ገነት እንደ ገባ፣ ሚስቱም ሔዋን በ80ኛው ቀን እንደ ገባች ይለናል (4:9, 12)። ወደ ገነትም ሳይገቡ በተወለዱበት አገር በኤልዳ እየቆየ አዳም መጀመርያው ሳምንት እንስሶችን ያሰይማቸው ነበር፣ ከ፪ኛውም ሳምንት ጀምሮ ሔዋንን ያውቃት ነበር። አዳም ከተፈጠረበት ከዓለም 6ኛው «ቀን» አስቀድሞ ዓለሙ፣ ምድሩ፣ አትክልቱና እንስሶች ሁሉ ወዘተ. ተፈጥረው ነበር፤ እነዚህ 6ቱ «ቀኖች» ግን እንደ አሁን የ24 ሰዓት ቀኖች እንደ ነበሩ አይመስልም።

ሥነ ቅርስ መጀመርያው የምናውቀው ታሪካዊ ሰነድ «የመንደሮቹ መኳያ ሰሌዳ» 3125-3100 ዓክልበ.ግ. ይመስላል፤ ከዚያ አስቀድሞ ለነበረው ዘመን የሰው ልጅ ታሪካዊ መዝገቦች (ሰነዶች) በፍጹም ባለመኖራቸው፣ ይህ ስለ «ቅድመ ታሪክ» አንድ ቅድመ-ታሪካዊ አስተያየት ሲሆን፣ በሰፊ በአብርሃማዊ ሃይማኖቶች (በተለይ ክርስትናእስልምናአይሁድና) የሚገኝ አስተያየት ነው። (ደግሞ ባለሙያ ንድፍን ይዩ።)

በዚሁም አጭር የገነት ወቅት ከአሁን በጣም የተለዩ ሁናቴዎች እንደ ነበሩ የሚል አሣብ ይፈጠራል።

  • አዳም እና ሔዋን በኤድን ሲቆዩ መዋቲ መሆናቸው እንደ ታሠበ አይመስልም። ሞት ለሰው ልጆች የመጣበት ምክንያት አዳም እና ሔዋን በዓመፃ ጸባይ የተከለከለውን ፍሬ ተመግበው ከዔድን ገነት ስለ ተሰደዱ እንደ ሆነ ይመስላል።
  • የእንስሶች ጉዳይ በግልጽ ባይብራራልንም ከአዳም ጋር ለመናገር በዚሁ ወቅት ችሎታው እንደ ነበራቸው በኩፋሌ 5:2 ይጻፋል።
  • እባብ በዚህ ሰዓት እግሮቹን ገና ስላላጣ ባለ እግር ፍጡር እንደ ነበር ይመስላል።
  • የእግዚአብሔር መላእክት ለአዳምና ሔዋን የገነት አጠባበቅ በነዚህ 7 አመቶች ያስተምራቸው ነበር (ኩፋሌ 4:14)።
1522 ዓም ተሳለ።

«የአዳምና ሔዋን ትግል ከሠይጣን ጋራ» ለማስተካከል

የአዳምና ሔዋን ትግል ከሠይጣን ጋራ ሌላ ቀኖናዊ ያልሆነ በተለይ በአረብኛግዕዝ የታወቀ ጥንታዊ ጽሑፍ ነው። በዚህ ጽሑፍ ዘንድ ግን አዳምና ሔዋን ሳይበድሉ በገነት የቆዩበት ወቅት ጥቂት ሰዓቶች ብቻ ነበር፤ ከገነትም በወጡ በ223ኛው ቀን (ወይም ከ7 ወርና 13 ቀናት በኋላ) አዳም ሔዋንን በጋብቻ ያገባት ነው። ይህ መረጃ ከኩፋሌ ጋር አይስማማም።

ይኸውም መጽሐፍ ስለ ዔድን ገነት ተጨማሪ ዝርዝርዎች ይሰጣል። ከነዚህም መሃል፦

  • አዳም በገነት እያለ ሌሊትን አላወቀም ነበር። (እንደ ክፋሌ ለ፯ አመት እንዲህ ከሆነ የምድር ምኋር ከአሁን እንደ ተለየ መስሎ በገነት ምንጊዜም መዓልት ነበር ማለት ነው።)
  • የገነት ፍሬ ከአሁን ትልቅ ነበር፤ በገነት ውስጥ አንድ የበለስ ፍሬ ክብደት እንደ አንድ ሃብሃብ ነበር። ጻዕሙም እንደ ጣፋጭ ሥጋ ወጥ ነበር። ወርቅዕጣንከርቤም በገነት መኖራቸውም ይጠቀሳል።

የተከለከለው ፍሬ ለማስተካከል

እነዚህ ምንጮች የተከለከለውን ፍሬ መታወቂያ አይወስኑም። ብዙዎች እንደሚገመቱ የቱፋሕ ወይም የበለስ ዛፍ ነበረ። አንድ ሰነድ በጥንታዊ ስላቭኛ የተጠበቀው መጽሐፍ 3 ባሮክ እንዳለው፣ የተከለከለው ፍሬ ወይን ነበር። እግዚአብሐር የእባቡን ባሕርይ እንደ ለወጠ ሁሉ የወይኑንም ባሕርይ በቅጣቱ ከዛፍ ወደ ሐረግ ብቻ ለወጠ ይላል። ሆኖም በእቅዱ ወደፊት የመድኃኔ አለም ደም በመሆኑ ከእርጉም ወደ በረከት ይለውጠዋል በማለት ተጨመረ።

ሥፍራ ለማስተካከል

በመጽሐፍ ቅዱስና ሌሎች ምንጮች ስለ ገነቱ ሥፍራ አንዳንድ ፍንጭ ይሰጣል፤ ስለ ፍንጮቹ ትርጓሜ ግን አስተሳሰቦች ተለይተዋል።

  • «እግዚአብሔር አምላክ በምሥራቅ በኤድን ገነትን ተከለ... ወንዝም ገነትን ያጠጣ ዘንድ ከዔድን ይወጣ ነበር፤ ከዚያም ለአራት ክፍል ይከፈል ነበር። የአንደኛው ወንዝ ስም ፊሶን ነው፤ እርሱም ወርቅ የሚገኝበትን የኤውላጥ ምድርን ይከብባል፤ የዚያም ምድር ወርቅ ጥሩ ነው፤ ከዚያም ሉልና የከበረ ድንጋይ ይገኛል። የሁለተኛው ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል። የሦስተኛውም ወንዝ ስም ጤግሮስ ነው፤ እርሱም በአሦር ምሥራቅ የሚሄድ ነው። አራተኛውም ወንዝ ኤፍራጥስ ነው።» (ዘፍ. 2:8, 10-14)

በዚህ ጥንታዊ ወቅት የነበረው መልክዓምድር ከአሁኑ እንደ ተለየ ይመስላል። ከተጠቀሱት ወንዞች፣ የጤግሮስና የኤፍራጥስ መታወቂያዎች ያለ ክርክር ታውቀዋል። «ግዮን» የአባይ (ናይል) ስም ሲሆን ኢትዮጵያንም ይከብባል። የ«ፊሶን» ሥፍራ በተለይ አጠያያቂ ሆኗል፣ ኤውላጥ ግን በኋላ የኖህ ልጆች ዘመን ስሙን ለአገሩ ሰጠ፤ በአረቢያቀይ ባሕር አጠገብ እንደ ተገኘ ይታስባል። ቀይ ባሕሩ በዚህ ወቅት ወንዝ ብቻ ከሆነ፣ እሱ የፊሶን መታወቂያ ሊሆን ይቻላል፤ ወይም የሕንድ ሥፍራ ያንጊዜ በአፍሪካና በአረቢያ አጠገብ ከሆነ፣ የፊሶን መታወቂያ ሌሎች እንደሚሉ ሕንዱስ ወንዝ ሊሆን ይቻላል። አባይ ደግሞ ወደ ሜድትራኔያን ባህር ሳይፈስ ወደ ዔድን ለመድረስ በሲናዮርዳኖስ በኩል እንደ ተዛወረ ይመስላል።

ዕብራይስጥ ትርጉሙ፣ በኢትዮጵያ ሥፍራ «ኩሽ» አለው፤ በአንዳንድ ምዕራባውያን ሊቃውንት ሃልዮ ዘንድ ይህ «ኩሽ» ኢትዮጵያ ሳይሆን በ1500-1100 ዓክልበ. ግድም ባቢሎንን የገዙት ብሔር «ካሣውያን» ይሆናሉ ብለዋል።

በኩፋሌ 9፣ የገነቱ ሥፍራ በሴም ርስት ውስጥ፣ ለካም ርስት ቅርብ መገኘቱ ይመስላል። በተለይም በ9:8 ዘንድ ገነት፣ ደብረ ሲናደብረ ጽዮን ሦስቱ ቅዱስ ቦታዎች «አንዱ በአንዱ አንጻር ለምስጋና ተፈጠሩ» ይለናል። ሄኖክ ሳይሞት መላእክት ወደ ገነት እንዲመለስ ፈቀዱ በምዕራፍ ፭ ሲለን፣ አራተኛው የተቀደሠ ቦታ «የምሥራቁ ደብር» ይባላል፤ ይህ ደብረ አራራት መሆኑ ይታስባል።

በተቀበልነው ትርጉም በዘፍጥረት ዘንድ አዳምና ሔዋን ከኤድን ወደ ምሥራቅ ተሰደዱ፤ በኩፋሌ ወደ ተፈጠሩበት ወደ ኤልዳ (ወይም «ሞኤልዳ») ተመለሱ፤ ባብዛኞች ጥንታዊ ምንጮች ይህ ከገነት ወደ ምዕራቡ ተገኘ።

ወንዞቹ ሁሉ በዚያን ጊዜ የተጋጠሙበት ምድር አሁን የአረብ በረሃ ቢመስልም፣ በመስጴጦምያ ወይም በአፍሪካ እንደ ነበር የሚሉ ብዙ አሉ። እንዲሁም ሌሎች በጣም ልዩ ልዩ አስተሳስቦች አሉ። ለምሳሌ በሞርሞኒስም ዘንድ፣ የዔድን ገነትና የአዳምና ሔዋን ዕውነተኛ መገኛ በሚዙሪ ክፍላገር አሜሪካ ነበረ።