ሚያዝያ ፳
ሚያዝያ ፳፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፴ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፳፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፴፮ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፴፭ ቀናት ይቀራሉ።
ታሪካዊ ማስታወሻዎች ለማስተካከል
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - የኢጣልያ የፋሺስት መሪ የነበረው ቤኒቶ ሙሶሊኒ ከነውሽማው ክላራ ፔታቺ ጋር በቀበሌ ታጣቂዎች ተይዞ በኮሎኔል ካሌሪዶ ከተረሸነ በኋላ አደባባይ ላይ ቁልቁል ተሰቀለ።
- ፲፱፻፶፱ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው ቡጢኛ ሙሐመድ አሊ ወደአገሪቱ ጦር ሠራዊት ገብቶ የማገልገል ግዴታውን እንዲወጣ ቢጠየቅም አሻፈረኝ አለ። የዚያኑ ዕለት የዓለም ቻምፒዮናነቱን ማዕረግ በኒው ዮርክ የአትሌቲክ ባለ ሥልጣን ተገፈፈ።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ የአገራቸውን አርበኞች የመሩትና ከነጻነት በኋላም የፈረንሳይ ፕሬዚደንት ሆነው ለ አሥራ አንድ ዓመታት ያገለገሉት ሻርል ደጎል በፈቃድቸው ሥልጣናቸውን ለቀቁ።
- ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በስዊድን፤ ፊንላንድ እና ኖርዌይ የሚገኙ የኑክሊዬር ምርመራ ማዕከላት ያልተለመደ የራዲዮ-አክቲቭ በከላ በምድር ጠፈር ላይ እንዳገኙ ባስታወቁ በሁለተኛው ቀን የሶቪዬት ኅብረት ባለ ሥልጣናት ቸርኖቢል የሚባለው የኑክሊዬር የመብራት ኃይል ማምረቻ አደጋ እንደደረሰበት ይፋ አደረጉ።
ልደት ለማስተካከል
ዕለተ ሞት ለማስተካከል
ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል
- (እንግሊዝኛ) P.R.O., FO 371/154836 Annual Report from Ethiopia for 1960
- (እንግሊዝኛ) http://www.thepeoplehistory.com/april27th.html
- (እንግሊዝኛ) http://en.wikipedia.org/wiki/April_28
- (እንግሊዝኛ) http://news.bbc.co.uk/onthisday/hi/dates/stories/april/28/newsid_3564000/3564529.stm
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |