ሐምሌ ፳፫

ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፳፫ ኛው ዕለት ነው።

ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ዮሐንስ ፵፫ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስማርቆስ እና ሉቃስ ደግሞ ፵፪ ዕለታት ይቀራሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዕለት ስማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን ታስባለች።


ታሪካዊ ማስታወሻዎች ለማስተካከል

፯፻፶፬ ዓ/ም የዛሬዋ የኢራቅ ዋና ከተማ ባግዳድ ተመሠረተች።

፲፮፻፳፩ ዓ/ም ናፖሊ በተባለች የምዕራብ ኢጣልያ ከተማ በመሬት ነውጥ ፲ ሺህ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።

፲፰፻፺፩ ዓ/ም - የሐረር ከተማ የመጀመሪያው የመድኀኒት መደብር፤ ዛፊሮፖፑሎ በተባለ ግሪክ ‘ፋርማሲ ኢትዮፕዬን’በሚል ስም ተከፈተ።

፲፱፻፫ ዓ/ም ደጃዝማች ተፈሪ መኮንን እና ወይዘሮ መነን አስፋው በዚህ ዕለት ተጋቡ።

፲፱፻፳፪ ዓ/ም በኡራጓይ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር ዋንጫ ውድድር አስተናጋጇ ኡራጓይ ዋንጫውን ዋና ከተማዋ ሞንቴቪዲዮ ላይ አሸነፈች።

፲፱፻፵፰ ዓ/ም ፕሬዚደንት አይዘንሃወርአሜሪካ "የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት" (House of Representatives) እና "የእንደራሴዎች ሸንጎ" (Senate) በአንድነት ያጸደቁትን “በእግዚአብሔር እናምናለን” ("In God We Trust”) የሚለውን የአገሪቱን ብሔራዊ መፈክር ሕግ ፈረሙ።

ልደት ለማስተካከል

ዕለተ ሞት ለማስተካከል

ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል