ኅዳር ፱ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፷፱ኛ ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፪፻፺፯ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፺፮ ቀናት ይቀራሉ።

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ለማስተካከል

፲፬፻፹፮ ዓ.ም. - ክሪስቶፎሮ ኮሎምቦ የተባለው ኢጣልያዊ መርከበኛ በሰሜናዊ አሜሪካ ምሥራቃዊ ድንበር በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ የምትገኘውን የፑዌርቶ ሪኮ ደሴትን አገኘ።

፲፱፻፲፩ ዓ.ም. - በባልቲክ ባሕር የምትገኘው ላትቪያሩስያ ነጻ የሆነች ሉዐላዊ አገር መሆኗን አወጀች።

፲፱፻፲፱ ዓ.ም. - በደብሊን አየርላንድ የተወለደው ታዋቂ የሥነ ጽሑፍ ሰው ጆርጅ በርናርድ ሾው በስነጽሑፍ የተሸለመውን የኖቤል ሽልማት ቢቀበልም ለዚሁ ሽልማት የተወሰነውን አንድ መቶ አሥራ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ስድሳ አምሥት የስዌድ ክሮና ግን አልቀበልም አለ። በኋላ ግን በገንዘቡ በስዌድ ቋንቋ የተጻፉ መጻሕፍት ወደ እንግሊዝኛ እንዲተረጎሙበት አደርገ። ጆርጅ በርናርድ ሾው የሽልማቱ አሸናፊነቱ ይፋ በሆነ ጊዜ፤ “አልፍሬድ ኖቤልን ዲናሚትን መፍጠሩን ይቅር ልለው እችላለሁ፤ ነገር ግን የኖቤል ሽልማትን ለመፍጠረ የሚበቃ ግን በሰው የተመሰለ ሰይጣናዊ መንፈስ ነው” አለ።

፲፱፻፷፱ ዓ.ም. - የእስፓኝ የሕዝብ ምክር ቤት፣ አገሪቱን ከ ሠላሳ ሰባት ዓመት የ”አምባገነን” መንግሥት ስርዐት በኋላ፣ ወደዴሞክራሲያዊ ስርዐት የሚያሸጋግር ህግ አጸደቀ።

ልደት ለማስተካከል

2013

ዕለተ ሞት ለማስተካከል


ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል

  • (እንግሊዝኛ) The London Gazette; p. 6608


የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ