ሶበክሆተፕ ሰኸምሬሰዋጅታዊ ግብጽ2ኛው ጨለማ ዘመን (13ኛው ሥርወ መንግሥት) ከ1741 እስከ 1701 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛ ፈርዖን ነበረ። የሴት መሪብሬ ተከታይ ነበረ።

ሶበክሆተፕ ሰኸምሬ ሰዋጅታዊ
3 ሶበክሆተፕ ጣኦትን ሲያመልክ
3 ሶበክሆተፕ ጣኦትን ሲያመልክ
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1741-1701 ዓክልበ. ግ.
ቀዳሚ ሴት መሪብሬ
ተከታይ 1 ነፈርሆተፕ
ባለቤት ሰነብኸናስ፣ ነኒ
ሥርወ-መንግሥት 13ኛው ሥርወ መንግሥት
አባት መንቱሆተፕ

ቶሪኖ ቀኖና ዘንድ ሶበክሆተፕ ሰኸምሬሰዋጅታዊ ለ፬ ዓመት ብቻ ሲለን ለእርሱ ብዙ ሐውልቶችና ቅርሶች ስለሚታወቁ ይህ ስኅተት ይመስላል። ከታወቁት ሐውልቶች መካከል አንዳንድ የቀዳሚው የሴት መሪብሬ ሐውልት ሆነው ነበር፣ ስሙ በመሪብሬ ስም ላይ ተቀረጸ። አንዳንድ የተገኘው ማህተም «የንጉሥ ሊቅ መኮንን ሶበክሆተፕ፣ የንጉሥ ሊቅ መኮንን መንቱሆተፕ ልጅ» አለበት። እንዲሁም ፓፒሩስ ቡላቅ 18 በተባለው ሰነድ «ሶበክሆተፕ» የሚባል «የንጉሥ ሊቅ መኮንን» አለ። የዚህ ፈርዖን አባት ስም «መንቱሆተፕ» መሆኑ ከብዙ ሌላ ጽላት ስለታወቀ፣ ሶበክሆተፕ ፈርዖን ከሆነ በፊት ይህን ወታደራዊ ማዕረግ እንደ ያዘ ይመስላል። ስለዚህ ሶበክሆተፕ በመንፈቅለ መንግሥት እንደ ተነሣ ይታስባል።

ሶበክሆተፕ ፈርዖን በሆነው ጊዜ፣ የፈርዖን ስም «ሰዋጅታዊ» (ሁለቱን አገራት የሚያፈራ) ወሰደ፤ ይህም ምናልባት የጌሤም ሥርወ መንግሥት በዚህ ጊዜ በመጨረሱ ሁለቱ አገራት (ላይኛና ታችኛ ግብጽ) ዳግመኛ ስለ ተወሐዱ ሊሆን ይችላል።

በዚህ ዘመን በተጻፈ በአንዱ ሰነድ የባርዮች ዝርዝር አለ። በተለይ ትኩረት የሚስበው አንዲቱ ሲፓራ የተባለች ባርያ ስለ ተዘረዘረች። በብዙ ሊቃውንት አስተሳሰብ ይህች ሲፓራ በሙሴ ልደት ወቅት በኦሪት ዘፍጥረት 1:15 የተጠቀሰችው ዕብራዊት አዋላጅ ልትሆን ይቻላል፤ ሶበክሆተፕም የተወለዱት ዕብራውያን ወንዶች ወደ አባይ ወንዝ እንዲጣሉ ያዘዘ እርሱ ይሆናል ባዮች ናቸው። ይህም በመጽሐፈ ኩፋሌ ውስጥ ከተገኘው ዜና መዋዕል ጋር ልክ ይስማማል።

የሶበክሆተፕ ጨቲ (ጠቅላይ ሚኒስትር ያህል) ረሠነብ (የአንኹ ልጅ) ነበረ። በተረፈ የሶበክሆተፕ እናት ዩኸቲቡ ተባለች፣ ወንድሞቹም ስነብና ኻካው፤ እኅቱም ረኒሰነብ፣ ሚስቶቹ ሰነብኸናስና ነኒ ተባሉ። የነኒ ሴት ልጆች ዩኸቲቡ ፈንዲ እና ደደታኑቅ ነበሩ። በኩፋሌ እና በሌሎች ምንጮች ዘንድ ሙሴን ያዳነችው ግብጻዊት ልዕልት ተርሙት ተባለች።

ቀዳሚው
ሴት መሪብሬ
ግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን
1741-1701 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
1 ነፈርሆተፕ

ዋቢ ምንጭ ለማስተካከል

  • K.S.B. Ryholt: The Political Situation in Egypt during the Second Intermediate Period, c. 1800 – 1550 BC, Carsten Niebuhr Institute Publications, vol. 20. Copenhagen: Museum Tusculanum Press, 1997 (እንግሊዝኛ)