ሴት መሪብሬ ላይኛ ግብጽ2ኛው ጨለማ ዘመን (13ኛው ሥርወ መንግሥት) ከ1744 እስከ 1741 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛ ፈርዖን ነበረ። የሰኸተፕካሬ አንተፍ ተከታይ ነበረ።

ሴት መሪብሬ
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1744-1741 ዓክልበ. ግ.
ቀዳሚ ሰኸተፕካሬ አንተፍ
ተከታይ 3 ሶበክሆተፕ
ሥርወ-መንግሥት 13ኛው ሥርወ መንግሥት

የሴት መሪብሬ ሕልውና እርግጥኛ አይደለም። ስሙ በቶሪኖ ቀኖና ላይ ብቻ በእርግጥነት ይታወቃል፣ በዚያም «<...>ኢብ<...> ሴት» ብቻ ይታያል። ዘመኑ ምን ያህል ጊዜ እንደ ቀረ ከ«<...>ና ፮ ቀን» በቀር ምንም አይነብም። በአንዳንድ ሊቃውንት አስተሳሰብ ግን ስሙ «መሪብሬ» ሲሆን ሐውልቶቹ በሚከተለው ዘመን በሌላው ፈርዖን ስም እንደ ተቀረጹ ያስባሉ። በነዚህ ቅርሶች ላይ ስሙ ተደምስሶ በመነመነ ምልክት እንደሚታይ ያምናሉ። ምንም እርግጠኛ ስላልሆነ ግን ትቃራኒ ሀሣቦች አሉ። በዝርዝሩ ዘንድ ከእርሱ ቀጥሎ 3 ሶበክሆተፕ (ሰኸምሬሰውጅታዊ) ገዛ። ይህም ሶበክሆተፕ ፈርዖን ከሆነ በፊት ማዕረጉ «የንጉሥ ሊቅ መኮንን» መባሉ ይመስላል።

ቀዳሚው
ሰኸተፕካሬ አንተፍ
ግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን
1744-1741 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
3 ሶበክሆተፕ

ዋቢ ምንጭ ለማስተካከል

  • K.S.B. Ryholt: The Political Situation in Egypt during the Second Intermediate Period, c. 1800 – 1550 BC, Carsten Niebuhr Institute Publications, vol. 20. Copenhagen: Museum Tusculanum Press, 1997 (እንግሊዝኛ)