ሙሴ (ዕብራይስጥ፡ מֹשֶׁה /ሞሼህ/) በብሉይ ኪዳን ከሚጠቀሱት ታላላቅ ነብያት አንዱ ነው። ሙሴ በተወለደበት ዘመን የእስራኤል ልጆች በግብጽ ውስጥ በባርነት ተገዝተው የነበርበት ሆኖም ግን ቁጥራቸው እየበዛና እየተጠናከሩ የነበርበት ጊዜ ነበር።

ታላቁ ነብይ ሙሴ
ሙሴ ፲ቱን ቃላት ሲቀበል
ነፃ አውጪው
የኖረበት ዘመን ሺ፬፻ ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት
ዜግነቱ እስራኤላዊ
ያደገው በግብፅ ፈርዖን ቤት
የአባት ስም አንበረም
የእናት ስም ዮካብድ
ወንድምና እህቱ አሮንና ማርያም
የባለቤቱ ስም ሲፓራ
የሚከበረው አይሁድና ፣ በክርስትና ፣ በእስልምና ሃይማኖቶች እምነት ተከታዮች
በዓል ንግሥ የካቲት ፲፯


በዚህ ዘመን ግብፅን ያስተዳድር የነበር፣ ስሙ በብሉይ ኪዳን ያልተጠቀሰው የግብፅ ፈርዖን፣ የእስራኤል ልጆች ከውጭ የግብፅ ጠላቶች አግዘው ሊወጉን ይችሉ ይሆናል በሚል ፍራቻ ማናቸው የእስራኤል ወገን የሆኑ ወንድ ልጆች በተወለዱ ጊዜ እንዲገደሉ አዘዘ። ሆኖም የሙሴ እናት፣ ዮካብድ፣ ልጇን ደብቃ ታኖር ነበር። ከሶስት ወር ድበቃ በኋላ ልጁን በደንገል ሳጥን አድርጋ በአባይ (ናይል) ወንዝ አጠገብ አስቀመጠችው። ሳጥኑ እየተንሳፈፈ የፈርዖን ልጅ እምትታጠብበት ስፍራ ደረሰ፣ የፈርዖንም ልጅ ለህጻኑ ስላዘነች በፈርዖን ቤት አደገ።

ከስደቱ እስከ እረፍቱ ባጭሩ ለማስተካከል

ካደገ በኋላ አንድ የግብፅ ባሪያ አሳዳሪ እስራኤላዊ አሽከሩን ሲደበድብ አይቶ ሙሴ ግብጻዊውን ገደለው። ሆኖም ይህ ጉዳይ በግብጽ ባለስልጣኖች ዘንድ እየተሰማ ስለሄደ ሙሴ ወደ ምድያም አገር ተሰደደ። በዚያ ለ40 አመት ያክል ሲቀመጥ የካህኑን ዮቶርን በጎች ይጠብቅ ነበር። በዚህ ጊዜ የድሮው ፈርዖን ሞቶ አዲስ ፈርዖን በግብፅ ነግሶ ነበር።

በአዲሱ ፈርዖን ዘመን የእስራኤላዊያኑ ጭቆና ባሰ እንጅ አልቀነሰም። ከኮሬብ ተራራ በሚገኝ ቁጥቋጦ ውስጥ በተገለጠለት መልዕክት መሰረት ሙሴ እድሜው 80 ከሞላ በኋላ ወደ ግብፅ ተመለሰ ።

 
እግዚአብሔር ሙሴን በምትቃጠለው እፀጳጦስ ሆኖ እስራኤላውያንን ነፃ እንዲያወጣ ሲያዘው

የመመለሱም ዋና ዓላማ እስራኤላውያኑ ግብፅን ለቀው እንዲወጡ አዲሱን ፈርዖን ለማስፈቀድ ነበር። አዲሱ ፈርዖን እምቢ ስላለ ሙሴ 10 መቅሰፍቶችን በግብፅ ላይ ከፈፀመ በኋላ ንጉሱ ስለተስማማ እስራኤላውያንን እየመራ ፣ ቀይ ባሕርን በእግዚአብሔር ኃይል ከፍሎ በደረቅ ምድር ላይ አሳልፏቸው ከተገዙበት ግብፅ አውጥቶ በሲናይ (ሲና) በረሃ ብዙ ታአምራትን እያደረገ ፣ ውሀ ከዲንጋይ እያፈለቀ ፣ ከፀሐይ በደመና እየጋረደ ፣ በሌሊት ብርሃን እያደረገ ፣ መና ከሰማይ እያወረደ ሌላም ብዙ ተአምር የሠራ መርቷቸዋል ።

 
እስራኤላውያ ቀይባሕርን ሲሻገሩ

በዚህ ወቅት እስራኤላውያኑ በኮሬብ ተራራ ተመስርተው የኤዶምን ደንበሮች ያስሱ ነበር ።

 
ሙሴ ጽላቱን ሲቀበል

አሥርቱ ትዕዛዛትን ሙሴ የተቀበለው በዚህ ወቅት ነበር። በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ሙሴና ህዝቡ ለ40 ዓመት በበረሃው ውስጥ ከዋተቱ በኋላ ሙሴም ወደ ተስፋይቱ ምድር ወደ ከነዓን ሳይገባ እሱን እንዲተካው እያሱን መርጦ በዚሁ በስደት ወራት እድሜው 120 ሲሆን አልፏል።

የኖረበት ዘመን አጭር መረጃ ለማስተካከል

በታሪክ አጥኝዎች ዘንድ፣ ሙሴ መቼ እንደኖረ በዕርግጥ አይታወቅም። አንድ አንድ ተመራማሪዎች የኖረበትን ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት በ13ኛው ክፍለዘመን ሲያደርጉ ሌሎች ከዛ በፊት ነው ይላሉ። ይህም ግመት በዚያው ክፍለ ዘመን መጨረሻ የገዛው ፈርዖን መርነፕታህ በጽላቱ የእስራኤል ስም መጀመርያው ስለ ጠቀሰው ነው፤ እንዲሁም የአባቱም ስም ራምሴ በኦሪት ዘጸአት ፩፡፲፩ የከተማ ስም ሆኖ ስለ ታየ ነው። ንጉሥ ዳዊት ግን በእስራኤል በ1000 ዓክልበ. ያህል ስለ ገዛ፣ ጸአቱ በመርነፕታህ ዘመን ሆነ ማለቱ ለእብራውያን ዘመነ መሳፍንት አይበቃም። በፈርዖኑ፪ ራምሴ ሥር የተገነባው ፒ-ራምሴስ በጥንቱ አቫሪስ ሥፍራ ስለ ሆነ፣ የከተማው ኋለኛው ስም በተቀበለው ጽሑፍ እንደ ተገኘ መስሏል። ሌላው የተሰየመው ከተማ ፊቶም (ፒጦት በኩፋሌ) በግብጽኛ ፐር-አቱም ተብሎ ከአቫሪስ ዘመን መኖሩ ታውቋል።

በኩፋሌ ለማስተካከል

መጽሐፈ ኩፋሌ ዘንድ የእግዚአብሔር መላእክት ለሙሴ በደብረ ሲና ላይ ያቀረቡት ቃል ነው። ይህ የሆነበት ዓመተ ዓለም አዳምሕይዋንኤዶም ገነት ከወጡ 2,410 ዓመታት በኋላ እንደ ነበር በኢዮቤልዩና በሱባዔ አቆጣጠር ያመለክታል። ዕብራውያንን ከግብጽ ባርነት ወደ ደብረ ሲና የመሩዋቸውም በ2410 ዓ.ዓ. እንደ ሆነ ይነግረናል።

የመጽሐፈ ኩፋሌ ዜና መዋዕል አከፋፈል በጠቅላላ ከሥነ ቅርሳዊ መዝገቦች ጋር ሊነጻጽር ይችላል። በዚህ አከፋፈል 2410 ዓ.ዓ. ማለት ከክርስቶስ ልደት በፊት (እንደ ኢትዮጵያዊ አቆጣጠር) 1661 ዓመታት አካባቢ እንደ ነበር ሊገመት ይቻላል።

  • 2149 ዓ.ዓ. (1922 ዓክልበ. ግ.) - የያዕቆብ ልጅ ዮሴፍ ወደ ግብጽ ባርነት ተሸጠ።
  • 2164 ዓ.ዓ. (1907 ዓክልበ. ግ. - ዮሴፍ የፈርዖን ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነ።
  • 2171 ዓ.ዓ. (1900 ዓክልበ. ግ.) - የ፯ አመት ታላቅ ረሃብ በመካከለኛው ምሥራቅ ጀመረ
  • 2172 ዓ.ዓ. (1899 ዓክልበ. ግ.) - የተረፉት የእስራኤል ልጆች ከከነዓን ወደ ጌሤም አገር (በአባይ ወንዛፍ) ፈለሱ።
  • 2242 ዓ.ዓ. (1829 ዓክልበ. ግ.) - ዮሴፍ በግብጽ ዓረፈ።
  • 2263 ዓ.ዓ. (1808 ዓክልበ. ግ.) - ዕብራውያን የወንድሞቹን ሬሳዎች ወደ ከነዓን አድርሰው ብዙዎችም ወደ ግብጽ ተመልሰው ጥቂቶቹ ግን ከነሙሴ አባት ዕብራን (ወይም እንበረም እንደ ኦሪት ዘጸአት) በኬብሮን ቀሩ። የከነዓን ንጉሥ መምከሮን ከግብጽ ፈርዖን ጋር ስለ ተዋጋ የግብጽ በር ተዘጋ።
  • 2303 ዓ.ዓ. (1768 ዓክልበ. ግ.) - የሙሴ አባት ዕብራን ከከነዓን ወደ ጌሤም ተመለሰ።
  • 2330 ዓ.ዓ. (1741 ዓክልበ. ግ.) - የዕብራውያን መከራ ዘመን በጨካኝ ፈርዖን ተጀመረ። ሙሴ በጌሤም ተወለደ።
  • 2372 ዓ.ዓ. (1699 ዓክልበ. ግ.) - ሙሴ ከግብጽ ወደ ምድያም ሸሸ።
  • 2410 ዓ.ዓ. (1661 ዓክልበ. ግ.) - ሙሴ ከምድያም ወደ ግብጽ ይመልሳል፣ ፲ የግብጽ መቅሰፍቶች፣ ዕብራውያን ወደ ሲና በረሃ አመለጡ፣ ሕገ ሙሴን በደብረ ሲና ይቀበላሉ።

በዚህ አከፋፈል፣ እስራኤል ከነዓንን የወረረበት ወቅት ከ፵ ዓመት በኋላ (2450 ዓ.ዓ. ወይም 1621 ዓክልበ.) ጀመረ፣ ሙሴም ከዮርዳኖስ ወንዝ ምሥራቅ አንዳንድ አሞራዊ አገር አሸንፎ ወንዙን ሳይሻገር ግን በዚያው ዓመት እንዳረፈ በኦሪት ይዘገባል።

በ1661 ዓክልበ. የግብጽ ሃይል እጅግ ተደከመ፣ ከመርነፈሬ አይ በኋላ የተከተሉት ፈርዖኖች ከዋና ከተማቸው ከጤቤስ ውጭ ሥልጣን አልነበራቸውም። በዚያም ጊዜ ሂክሶስ የተባለው የአሞራውያን ብሔር ጌሤምን ወረሩ፣ ከግብጻውያንም ጋራ ይዋጉ ጀመር። እነዚህ ሂክሶስ (ወይም «15ኛው ሥርወ መንግሥት») በመጨረሻ በ1548 ዓክልበ. ከግብጽ ተባረሩ፣ የታሪክ ጸሐፊዎች ግን ብዙ ጊዜ ይህን ድርጊት ከጸአቱ ጋራ ይደናገሩ ነበር። ሆኖም በጌሤም የገዛው «14ኛው ሥርወ መንግሥት» (1821-1742 ዓክልበ. ግ.) የተባሉት ነጋዴዎችና እረኞች ለሥነ ቅርስ ታውቀዋል።

ደግሞ ይዩ ለማስተካከል