1 ነፈርሆተፕ ኻሰኸምሬ ግብጽ2ኛው ጨለማ ዘመን (13ኛው ሥርወ መንግሥት) ከ1701 እስከ 1690 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛ ፈርዖን ነበረ። የ3 ሶበክሆተፕ ተከታይ ነበረ።

ነፈርሆተፕ ኻሰኸምሬ
የነፈርሆተፕ ምስል
የነፈርሆተፕ ምስል
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1701-1690 ዓክልበ. ግ.
ቀዳሚ 3 ሶበክሆተፕ
ተከታይ ካነፈሬ 4 ሶበክሆተፕ
ባለቤት ሰነብሰን
ሥርወ-መንግሥት 13ኛው ሥርወ መንግሥት
አባት ሀዓንኸፍ

ቶሪኖ ቀኖና ዘንድ ኻሰኸምሬ ነፈርሆተፕ ለ፲፩ ዓመት ገዛ ሲለን ለእርሱ ብዙ ሐውልቶችና ቅርሶች ይታወቃሉ። እንደ ቀዳሚው ፫ ሶበክሆተፕ ከወታደራዊ ቤተሠብ እንደ መጣ ይመስላል። አባቱ ሀዓንኸፍና እናቱ ከሚ ነበሩ፤ የዚህም ሀዓንኸፍ አባት ነሂ እናቱም ሰነብቲሲ ተባሉ። ይህም ነሂ «የከተማ ሻለቃ» የሚመስል ማዕረግ እንደ ነበረው ይታወቃል። የሀዓንኸፍ ፫ ልጆች ሁሉም ፈርዖኖች ስለ ሆኑ በበርካታ ጽላቶች ይከበራል። የነፈርሆተፕ ልጆች ደግሞ ልዑል ሀዓንኸፍና ልዕልት ከሚ ተባሉ።

ጌባል (በፊንቄ) የተገኙት ቅርሶች የነፈርሆተፕ «አገረ ገዥ» በጌባል «ያንቲኑ» እንደ ነበር ያስረዳሉ። እሱም ከማሪ ጽላቶች ያንቲን-ዓሙ «የጌባል ንጉሥ» ይባላል። ይህም ነፈርሆተፕ በባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ዘመን እንደ ነገሠ ማስረጃ ነው።

የ፩ ነፈርሆተፕ ምስል

ወደ ነፈርሆተፕ ዘመን መጨረሻ ወንድሙ ሲሐጦር ከእርሱ ጋራ የጋርዮሽ ፈርዖን ተደርጎ ሲሐጦር በጥቂት ወራት ውስጥ እንደ ሞተ ይመስላል፤ ከዚያም ሌላ ወንድማቸው ካነፈሬ 4 ሶበክሆተፕ የጋርዮሽ ፈርዖን ሆነ። ከዚያም ትንሽ በኋላ ነፈርሆተፕ ዓርፎ ካነፍሬ ሶበክሆተፕ ለብቻ ፈርዖን ሆነ።

ቀዳሚው
3 ሶበክሆተፕ
ግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን
1701-1690 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ካነፈሬ 4 ሶበክሆተፕ

ዋቢ ምንጭ ለማስተካከል

  • K.S.B. Ryholt: The Political Situation in Egypt during the Second Intermediate Period, c. 1800 – 1550 BC, Carsten Niebuhr Institute Publications, vol. 20. Copenhagen: Museum Tusculanum Press, 1997 (እንግሊዝኛ)