አብርሃምመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት በዑር ከላውዴዎን አብራም ተብሎ ተወልዶ በኋላ ወደ ካራንና ወደ ከነዓን ግብፅም የሄደው የዕብራውያንና፣ የእስማኤላውያን የብዙ ሕዝቦች አባት ነበረ።

አብርሃም
ሥላሴ በአብርሃምና በሳራ ቤት እንደተስተናገዱ

ሥላሴ ቤተክርስቲያን የሚገኝ የመስኮት ሥዕል አዲስ አበባ
የብዙ ሕዝብ አባት
የመጀመሪያ ስሙ አብራም በኋላ አብርሃም
አባቱ ታራ
ባለቤቶቹ ሳራ
አጋር ዕቁባቱ
በመጨረሻም ኩትራ
ልጆቹ እስማኤል
ይስሐቅ
ዝምራን
ጆክሻን
ሜዳን
ሚዲያን
ኢሽባክ
ሹሃ
ወንድሞቹ ሃራን
ነሆር
የአጎቱ ልጅ ሎጥ
የትውልድ ቦታ ዑር ከላውዴዎን
ያረፈበት ቦታ ኬብሮን
ያስከተለው የአይሁድ ክርስትናና እስልምና ሃይማኖት
አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ሊሰዋ ሲል


የአብርሃም ታሪክ በተለይ የሚታወቀው ከብሉይ ኪዳን ኦሪት ዘፍጥረት መጽሐፍ ውስጥ ነው። በተጨማሪ መጽሐፈ ኩፋሌ ስለ አብርሃም ሕይወት ብዙ ምዕራፍ ይሰጣል።

የአብርሃም ዕድሜ በመጽሐፈ ኩፋሌ ለማስተካከል

  • 1876 ዓመተ ዓለም (ዓ.ዓ.) - አብራም ለአባቱ ታራ እና ለእናቱ ኤድና በዑር ከላውዴዎን ተወለደ።
  • 1886 ዓ.ዓ. - ሦራ (በኋላ ሣራ) ተወለደች (?)።
  • 1891 ዓ.ዓ. - አብራም ወጣት ሆኖ በከብት የሚስብ ማረሻ ፈጠረ።
  • 1903 ዓ.ዓ. - አብራም አባቱን ታራን በጣኦታት ለምን ታምናለህ ብሎ ጠየቀው።
  • 1925 ዓ.ዓ. - አብራም ሦራንን አገባት።
  • 1932 ዓ.ዓ. - ሎጥ ተወለደ።
  • 1936 ዓ.ዓ. - አብራም የዑርን አረመኔ መቅደስ አቃጠለና ወደ ካራን ሸሸ።
  • 1950 ዓ.ዓ. - የሰናዖር ንጉሥ አምራፌልና የኤላም ንጉሥ ኮሎዶጎምርሰዶምን አካባቢ በከነዓን ያዙ።
  • 1951 ዓ.ዓ. - እግዚአብሔር አብርሃምን ባረከው፣ አብርሃምም ሰማያዊ ቋንቋ ለመማር ጀመረ።
  • 1953 ዓ.ዓ. - አብርሃም ከካራን ወደ ከነዓን ተጓዛ።
  • 1954 ዓ.ዓ. - ኬብሮን በከነዓን ተሠራ።
  • 1956 ዓ.ዓ. - አብርሃም ወደ ግብፅ ሄደ።
  • 1961 ዓ.ዓ. - ጣይናስ በግብጽ ተሠራ።
  • 1963 ዓ.ዓ. - አብርሃም ወደ ከነዓን ወደ ቤቴል ተመለሰ። ሰዶም በኤላም ላይ አመጸ።
  • 1964 ዓ.ዓ. - የነገስታት ጦርነት፦ የአብርሃም ሠራዊት አምራፌልን ወዘተ. አሸነፉ። አብርሃምም በምላሽ ስንኳ አንዳችም ሲባጎ ከሰዶም ንጉሥ እንዳይወስድ አሻፈረኝ ነገረለት ። መልከ ሴዴቅ አብርሃምን ባረከው።
  • 1965 ዓ.ዓ. - እስማኤል ተወለደ።
  • 1979 ዓ.ዓ. - እሳት ከሰማይ ወርዶ ሰዶምንና ገሞራን አጠፋ። አብርሃም ወደ ቤርሳቤ ሄደ፣ ይስሐቅ ተወለደ።
  • 1982 ዓ.ዓ. - እስማኤልና እናቱ ሀጋር ወደ ፋራን ምድረ በዳ ተሰደዱ።
  • 2003 ዓ.ዓ. - አብርሃምና ይስሐቅ ወደ ደብረ ጽዮን ተጓዙ፤ ወደ ቤርሳቤ ተመለሱ።
  • 2010 ዓ.ዓ. - አብርሃም ከቤርሳቤ ወደ ኬብሮን ተመለሰ።
  • 2024 ዓ.ዓ. - ሣራ ዐረፈች፤ ለመቃበርዋም አብርሃም ዋሻ ከኬጢያውያን ሰው ከኤፍሮን ገዛ።
  • 2027 ዓ.ዓ. - ይስሐቅ ርብቃን አገባት፣ አብርሃምም ከጡራን አገባት።
  • 2046 ዓ.ዓ. - ያዕቆብኤሳው ለይስሐቅ ተወለዱ።
  • 2060 ዓ.ዓ. - አብርሃም አረፈ።
: