ምጽራይም (ዕብራይስጥמִצְרָיִם /ሚጽራዪም/) በኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 10 መሠረት ከኖህ ልጆች መካከል የካም ሁለተኛ ልጅ ነበረ። የምጽራይምም ልጆች ሉዲምዐናሚምላህቢምነፍታሌምፈትሩሲምከስሉሂምቀፍቶሪም ናቸው።

የ«ሚጽራዪም» ትርጉም በዕብራይስጥ ደግሞ ግብጽ (ምሥር) አገር ነው። እንዲሁም በአረብኛ የአገሩ ስም مصر (ምጽር) ይባላል። ስሙ ዕጅግ የቆየ መሆኑ እርግጠኛ ነው። በአካድኛ መዝገቦች የግብጽ ስም «ሙሱር»፣ «ሙስሪ»፣ በኡጋሪትም ጽላቶች «ምስርም» ተብሏል።

አባ አውሳብዮስ በጻፉት ዜና መዋዕል ዘንድ፣ የድሮ ግብጻዊው ባለታሪክ ማኔጦን (3ኛው ክፍለ ዘመን ዓክልበ.) ስለ ኋለኞቹ ግብጻውያን ሲጽፍ፣ ይኮሩበት የነበረው የታላቁ ጥንት ዘመን ከማየ አይህ አስቀድሞ እንዳለፈ፣ በኋላም በዚያው አገር ዳግመኛ ከሠፈረበት ከካም ልጅ ምጽራይም በውኑ እንደ ተወለዱ ጽፎ ነበር። ተመሳሳይ ታሪክ በእስላም ጸሐፊዎች በግብጻዊው እብን አብድ ኤል-ሀከም እና በፋርሳውያን አል-ታባሪሙሐመድ ቈንዳሚር መጻሕፍት ሲገኝ፣ ፒራሚዶችእስፊንክስ ወዘተ. ሁሉ የተሠሩ ከጥፋት ውኃ በፊት በኖሩት ክፉ ዘሮች ሆኖ፣ ከዚያ በኋላ ግን አገሩ ለካም ተወላጅ ለምጽራይም (ማሣር ወይም መሥር) ተሠጠ ብለው ጻፉ። በነዚህም ደራስያን ዘንድ የመሥር ዕድሜ እስከ 700 መቶ አመት ድረስ ደረሰ።

ፊንቄ አፈ ታሪክ ዘንድ፣ «ሚሶር» የሚባል ሰው የታዓውቶስ አባት ሲሆን የጌባል ንጉሥ ክሮኖስ ግብጽን ለዚሁ ታዓውቶስ እንደ ሰጠ ይታመን ነበር።

በዕብራይስጥ ስዋሰው «-አዪም» የሚለው ባዕድ መድረሻ የድርብ ቁጥር ምልክት ሲሆን ስሙ 'ሁለት ምድሮች' ይመስላል፤ የዚህም ትርጉም በጥንታዊ ግብጽኛ «-ታ-ውይ» ነው። ከመጀመርያው መካከለኛ ዘመን ጀምሮ ግብጽ «-ታ-ውይ» (ሁለቱ ምድሮች ወይም «ላይኛው መንግሥት» እና «ታችኛው መንግሥት») ይባል ነበር። ይህም በ፱ኛው ሥርወ መንግሥት ፈርዖን ስም መሪብታዊ ቀቲ (2300 ዓክልበ. አካባቢ) ይታያል።

ጸሓፊው ጊዮርጊስ ስንቄሎስ (800 ዓ.ም. አካባቢ) አስተሳሰብ ግን ምጽራይም የግብጽ ቀድሞ ዘመን መንግሥት የመሠረተው ፈርዖን መኔስ እንደ ነበረ ገመተ።

ሌሎች አጻጻፎች ለማስተካከል

  • ግሪክ ትርጉም፦ Μεστράιμ /መስትራይም/
  • በአማርኛ መጽሐፈ ኩፋሌ፦ ሜስጥሮም
  • ኦሪት ዘፍጥረት፣ ልዩ ልዩ ግዕዝ ቅጂዎች፦ ምሴጣሬም፣ ሴጣሬም፤ ሚጣራም፣ ምስጢየረም
  • በግዕዝ መጽሐፈ ኩፋሌ፦ መስጥሬም
  • በ1879 አማርኛ ኦሪት ዘፍጥረት፦ ሚስራይም