ዓፄ ዘድንግል1603 እስከ 1604 እ.ኤ.አ. የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት የነበሩ ሲሆን የዙፋን ስማቸውም «ዳግማዊ አፅናፍ ሰገድ» ሲሆን የአጼ ስርፀ ድንግል ወንድም የልሳነ ክርስቶስ ልጅ ናቸው።

ዓፄ ዘድንግል
ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ
ግዛት ከ1603 እስከ 1604 እ.ኤ.አ.
ቀዳሚ ዓፄ ያዕቆብ
ተከታይ ዓፄ ያዕቆብ
ሙሉ ስም ዳግማዊ አፅናፍ ሰገድ (የዙፋን ስም)
ሥርወ-መንግሥት ሰሎሞን
አባት ልሳነ ክርስቶስ
የተቀበሩት ደጋ እስጢፋኖስ ቤ/ክርስቲያን፣ ደጋ ደሴት

አጼ ስርጸ ድንግል ከመሞታቸው ቀደም ብሎ የወንድማቸውን ልጅ ተተኪ ንጉስ ለማድረግ አስበው ነበር፣ ይህንንም ያሰቡት የራሳቸው ልጆች በእድሜ ህጻናት ስለነበሩና በዚህ ምክንያት የርስ በርስ ጦርነት እንዳይነሳስ ነበር። ነገር ግን ንግስት ማርያም ሰና (የንጉሱ መጀመሪያ ሚስት)ና ራስ አትናቲወስ ንጉሱ ከ ፈላሻዋ ቅምጡ ሐረግዋ የወለደውን የ7 አመቱን ያዕቆብ ንጉሰ ነገስት በ1597 እንዲሆን አደረጉ። ይህም ልጁ ህጻን ስለሆነ የሱ ሞግዚት በመሆን ስልጣኑን በተዘዋዋሪ ለመቆጣጠር ነበር። በዚህን ጊዜ ጦርነት እንዳይነሳ ዘ-ድንግልን በጣና ሃይቅ በሚገኘው ደቅ ደሴት እንዲታሰር አደረጉ።

ይህ በዚህ እንዳለ ዘ-ድንግል ከእስራቱ አምልጦ በጎጃም ውስጥ ተሸሸገ። በ1603 የጉራጌው ራስዘ ስላሴ ዘ-ድንግልን ንጉሰ ነገስት አፅናፍ ሰገድ አድርጎ ሾመው። አዲሱ ንጉስ ግን በዳንካዝ ቤተ መንግስቱ የጀስዩቱን መሪ ፔድሮ ፔዝ በማስመጣት የካቶሊክ እምነት ተከታይ ሆነ። በዚህ ጊዜ ያነገሱት ራስ ዘ ስላሴ ዘድንግልን መቃወም ብቻ ሳይሆን ከስልጣኑም እንዲወርድ በጎጃም አመጽ ማነሳሳት ጀመሩ። ይን አመጽ ለማስቆም ጥቅምት 16፣ 1604 አጼ ዘድንግል ከ200 ጠብመንጃ ከታጠቁ ፖርቹጋሎች ጋር በመሆን በባርቾ ሜዳ ላይ ዘመተ። አማጺወቹ የንጉሰ ነገስቱን ጦር ከማሸነፋቸው በተጨማሪ፣ ንጉሱንም ገደሉት። ጄምስ ብሩስ እንደመዘገበው የንጉሱ ሰውነት እስከ 3 ቀን በሜዳው ላይ ካረፈ በኋላ ያካባቢው ገበሬወች ትንሽ መቃብር ሰርተው በዚያው ሜዳ እንደቀበሩት ያትትታል። ከ10 አመት በኋላም ወደጁ የነበረው የአጎቱ ልጅ ሱሰንዮስ ሬሳው ተቆፍሮ ወጥቶ በደጋ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን፣ ደጋ ደሴትጣና ሃይቅ ከሌሎች ቀደምት ነገሥታት ጎን እንዲያርፍ አድርጓል። [1]

ማጣቀሻወች ለማስተካከል

  1. ^ James Bruce, Travels to Discover the Source of the Nile (1805 edition), vol. 3, pp. 270f