ነሐሴ 26 ቀን: የሕገመንግስት ቀን በስሎቫኪያ...

፲፯፻፯ ዓ/ም በአውሮፓ ንጉዛት በረዥምነት አንደኛው ንጉሥ ሉዊ ፲፬ኛ ለ፸፪ ዓመታት በፈረንሳይ ዙፋን ላይ ከተቀመጡ በኋላ በዛሬው ዕለት አረፉ።

፲፱፻፲፭ ዓ/ም በጃፓን ውስጥ በተነሳ የመሬት እንቅጥቅጥ አደጋ በቶክዮ እና ዮኮሃማ ከተሞች እስከ መቶ ሃምሳ ሺህ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።

፲፱፻፴፩ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነትአዶልፍ ሂትለር ናዚ ጀርመን ሠራዊቶች ፖላንድን ሲወሩ ብሪታንያ እና ፈረንሳይ በአጋርነት ጀርመን ላይ ጦርነት አወጁ።

፲፱፻፶፫ ዓ/ም ራስ አዳል (አዳል ተራራ) በተባለ ቦታ በሀሚድ ኢድሪስ አዋቴ እጅ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የፖሊስ አባል ሲገደል የኤርትራ ነጻነት ትግል በይፋ ተጀመረ።

፲፱፻፷፩ ዓ/ም በሊቢያ ንጉዛት ውስጥ የተነሳው አብዮት ንጉሥ ኢድሪስን ከሥልጣን አውርዶ ሙአማር ጋዳፊን ሥልጣን አስጨበጠ።

፲፱፻፸፫ ዓ/ም በመካከለኛው የአፍሪቃ ሪፑብሊክ የተካሄደው ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት አገሪቱን ከነጻነት ጀምሮ የመሩትን ፕሬዚደንቱን ዴቪድ ዳኮን ከሥልጣን አወረደ።