ቡልጋአማራ ክልልሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኝ ወረዳ ሲሆን አቀማመጡ በአብዛኛው ከቆላ እስከ ወይና ደጋ ነው። የወረዳው አስተዳደር ፣ የሀገረ ማርያም ከሰም ወረዳ ሲባል ሀገረ ማርያም (ሾላ ገበያ ) የሚባለው የገጠር ከተማ ላይ ይገኛል።

በወረዳው ውስጥ የዳግማዊ ምኒልክ ምሽግና የመሳሪያ ግምጃ ቤት የነበረችው ኮረማሽ የምትገኝበት ወረዳ ሲሆን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት ተከታዮች እንደሚያውቁት ቡልጋ የብዙ ኢትዮጵያውያን ቅዱሳን እና ቅዱሳት የትውልድ አገርም ነች።

፲፱፻፺፱ ዓ/ም የሕዝብ ቆጠራ ውጤት እንደሚያመለክተው በወረዳው ውስጥ ፶፭ ሺህ ፪፻፩ ሰዎች ሲኖሩ የወንዶች ብዛት ፳፰ ሺህ ፫፻፸፭ እና ሴቶች ደግሞ ፳፮ ሺህ ፰፻፳፮ እንደሆኑ ይጠቁማል። ከነኚህ ቡልጎች ፶፫ ሺህ ፲፭ቱ ሰዎች የገጠር ነዋሪዎችና በግብርና የተሠማሩ አርሶ አደሮች እንደሆኑ ያረጋግጣል።[1]

ታሪክ ለማስተካከል

የታወቁ የቡልጋ ተወላጆች ለማስተካከል

  • አክሊሉ ሀብተ-ወልድ ( ፀሐፌ ትዕዛዝ ) ዲፕሎማት፣ አምባሳዶር፣ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ፤ የጽሕፈት ሚኒስቴር፣ ጠቅላይ ሚኒስቴር
  • [አርበኛ እና የባህል ሐኪም ማሞ ኃይሌ ዘብሔረ ቡልጋ ከሰም]

ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል

  1. ^ Summary & Statistical Report of the 2007 Population & Housing Census, FDRE Population Census Commission