2 ዩባ (60 ዓክልበ. እስከ 15 ዓ.ም. የኖረ) የኑሚዲያ ንጉሥ በኋላም የማውሬታኒያ ንጉሥ ነበረ።

የ2 ዩባ ቅርጽ

2 ዩባ የኑሚዲያ ንጉሥ 1 ዩባ አንድያ ልጅና ወራሽ ነበረ። እናቱ ማን እንደሆነች አልታወቀም። በ54 ዓክልበ. አባቱ በዩሊዩስ ቄሣር ከተሸነፈ በኋላ ራሱን ገደለ። ያንጊዜ ኑሚዲያ የሮማ መንግሥት ክፍላገር ሆነ።

ዩሊዩስ ቄሣር 2 ዩባን ወደ ሮማ አመጣውና ድሉን ለማክበር በሠልፍ አሠለፈው። በሮማ እየቆየ ልጁ ዩባ ሮማይስጥግሪክ ይማር ነበረና የሮማ ዜግነት አገኘ። ለትምህርቱ ትጉህ በመሆኑ ከሮማ ሊቃውንት አንዱ ሆነና እድሜው 20 አመት ሲሆን «የሮማ ሥነ ቅርስ» የተባለ መጽሐፍ ጻፈ። አሳዳጊዎቹ ዩሊዩስ ቄሣርና በኋላ ኦክታውያኑስ (ከዚያ ወደፊት አውግስጦስ ቄሣር የተባለውን ስያሜ የወሰደ) ነበሩ። ዩባ ከኦክታውያኑስ ጋር ሲዘመት የመሪነት ልምምድ አገኘ። በ39 ዓክልበ. በአክቲዩም ውግያ በኦክታውያን አጠገብ ተዋጋ።

የ2 ዩባ መሐልቅ

በ33 ዓክልበ. አካባቢ አውግስጦስ ዩባን ወደ ኑሚዲያ ዙፋን መለሰው። ኑሚዲያ ግን ለሮማ መንግሥት ተገዥና ታማኝ ሆኖ ማገልገሉ እርግጥኛ ነው። በ27 ዓክልበ. አካባቢ አውግስጦስ ለ2 ክሌዎፓትራ ሰሌኔ በትዳር ሰጠው፣ ትልቅ ጥሎሽንም ጨምሮ ንግሥቱም ሆና ሾማት። ይች የግብጽ ንግሥት 7 ክሌዎፓትራና የሮማ መሪ ማርክ አንቶኒ ልጅ ነበረች። በዚህ ወቅት አውግስጦስ ከኑሚዲያ ወደ ማውሬታኒያ ዙፋን አዛወራቸው።

የኑሚዲያና ማውሬታኒያ ሥፍራ በደቡብ-ምዕራብ

ዩባና ክሌዎፓትራ በማውሬታኒያ ሲደርሱ ዋና ከተማቸው ቄሣርያ ተባለ (የአሁኑ ሸርሸልአልጄሪያ)።

2 ዩባ የትምህርት፣ ኪነትና ሳይንስ ምርመራ ማዕከል አደረገው። ከዚህ ደግሞ ታላቅ የንግድ ደጋፊ ሆነ። ለውጭ አገር የተላኩት ነገሮች በተለይ ዓሣወይንሉልበለስእህል፣ የእንጨት እቃ፣ ከዛጎልም አሳ የተለቀመ ሐምራዊ ቅለም ነበሩ። ቲንጊስ (በጂብራልታር ወሽመጥሞሮኮ ዳርቻ) ዋና የንግድ ወደብ ሆነ። እንዲሁም አውግስጦስ በጋዲር ላይ (በእስፓንያ በኩል) አለቃ ሆኖ አሾመው።

2 ዩባ እራሱ ብዙ መጽሐፍት ስለ ታሪክ፣ ሥነ ፍጥረት፣ መልክዐ ምድር፣ ስዋሰው፣ ስዕልና ቴያትር በግሪክና በሮማይስጥ ጻፈ። ስለ አረቢያ የጻፈው ጽሑፍ በተለይ በሮማ ይወድድ ነበር። ከጻፋቸው መጽሐፍት ግን ትንሽ ከፊል ብቻ አሁን ይገኛል።

በተጨማሪ 2 ዩባ ወደ ካናሪ ደሴቶችና ወደ ማደይራ ተጓዦችን ላከ። አውሬ ውሾች በካናሪ ደሴቶች ስለ ተገኙ፣ ዩባ ስማቸውን «ካናሪዩስ» ('የውሾቹ' ማለት ነው) አላቸው።

13 ዓ.ም. ዩባ ልጁን ቶሌሚን አብሮ እንዲነግሥ አደረገ፤ በ15 አረፈ። ቶሌሚም ለብቻ የማውሬታኒያ ንጉሥ ሆነ።

ምንጮች ለማስተካከል