ጥቅምት ፳፱

  • ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. - በአሜሪካ ሰሜን ምዕራብ የሚገኘውና ስሙ ከስፓኝኛ ቋንቋ ሞንታኛ (ተራራ) የመጣው ሞንታና የተባለው ክልል የአሜሪካ ሕብረትን በመቀላቀል አርባ አንደኛው ክፍለ ግዛት ሆነ።
  • ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. - በብሪታንያ የሞት ቅጣትን የሚሽር ሕግ በአገሪቷ ንግሥት ስምምነትና ፊርማ ተደነገገ።
  • ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአድአን አካባቢ በዘመናዊ ግብርና ለማልማት የሚያስችል፣ በ፵ ዓመት የሚከፈል የሦስት ተሩብ ሚሊዮን ብር (E$3.25 million) ብድር ውል ከአሜሪካ መንግሥት ጋር ተፈራረመ።