ሐምሌ ፲፫ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፫፻፲፫ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፶፫ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ዮሐንስማቴዎስ፤ እና ማርቆስ ደግሞ ፶፪ ቀናት ይቀራሉ።

አቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች ለማስተካከል

  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በቆጵሮስ ደሴት ላይ በተካሄደ መፈንቅለ መንግሥት የአገሪቱ ፕሬዚደንት ሊቀ ጳጳስ ማካሪዮስ ከስልጣን በወረዱ በአምስተኛው ቀን፣ የቱርክ ሠራዊቶች ደሴቷን ወረሩ። እስካሁንም ይቺ ደሴት ለሁለት ተከፍላ የግሪክ ቆጵሮስ እና የቱርክ ቆፕሮስ በመባል የሁለቱ ዘሮች የልዩነት መተዳደሪያ ደሴት ናት።
  • ፲፱፻፺፱ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የምርጫ ፺፯ ውጤት ተጭበርብሯል በማለታቸው የአገሪቱን ሕገ መንግሥት ተቃራኒዎች ናችሁ በመባል ታሥረው የነበሩት የቅንጅት መሪዎችና ሌሎችም በተደረገላቸው “ምሕረት” ተለቀቁ።

ልደት ለማስተካከል

ዕለተ ሞት ለማስተካከል

፲፱፻፵፫ ዓ/ም የዮርዳኖስ ንጉሥ፣ ቀዳማዊ አብዱላ

ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል