ላርሳ (አረብኛ፦ ተል-አስ-ሠንከረህ) ከ1844 እስከ 1675 ዓክልበ. ድረስ የሜስፖጦምያ ከተማ-ግዛት ነበረ።

ላርሳ
(ተል-አስ-ሠንከረህ)
የላርሳ ነገሥታት ዝርዝር
ሥፍራ
ላርሳ is located in መስጴጦምያ
{{{alt}}}
መንግሥት የላርሳ መንግሥት
ዘመን 1844-1675 ዓክልበ.
ዘመናዊ አገር ኢራቅ
ጥንታዊ አገር ሱመር

ከተማው በኤአናቱም ዘመን (2200 አካባቢ) መኖሩ ይታወቃል። በ1844 ግን የኢሲን መንግሥት በሱመር ላይኛ ሥልጣን እየሆነ የላርሳ አሞራዊ አለቃ ጉንጉኑም ነጻነቱን ከኢሲን አዋጀ። በ1835 ጉንጉኑም ኡርንም ያዘ።

ላርሳና ኢሲን፣ ከ1807 በኋላ ባቢሎንም ተወዳዳሪዎች ነበሩ። በየጊዜ ሦስቱ እርስ በርስ ጦርነት ያድርጉ ነበር። ኢሲን በ1709 ከወደቀ በኋላ የላርሳ ንጉሥ ሪም-ሲን ለትንሽ ወቅት ላይኛ ሥልጣን ነበር። ነገር ግን የባቢሎን አዲስ ንጉሥ ሃሙራቢ በረታና በ1675 ላርሳን ያዘ።

የላርሳ ነገሥታት ለማስተካከል

(ኡልትራ አጭር)