እማሆይ ፅጌ ማርያም ገብሩ ደስታ ዝነኛ ኢትዮጵያዊ ሙዚቀኛ ሲሆኑ የኢትዮጵያ ክላሲካል ሙዚቃዎች እናት ተብለው ይጠራሉ። ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ለመጀመሪያ ጊዜ በጀርመን ሀገር በሸክላ እንዳስቀረፁ ሁሉ እማሆይ ፅጌ ማርያምም ከዓመታት በኋላ የኢትዮጵያን ክላሲካል ሙዚቃዎች በሲዲ በማስቀረፅ ለዓለም ሕብረተሰብ ያስተዋወቁ የመጀመሪያዋ እንስት ሆነዋል።

የህይወት ታሪክ ለማስተካከል

እማሆይ ፅጌ ማርያም ገብሩ ከአባታቸው ከከንቲባ ገብሩ ደስታ በአዲስ አበባ ከተማ በ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. ተወለዱ። እማሆይ ትምህርታቸውንም ስዊዘርላንድ ውስጥ በሚገኘው ቅዱስ ክርስትና የሰብዓዊ ትምህርትን አጥንተዋል። እማሆይ ፅጌ ማርያም ቫዮሊን መጫወትን ተምረው በ፱ ዓመታቸው ትርኢት ለማሳየት ችለዋል።

ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ ከመላ ቤተሰባቸው ጋር በመሰደድ የጥቁር አንበሳ ጦር ተቀላቅለው በሽምቅ ውጊያ ሦስት ወንድሞቻቸው ተገድለዋል። ጦርነቱ ሲፋፋምም ቤተሰባቸው በሙሉ ተግዘው ወደ ኔፕልስ፣ ጣሊያን በግዞት ተወሰዱ። በእስር ቆይታቸው አብዛኛውን ጊዜያቸውን የሚያሳልፉት ከካቶሊክ መነኮሳት ጋር በመሆኑ በውስጣቸው መንፈሳዊ ሕይወት እንዲያቆጠቁጥ ምክንያት ሆነ።

ከጣሊያን ሽንፈት በኋላም በካይሮ የሙዚቃ ትምህርታቸውን ቀጠሉ። በ21 ዓመታቸው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ የክብር ዘበኛ ሙዚቃ ባንድ ዳይሬክተር ሆነው ሠርተዋል። ይህም የሙዚቃ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉበት አስችሏቸዋል።

እማሆይ ፅጌ ማርያም እንግሊዝኛጀርመንኛዕብራይስጥኛአማርኛግዕዝን አቀላጥፈው ይናገራሉ። የተለያዩ የሙዚቃ ስራዎቻቸውንም በተለያዩ ኮንሰርቶች ላይ በማቅረብ የሚገኘውንም ገንዘብ ለድሆች መርጃ አውለዋል።

የሥራዎች ዝርዝር ለማስተካከል

«Homeless Wonder» /ሆምለስ ወንደር/ ፣ «The Son of Seam» /ዘ ሰን ኦፍ ሲም/፣ «The Mad Man's Daughter» /ዘ ማድ ማንስ ዶተር/ እና «Mother's Love» /ማዘርስ ላቭ/ የሚል አርዕስት ያላቸው ሙዚቃዎች ከበርካታ ሥራዎቻቸው ውስጥ እንደ ምሳሌ ይጠቀሳሉ።

በ2006 እ.ኤ.አ. ፍራንሲሊስ ፋልሴቶ የተባለው ፈረንሳዊ የኢትዮጵያ ባህላዊ ሙዚቃዎችን ሰብስቦ እንደ አዲስ «ኢቶፒክስ» የተባለ ሲዲ ባወጣበት ጊዜ ቁጥር ፳፩ ላይ የእማሆም ሥራዎች አካቷል። ሲዲው በዓለም አቀፍ ደረጃ ካለው ሰፊ ስርጭት አንፃር ስለ እማሆይ ፅጌ ማርያም ቀሪው ዓለም ብዙ እንዲያውቅ ረድቷል።

ማጣቀሻ ለማስተካከል