የ1970 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ

የ1970 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከግንቦት ፳፫ እስከ ሰኔ ፲፬ ቀን ፲፱፻፷፪ ዓ.ም. በሜክሲኮ ተካሄዷል። ይህ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ በሰሜን አሜሪካ የቀረበው የዓለም ዋንጫ ነው። ብራዚል ጣሊያንን ፬ ለ ፩ በመርታት ለ፫ኛ ጊዜ ውድድሩን አሸንፏል። የጁልስ ሪሜት ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ውድድር የተሸለመ ሲሆን ተሸላሚው የብራዚል ቡድን እስከ መጨረሻው ዋንጫውን እንዲይዝ ተፈቅዶለታል።

የ1970 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ

ይፋዊ ምልክት
ይፋዊ ምልክት
ይፋዊ ምልክት
የውድድሩ ዝርዝር
አስተናጋጅ  ሜክሲኮ
ቀናት ከግንቦት ፳፫ እስከ ሰኔ ፲፬ ቀን
ቡድኖች ፲፮ (ከ፭ ኮንፌዴሬሽኖች)
ቦታ(ዎች) ፭ ስታዲየሞች (በ፭ ከተማዎች)
ውጤት
አሸናፊ  ብራዚል (፫ኛው ድል)
ሁለተኛ  ኢጣልያ
ሦስተኛ  ምዕራብ ጀርመን
አራተኛ  ኡራጓይ
እስታቲስቲክስ
የጨዋታዎች ብዛት ፴፪
የጎሎች ብዛት ፺፭
የተመልካች ቁጥር 1,603,975
ኮከብ ግብ አግቢ(ዎች) ምዕራብ ጀርመን ጀርድ ሙለር
፲ ጎሎች
እንግሊዝ 1966 እ.ኤ.አ. ምዕራብ ጀርመን 1974 እ.ኤ.አ.