አባላ አባያ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ውስጥ በዎላይታ የሚገኝ ወረዳ ነው። ወረዳው 16 የቀበሌ አስተዳደሮችን ያቀፈ ሲሆን ከነዚህም 13ቱ ገጠር 3ቱ ደግሞ ከተማ ናቸው። በ6°38′ N ኬክሮስ እና 37° 42′ E ኬንትሮስ መካከል ተቀምጦ ከአዲስ አበባ በደቡብ 419 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል። ወረዳው የተቋቋመው እኤአ በ2019 ከአካባቢው ወረዳዎች ነው። [1] አባላ አባያ በደቡብ በኩል በአባያ ሀይቅ[2] በምዕራብ በሁምቦ ወረዳ፣ በሰሜን በሶዶ ዙሪያ ወረዳ፣ በምስራቅ በሆቢቻ ወረዳ ይዋሰናል። የዚህ ወረዳ የአስተዳደር ማዕከል አባላ ፓራቾ ከተማ ነው።

አባላ አባያ
Abbala Abbaayaa
ወረዳ
በአባላ አባያ አባያ ሀይቅ ዳርቻ
ሀገር ኢትዮጵያ
ክልል ደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት
ዞን ዎላይታ
ርዕሰ ከተማ አባላ ፓራቾ
የሕዝብ ብዛት
   • አጠቃላይ 56,812

የህዝብ ብዛት

ለማስተካከል

የዚህ ወረዳ አጠቃላይ ህዝብ 56,812 አካባቢ ነው። ከዚህም በወረዳው 27,627 አባወራዎች ያሉ ሲሆኑ ከነዚህም 16,981 ወንድ እና 10,646 ሴት አባወራዎች ናቸው። [3]

  1. ^ "Abala Abaya woreda". Archived from the original on 2023-06-10. በ2024-06-23 የተወሰደ.
  2. ^ "direction to Abala Abaya district". Archived from the original on 2021-09-08. በ2024-06-23 የተወሰደ.
  3. ^ "Assessing climate change-induced poverty of mixed crop-livestock smallholders in Wolaita zone". Research in Globalization (ScienceDirect) 7. https://www.sciencedirect.com/science/article/pii/S2590051X23000485.