ትግርኛኢትዮጵያና በኤርትራ የሚነገር የሴማዊ ቋንቋዎች ቤተሰብ አባል ነው። ትግርኛ በኢትዮጵያ የብሄረ ትግራይ ( ተጋሩ ) ኣፍ መፍቻና 3ኛ ከፍተኛ የተናጋሪ ቁጥር ያለዉ ቋንቋ ሲሆን በኤርትራ ደግሞ የብሔረ ትግርኛ የአፍ መፍቻ ቋንቋ ነው:: የቋንቋው ተናጋሪዎች ከ11 ሚሊዮን በላይ ይሆናሉ ተብሎ የሚገመት ሲሆን ፣ ከዚህ ውስጥ ከ8 ሚሊዮን በላይ በትግራይና በተቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚነገር ሲሆን በኤርትራ ከ3 ሚሊዮን በላይ ተናጋሪዎች እንዳሉት ይገመታል:: በኤርትራ የአገሪቱ የሥራ ቋንቋና ኣብዛኞቹ የሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎች እንደ መግባብያ የሚጠቀሙበት ቋንቋ ነው::

ትግርኛ ቋንቋ የግዕዝን ፊደል የሚጠቀም ሲሆን በ ኤርትራ አሁን ብሄረ ትግርኛ በመባል የሚታወቀው የሦስቱ አውራጃዎች ማለትም የሓማሴን: ሰራየ ና ኣከለጉዛይ ሕዝብ የሚጠቀሙበት ሕጊ-እንዳባ የተባለው የህግ ስርዓት ተጽፎበት የሚገኝ ሲሆን የመጀመርያዉ የቋንቋዉ ጽሁፍ ደግሞ ሕጊ ኣድግና ተገለባ የሚባለዉ የኣከለጉዛይ ሕገ ስርዓት ነዉ[1]

ፊደል ለማስተካከል

የትግርኛ ቀለሞች በዓማርኛው ላይ ጥቂት ተጨማሪ ኣሏቸው እንጂ የተቀራረቡ ናቸው። ኣንዳንድ ፀሓፊዎች ግን ከትግርኛ ቀለሞች ውስጥ እነ ""፣ ""፣ ""፣ "" እና "" የራብኦቻቸው ሞክሼዎች መስለዋቸው ተሳስተው ሊቀንሷቸው ኣጥቁረዋቸዋል። እንደ ዶ/ር ኣበራ ሞላ ገለጻ ግን ሆሄያቱ ሞክሼዎች ስላልሆኑ መብታቸው መከበር ኣለበት ነው።

ደግሞ ይዩ ለማስተካከል

የውጭ መያያዣዎች ለማስተካከል

 
Wikipedia
  1. ^ Negash, Abraham, The Origin and Development of Tigrinya Publications, Santa Clara, California2019 p.3