ሠ ሡ ሢ ሣ ሤ ሥ ሦ ሧ



አቡጊዳ ታሪክ

ሠውት (ወይም ሣውት) በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 21ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥሶርያም ፊደሎች 21ኛው ፊደል "ሺን" ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል "ሺን" ተብሎ በ"አብጃድ" ተራ 21ኛ ነው።

አማርኛ አጻጻፍ ብዙ ጊዜ "ሠውት" ከ"ሳት"(ሰ) ጋራ ሊለዋውጥ ይችላል። ቀድሞ ግን በግዕዝ የ"ሠውት" ድምጽ "ሸ" ለማመልከት ይጠቅም ነበር።

ታሪክ ለማስተካከል

ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
   


የሠውት መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የጥርስ ስዕል መስለ።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
    ש  


የከነዓን "ሺን" እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ የአረብኛም "ሺን" ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት "ሲግማ" (Σ, σ/ς) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (S s) እና የቂርሎስ አልፋቤት (С с) እና (Ш ш) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ"ሠውት" ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል።