ሎጋሪዝም ማለት አንድ ቁጥር በስንት ቢነሳ ሌላን ቁጥር ሊሰጥ እንደሚችል የሚሰላበት የሒሳብ መሳሪያ ነው። በሒሳብ ቋንቋ ሎጋሪዝም እንዲህ ይጻፋል፣ log a b {\displaystyle \log _{a}b} ትርጓሜውም «የቁጥር b ሎጋሪዝምን ከመሠረት ቁጥር a አንጻር» ፈልግ ሲሆን «መሠረት ቁጥር a በስንት ቢነሳ ቁጥር b ን ይሰጣል?» ከማለት ጋር አንድ ነው። log a b = x {\displaystyle \log _{a}b=x\,} ሆነ ማለት a x = b {\displaystyle a^{x}=b\,\!} ነው።
ለምሳሌ፦
log 3 9 = 2 {\displaystyle \log _{3}9=2\,} ሲነበብ «የ 9 ሎጋሪዝም ከመሠረት 3 አንጻር ይሆናል 2» ምክንያቱም 32 = 9 ስለሆነ።
ሎጋሪዝምን ፈልስፎ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳተመው ስኮትላንዳዊው ጆን ኔፐር ነበር።