ላይቤሪያ (እንግሊዝኛLiberia)፣ በይፋ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ (እንግሊዝኛ፦ Republic of Liberia)፣ በምዕራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጊኒኮት ዲቯርሴራሊዮን እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ ትዋሰናለች። ላይቤሪያ የቅኝ ግዛት ሆና በ1822 እ.ኤ.አ. ከአሜሪካ በመጡ ነጻ የወጡ ባሪያዎች የተመሠረተች ሲሆን በአካባቢው ግን የተለያዩ ብሔሮች ለብዙ ምእተ አመታት ኖረዋል። መሥራቾቹ ዋና ከተማቸውን ሞንሮቪያ ብለው ለአሜሪካን ፕሬዝዳንት ጄምስ ሞንሮው ሰይመውታል። ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም ነጻነት አወጁና ግዛቷ የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ሆነች። በ1980 እ.ኤ.አ. በወታደራዊ መፈንቅለ-መንግስት የላይቤሪያ አመራር ከወረደ በኋላ ከ1989 እስከ 2005 እ.ኤ.አ. ድረስ ሀገሩዋ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀሉና የሀገሩዋን ኢኮኖሚ ያቃወሱ ሁለት የእርስ-በርስ ጦርነቶችን አይታለች።

የላይቤሪያ ሪፐብሊክ
Republic of Liberia

የላይቤሪያ ሰንደቅ ዓላማ የላይቤሪያ አርማ
ሰንደቅ ዓላማ አርማ
ብሔራዊ መዝሙር ኦል ሄል፣ ላይቤሪያ፣ ሄል!
እንግሊዝኛ፦ All Hail, Liberia, Hail!
የላይቤሪያመገኛ
የላይቤሪያመገኛ
ላይቤሪያ በቀይ ቀለም
ዋና ከተማ ሞንሮቪያ
ብሔራዊ ቋንቋዎች እንግሊዝኛ
መንግሥት
ፕሬዝዳንት
ምክትል ፕሬዝዳንት
ሪፐብሊክ
ጆርጅ ዌያ
ጁወል ተይለር
ዋና ቀናት
ሐምሌ ፳ ቀን ፲፰፻፴፱ ዓ/ም
(July 26, 1847 እ.ኤ.አ.)
 
የነጻነት ቀን
የመሬት ስፋት
አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.)
ውሀ (%)
 
111,369 (103ኛ)
13.514
የሕዝብ ብዛት
የ2008 እ.ኤ.አ. ግምት
የ2005 እ.ኤ.አ. ቆጠራ
 
3,489,072 (132ኛ)
3,482,211
ገንዘብ የላይቤሪያ ዶላር1
ሰዓት ክልል UTC +0
የስልክ መግቢያ 231
ከፍተኛ ደረጃ ከባቢ .lr
1. የአሜሪካ ዶላርም በሰፊ ጥቅም ላይ ነው

የስም አመጣጥ ለማስተካከል

«ላይቤሪያ» ከእንግሊዝኛው liberty (ሊበርቲ፣ ማለትም ነጻነት) ከሚለው ቃል ነው የመጣው።

ታሪክ ለማስተካከል

የምዕራብ አፍሪካ አገሬዎች (ተወላጆች) ለማስተካከል

የአንትሮፖሎጂ ምርምር እንደሚያሳየው ከሆነ፣ በላይቤሪያ ላይ ከ12ኛው ክፍለ-ዘመን ወይም ከዛ በፊት ጀምሮ ሰው ሠፍሯል። መንዴ (Mende) የሚባል ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች ወደ ምዕራብ ሲስፋፉ፣ ሌሎች ታናናሽ ብሄረሰቦችን ወደ ደቡብ ወደ አትላንቲክ ውቅያኖስ ገፍተዋቸዋል። ዴዪ፣ ባሳክሩጎላ እና ኪሲ የሚባሉ ጎሳዎች በአካባቢው ከመጀመሪያ ጀምሮ እንደነበሩ በማስረጃ ይታወቃል። ይህ ፍልሰት የጨመረው የማሊ ግዛት በ1375 እ.ኤ.አ. እና የሶንጋይ ግዛት በ1591 እ.ኤ.አ. ሲዳከሙ ነው። በተጨማሪም ወደ ውስጥ ያለው ሥፍራ ወደ በርሃነት እየተለወጠ ስለመጣ፣ ነዋሪዎቹ ወደ እርጥቡ ፔፐር ጠረፍ (Pepper Coast) እንዲሄዱ ተገደዱ። ከማሊና ሶንጋይ ግዛቶች የመጡ አዳዲስ ነዋሪዎች ጥጥ ማሽከርከር፣ ልብስ መስፋት፣ ብረት ማቅለጥ እና ሩዝና ማሽላ ማብቀልን የመሳሰሉ ጥበቦች ለቦታው አስተዋወቁ።

 
የላይቤሪያ አገሬ ሴቶች በ1910 እ.ኤ.አ.

መኔ ሰዎች (ከመንዴ ወታደሮች የመጡ) አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ ቫይ የሚባል የማሊ ግዛት ከፈረሰ በኋላ ለመሰደድ የተገደደ ብሔር ወደ ግራንድ ኬፕ ማውንት (Grand Cape Mount) የሚባለው ሥፍራ ፈለሱ። የክሩ ብሔር የቫይን ፍልሰት ተቃወሙ። ከመኔ ብሔር ጋር አንድ ላይ በመሆንም የቫይ ብሔርን ከግራንድ ኬፕ ማውንት አልፈው እንዳይስፋፉ አገዱ።

በጠረፍ ላይ የሚኖሩት ሰዎች ታንኳ ሰርተው ከካፕ-ቨርት እስከ የወርቅ ጠረፍ (Gold Coast) ድረስ ካሉት ሌሎች ምዕራብ አፍሪካውያን ጋር ይገበያዩ ነበር። የክሩ ጎሳ በመጀመሪያ ለአውሮፓውያን ሰው ያልሆኑ ነገሮችን ይሸጡ ነበር። ግን በኋላ በየአፍሪካ ባሪያ ንግድ ውስጥ መሳተፍ ጀመሩ።

የክሩ ሠራተኞች ቦታቸውን ትተው በትልቅ እርሻዎችና የግንባታ ሥራዎች ላይ ተሳትፈዋል። አንዳንዶቹም የስዊዝና ፓናማ መስኖዎች ለመገንባት ረድተዋል።

ሌላ ግሌቦ የሚባሉ ሰዎች የመኔ ጎሳ አካባቢያቸውን ሲወር፣ በኋላ የላይቤሪያ ወደ ሚሆነው ጠረፍ አመሩ።

የቀድሞ የአውሮፓውያን ግንኙነት ለማስተካከል

በ1461 እ.ኤ.አ. እና 17ኛው ክፍለ-ዘመን መጨረሻ መካከል ፖርቱጋላዊ፣ ሆላንዳዊና ብራታንያዊ ነጋዴዎች በላይቤሪያ የንግድ ቦታ አቋቁመው ነበር። በተጨማሪም የአንድ የሚጥሚጣ አይነት ፍሬ በመብዛቱ ፖርቱጋላዊያን አካባቢውን Costa da Pimenta (ኮስታ ዳ ፒሜንታ) ማለትም የፍሬ ጠረፍ ብለው ሰይመውት ነበር።

ከአሜሪካ የመጡ ሰፋሪዎች ለማስተካከል

በ1822 እ.ኤ.አ. የአሜሪካ የቅኝ መግዛት ማህበር ላይቤሪያን ባሪያ የነበሩ ጥቁር ሰዎች የሚላኩበት ቦታ አድርጎ አቋቋመ። ከሌሎች ባሪያ ያልነበሩ ጥቁር አሜሪካውያንም ወደ ላይቤሪያ ለመሄድ የመረጡ ነበሩ። ወደ እዛ የሄዱት አሜሪካዊ ላቤሪያዊያን በመባል ይታወቃሉ። በሐምሌ 20 ቀን 1839 ዓ.ም. እነዚህ ሰፋሪዎች የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ነፃነትን አወጁ።

የአመራር ክፍሎች ለማስተካከል

 
የላይቤሪያ የአመራር ክፍሎች
ቁጥር የአገዛዝ ክፍል የሕዝብ ብዛት (2008 እ.ኤ.አ.)[1] ስፋት (ካሬ ኪ.ሜ.)[1] የተፈጠረው (እ.ኤ.አ.)
1 ቦሚ 82,036 1942
2 ቦንግ 328,919 8772 1964
3 ግባርፖሉ 83,758 9689 2001
4 ግራንድ ባሳ 224,839 7936
5 ግራንድ ኬፕ ማውንት 129,055 5162
6 ግራንድ ጌዴህ 126,146 10484 1964
7 ግራንድ ክሩ 57,106 3895 1984
8 ሎፋ 270,114 9982 1964
9 ማርጊቢ 199,689 2616
10 ሜሪላንድ 136,404 2297 1857
11 ሞንትሴራዶ 1,144,806 1909 1847
12 ኒምባ 468,088 11551 1964
13 ሪቨር ሴስ 65,862 5594
14 ሪቨር ጂ 67,318 5113 2000
15 ሲኑ 104,932 10137 1847

ሀይማኖት ለማስተካከል

አርባ ከመቶ የሚሆነው የሀገሩ ሕዝብ ክርስቲያን ነው። ሌላ ሀያ ከመቶ የሚሆን ሕዝብ የራሱ የአገሬው ሀይማኖት አለው። የቀረው አርባ ከመቶ ሕዝብ የእስልምና እምነት ተከታይ ነው።

ትምህርት ለማስተካከል

 
ተማሪዎች በሻማ ብርሃን ሲያጠኑ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል፣ ላይቤሪያ

ላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲሞንሮቪያ ይገኛል። በ1862 እ.ኤ.አ. የተከፈተ ሲሆን ከአፍሪካ ቀደምት የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አንዱ ነው። በእርስ-በርስ ጦርነት ጊዜ በጣም የተጎዳ ሲሆን አሁን እንደገና እየተገነባ ነው።

ከቲንግተን ዩኒቨርሲቲየአሜሪካ ኢጲስ ቆጶስ ቤተክርስቲያን በ1889 እ.ኤ.አ. ተመሥርቷል። ግቢው በሱዋኮኮ፣ ቦንግ የአገዛዝ ክፍል ይገኛል።

ነጥቦች ለማስተካከል

  1. ^ "2008 National Population and Housing Census: Preliminary Results" (በእንግሊዝኛ). Government of the Republic of Liberia (2008). Archived from the original on 2012-02-13. በ2008-10-14 የተወሰደ.
 
በ"Wikimedia Commons"
(የጋራ ፎቶዎች ምንጭ)
ስለ ላይቤሪያ የሚገኛኙ
ተጨማሪ ፋይሎች አሉ።