ጤልክሲዮን (ግሪክ፦ Θελξίων) በሲክዮን ነገሥታት ዝርዝር የአርጊያሌያ (በኋላ ሲክዮን) ንጉሥ ነበር። ካስቶርን የጠቀሱት ጸሐፊዎች 52 ዓመት እንደ ነገሠ ይላሉ። ይህ ምናልባት 2243-2191 ዓክልበ. ግድም ያህል ነው። በዝርዝሩ ላይ ከአፒስ ቀጥሎና ከአይጊሮስ በፊት ይገኛል። ፓውሳኒዩስም የአፒስ ልጅና የአይጊሮስ አባት ይለዋል። በአርጎስ ነገሥታት ዝርዝር የአፒስ ዘመን ከዚህ በኋላ ስለሚታይ የጤልክኪዮን ቀዳሚ አፒስ ሳይሆን ቴልቂን ይመስላል።

ቢብሊዮጤኬ የተባለው መጽሐፍ (ከ150 ዓክልበ. በኋላ፣ በአፖሎዶሮስ ተጽፎ እንደተባለ) በፍጹም ሌላ ቅድም-ተከተል ያቀርባል። በዚህ ትውፊት ዘንድ መጀመርያው ንጉሥ አይጊያሌዎስ ያለ ልጅ ሞቶ ወንድሙ ፎሮኔዎስ አገሩን ያዘ፣ ከዚያ የፎሮኔዎስ ልጅ አፒስ አምባገነን ሆኖ አገሩን ስለ ራሱ ስም አፒያ አለው። ሆኖም ቴልቂንና ጤልክሲዮን አብረው አፒስን ገደሉት። ከዚያ በኋላ ከጊጋንቴስ ወገን (ታላላቅ ሰዎች) አርጎስ ፓኖፕቴስ ቂሙን በቅሎ ቴልቂንንና ጤልክሲዮንን ገደላቸው። በዚሁ ጽሑፍ ውስጥ አፒስን የገደለው ጤልክሲዮን የአፒስ ልጅ ስለማይባል፣ አንዳንድ ምሁር 2 ልዩ ልዩ ጤልክሲዮኖች እንደ ኖሩ ገምተዋል።

ቀዳሚው
ቴልቂን
የአይጊያሌያ (ሲክዮን) ንጉሥ
2243-2191 ዓክልበ. ግድም (አፈ ታሪክ)
ተከታይ
አይጊሮስ