ዓፄ ገላውዴዎስጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፭፻፴፫ ዓ/ም እስከ መጋቢት ፳፯ ቀን ፲፭፻፶፩ ዓ/ም ድረስ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ግዛታቸው በኢትዮጵያና አዳል ጦርነት ጊዜ ነበር። ዓፄ ገላውዴዎስ የስቅለተ ዓርብ ዕለት በአዋሽ አካባቢ ከአዳሉ አሚር ኑር ጋር በተደረገው ጦርነት ላይ ተወግተው ሞቱ። በዚሁ ጦርነት ላይ የደብረ ሊባኖስ እጨጌ ዮሐንስም ሕይወታቸውን አጥተዋል። የታሪኩ ምሑር ሪቻርድ ፓንክኸርስት፣ አሚር ኑር የንጉሠ ነገሥቱን ጭንቅላት ወደይፋቱ ሡልጣን ሳዳዲን እንደላከው ለመረጃ የሐረርን ዜና መዋዕል ይጠቅሳሉ።

ዓፄ ገላውዴዎስ
ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ
ግዛት ጥቅምት ፳፯ ቀን ፲፭፻፴፫ ዓ/ም እስከ መጋቢት ፳፯ ቀን ፲፭፻፶፩ ዓ/ም
ተከታይ ዓፄ ሚናስ (አድማስ ሰገድ)
ሙሉ ስም ቀዳማዊ አፅናፍ ሰገድ (የዙፋን ስም)
ሥርወ-መንግሥት ሰሎሞን
አባት ዓፄ ልብነ ድንግል
እናት ሰብለ ወንጌል
የሞቱት መጋቢት ፳፯ ቀን ፲፭፻፶፩ ዓ/ም
ሀይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል

  • መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፣ ዕለታዊ የታሪክ ድርጊት - የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያው ፓትረያርክ (፲፱፻፶፩ ዓ/ም)
  • (እንግሊዝኛ)Richard K. P. Pankhurst. The Ethiopian Royal Chronicles. Addis Ababa: Oxford University Press, 1967.