ዮሐንስ ፬ኛ
ዓፄ ዮሐንስ ፬ኛ፣ ከአባታቸው ከተንቤን ባላባት የራስ ስኹል ሚካኤል የልጅ ልጅ ሹም ተንቤን ምርጫ እና ከናታቸው የእንደርታው ገዢ የራስ አርአያ እህት ወይዘሮ ወለተ ሥላሴ ሐምሌ ፭ ቀን ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. ማይ በሀ በሚባል ሥፍራ ተወለዱ።
ዓፄ ዮሐንስ ፬ኛ | |
---|---|
![]() | |
ዓፄ ዮሐንስ ፬ኛ ከልጃቸው ከራስ አርአያ ሥላሴ ጋር | |
ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ | |
ግዛት | ከጥር ፲፫ ቀን ፲፰፻፷፬ ዓ.ም. እስከ መጋቢት ፪ ቀን ፲፰፻፹፩ ዓ.ም. |
በዓለ ንግሥ | ጥር ፲፫ ቀን ፲፰፻፷፬ ዓ.ም. |
ቀዳሚ | ዳግማዊ ዓፄ ተክለ ጊዮርጊስ |
ተከታይ | ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ |
ልጆች | ራስ አርአያ ሥላሴ ራስ መንገሻ |
ሙሉ ስም | አባ በዝብዝ (የግብር ስም) |
ሥርወ-መንግሥት | ሰሎሞን፣ የትግራይ ቅርንጫፍ |
አባት | ደጃዝማች መርጫ |
እናት | ወ/ሮ ሥላስ |
የተወለዱት | ሐምሌ ፭ ፲፰፻፳፱ ዓ.ም. በተንቤን፤ ትግራይ |
የሞቱት | መጋቢት ፪ ቀን ፲፰፻፹፩ ዓ.ም. |
ሀይማኖት | የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና |
ርዕሰ መኳንንት ደጃዝማች በዝብዝ ካሳ ሐምሌ ፮ ቀን ፲፰፻፷፫ ዓ/ም ዓፄ ተክለ ጊዮርጊስን አድዋ አካባቢ አሳም የሚባል ሥፍራ ላይ ወግተው ድል ካደረጉ በኋላ ጥር ፲፫ ቀን፲፰፻፷፬ ዓ/ም አክሱም ላይ ሥርዓተ ንግሣቸው ተፈጽሞ ዓፄ ዮሐንስ ፬ኛ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብለው ነገሡ።
-
አጼ ዮሐንስ 1877
-
አጼ ዮሃንስ
አፄ ዮሐንስ 4ኛ ከእንግሊዝ ንግስት ጋር በመፃፃፍ ነግስናቸውን አጠናክረዋል፡፡ ይህም ተቀናቃኛቸው የነበሩት አፄ ሚኒለክን ለማስገበር ተሳክቶላቸዋል ፡፡ ከአፃ ሚኒሊክ ጋር የነበራቸውን የስልጣን ሽሚያ ለመከላከል ሲባል ደብረ ብርሃን ድረስ በመሄድ ድርድር በማድረግ የነበራቸውን ባላንጣነት አስወግደው ሚኒሊክ ንጉስ እንድባልና አፄ የሐንስ ርዕሰ ብሔር እንድሆን ተስማምተዋል ፡፡ ከዛም ደርቡሾች ጋር መተማ አካባቢ ገጥመው አፄ ዮሐንስ በጥይት ቆስለው በመውደቃቸው መሐድስቶች አንገታቸዉን ቆርጠው ለግብፅ ማስፈራሪያእንዳደረጉት ይነገራል፡፡ ይህ የሆነው አፄ ዮሐንስ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ በመሆናቸው የደሴና ቦሩ ሜዳ አካባቢዎች ሙስሊሞችን በሀይል ወደ ክርስትና በማቀየራቸው ነው ፡፡ መሐድስቶችም ከዮሐንስ ጋር ጦርነት የገጠሙት ሙስሊሞችን ለመርዳት እንደሆነ በታሪክ ይነገራል ከዚህ በፊት ግን ከግብፅፆች ጋር ጉራና ጉንዳ ጉንድ በተባሉ ቦታዎች ገጥመው ማሸነፋቸውና የሀገርን ዳር ድንበር ለማስጠበቅ መጣጣራቸን በታሪክ ይወሳል፡፡
ዋቢ ምንጮች ለማስተካከል
- (እንግሊዝኛ) Zewde, Bahru, "A History of Modern Ethiopia 1855-1991, AA University Press (2001)
- መሪ ራስ አማን በላይ "የጥንቷ የኢትዮጵያ ትንሣኤ ታሪክ" (1985 ዓ/ም)
አፄ ዮሃንስ 4 በወሎ አካባቢ በነበሩ ሙስሊሞች ላይ ብቻ ነው ወይስ በሁሉም ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ላይ አደጋ አድርሰዋል? የአደጋው መጠንና ሁኔታ ቢብራራ ጥሩ ነው፡፡
8