1ኛ. ሀይደር ይባላል የአልከሶ አከባቢ ተወለጅ ነው። በአሁኑ ሰዓት በወራቤ ከተማ በሐጂ ፈድሉ ህንጻ ስር አንድ ክፍል ተከራይቶ የመድሐኒት መሸጫ መደብር ከፍቶ ይሸጣል(የገንዘብ ምንጩ ባይታወቅም)፤ይህ ግለሰብ ለረጅም ጊዜ በአልከሶ ሀድራ ውስጥ ሲካድም እንደነበረና ሙሉ ጊዜውን ጫት ሲቅም (ሲፈጭ ቢባል ይሻላል ላሉ በቅርበት የሚያውቁት) የኖረ ገሪባ ነገር እንደነበር በቅርበት የሚያውቁት ይናገራሉ ፤ በዚሁ አጋጣሚ ነበር በጴንጤዎች መረብ ተጠልፎ ገብቶ በሂደት ሱሱን አስትተው የኢኮኖሚ አቅሙን አሻሽለው ወደ ወራቤ መልሰውት በአሁኑ ሰዓት የአክፍሮት ስራውን በጥንቃቄ እየሰራ ይገኛል፡፡ እሱ መድኃኒት ለመግዛት የሚመጡ የገጠር ሰዎችን በተለይም መድኃኒት የመግዛት አቅም የሌላቸውን እንደሚያጠምድ ይነገራል፡፡

2ኛ. ሁሴን ቃዲ ይባላል፤ ወጣት ነው። በወራቤ መሰናዶ ትምህርት ቤት በመምህርነት እየሰራ ይገኛል። ይህ ግለሰብ አስተዳደጉ ወላጅ አጥ የሆኑ ህጻናት በሚያድግበት የህጻናት አምባ እንደሆነ ይገራል። ከሙስሊም ቤተሰብ ቢወለድም ምንም ዓይነት ኢስላማዊ መሰረት እንዳልነበረው ቢያንስ ይህ አስተዳደጉ አብነት ይሆናል። ይህ ወጣት ወንጌላዊ ከመሰል ከሌላ አከባቢ ከመጡ ወጣት ፕሮቴስታንቶች ጋር በመሆን ሴቶችን እየጋበዙ እንደሚያጠምዱ ይነገራል፡፡

3ኛ. ኪያር ይባላል የአልከሶ አከባቢ ተወላጅ እንደሆነ (አልከሶዎች ምን ነካቸው?) እና አስተዳደጉ ዝዋይ እንደሆነ ይነገራል። ከግንበኝት ተነስቶ በአጭር ጊዜ እንዴት ኮንትራከተር እንደሆነ እና የመኪና ባለቤት እንደሆነ አላህ ይወቀው ብቻ በአሁኑ ሰዓት በዞኑ ውስጥ በርካታ የግንባታ ጨረታዎችን ‹እያሸነፈ› ጴንጤ ባለሙያዎችን እያስመጣ ከእኛ የቀን ሰራተኛ ሴቶች ጋር እየቀላቀለ እያሰራ እንደሆነ የይዓን ምስክሮች ያናገራሉ። በአሁኑ ሰዓት በበተለይ በወራቤ በሚካሄዱ ግንባታዎች ላይ ከባለሙያ እስከ የቀን ሰራተኛ ሆነው የሚሰሩ ጴንጤዎችን ታያቸዋለህ አንድ እንኩዋን ቢሆን መዝሙሩን እያስጮሀ ነው የሚሰራው፣የእኛዎቹ ደግሞ የትግርኛ ወይም የስልጠኛ ዘፈን ከፍተው ሲያዳምጡ ታያቸዋለህ፡፡ (ሴኩላሪዝ በጣም ስለገባን ነው መሰለኝ)

4ኛ. ገነት ተክሌ ትባላለች ስልጤ ባትሆንም አባቷ ተክሌ ለረጅም ጊዜ በወራቤ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር እና የምርጫ(ቅርጫ) ቦርድ ሆኖ እያገለገለ ነው። ልጅትም እዚሁ ስለተወለደች ስልኛንም ስልጤንም በደንብ ታውቃቸዋለች፡፡ የማትሪክ ውጤቷ ከፍተኛ ትምህር ተቋም ባያስገባትም በአሁኑ ሰዓት ግን በሚሽነሪዎች(ምናልባትም በቤንጃሚን) አማካኝነት እስከ ውጭ ሀገር ተልካ ዲግሪ፣ሁለተኛ ዲግሪ እስከ ዶክትሬት ሊያስምሯት እንደሆነ ሰምተናል። ይህ ምን ችግር አለው ትሉኝ ይሆናል የእኛ ልጆች በባትሪ እየተፈለጉ በአክራሪነት እተፈረጁ ዞኑን ብሎም ሀገር ለቀው እንዲወጡ እየተደረገ ነገ ደግሞ ይህን ከፈተኛውን የዞን ሹመት መያዝ ያለባቸው ከፍተኛ የትምህርት ዝግጅት ያላቸው ብቻ ናቸው የሚል ህግ ቢያመጡ ማን ይሆን በቦታው የሚቀመጠው? አትጠራጠሩ ገነት ተክሌ ናት፡፡ ከዚያስ?ከዚያማ…..የእኛ በምንለው ሰማን ሽፋ እንኳን ካደረሰብን የሞራል ውድቀት፣ ፍራቻ፣ ውርደት እስካሁን ማንሰራራት አልቻልንም። መስጂድ ውስጥ እንኩዋን ኖርማል ዳዕዋ ማድረግ እየፈራን ያለንበት ሁኔታ ላይ ደርሰናል። አላህ ይድረስልን፡፡ ይህች ገነት በአሁኑ ሰዓት(የገንዘቡ ምንጭ ባይታወቅም) ወራቤ ከተማ ላይ በርካታ መሬቶችን በሊዝ አሸንፋለች መቼም ለምን ይሆን ብሎ የሚጠይቅ ካለ እርግጠኛ ሁኑ ለቸርች አገልግሎት ነው የሚሆነው፡፡

በአሁኑ ሰዓት ጴንጤዎች ለሚበትኑት በራሪ ወረቀት እንኳን መልስ ወረቀት መበተን አልቻልንም፡፡ አንዱ ወንድሜ ወራቤ ገበያ ላይ አጋጠመኝ ብሎ የነገረኝ ደግሞ ምን መሰላቹ? የገጠር ሴቶች ናቸው ሲገበያዩ ‹‹ቢሳ ሱም›› ሲሉ ሰምቼ በጣም ደነገጥኩኝ አለኝ። እዚህም ተደርሷል፡፡ ስለዚህ…..

ስለዚህማ ስልጤ 100 ሙስሊም ነው የሚለውን ያረጀ ተረታችንን ትተን ቢያንስ ቢያንስ ለቤተሰባችን ስንል እንንቀሳቀስ፣ እንደራጅ፤ ተቸገሩትን እንርዳ፤ ጧሪ ያጡ በርካታ አረጋዊያን አሉ ፤በርካታ አይታሞች(ወላጅ አጥ ህጻናት) አሉ፤ ቤታቸው የሚላስ የሚቀመስ የሌላቸው በርካታ ሚስኪኖች አሉ፤ አይደለም ስለመንሃጅ አርካኑል ኢስላም አርካኑል ኢማንን የማያውቁ ፤ስለጠሃራ፣ ስለሂጃብ፣ የማያውቁ በርካታ ወገናችን አለ። እነ እንትና መስጂድ እነ እንትና መስጂድ ከሚለው ዝቅታ ከፍ ብለን ስለ ህዝባች እንኑር። እኛ መስጂድ ውስጥ መስጂድ ከገባው ወንድማችን ጋር በመንሃጅ ጉዳይ ለመጋደል እንፈላለጋለን እነሱ(ጰንጤዎች ) ደግሞ የመስጂዱን አቅጣጫ የማያውቀውን ሙስሊም ነኝ እያለ ብቻ የሚኖረውን እየነጠቀን ነው። እንንቃ እርስ በርስ ከመተቻቸት በዘለለ እኔ ለህዝቤ ምን ሰራሁ እንበል እና ራሳችንን እንጠይቅ። አበቃሁ እኔንም እናንተንም የስራ ሰዎች ያድረገን። ቸር ያሰማን