HISTORY /ታሪክ ስያሜ


ሀገሬው አባይ ብሎ ይጠራዋል፣ አባይ(Abay) ማለት ታላቅ ማለት ነው። ከወንዞች ሁሉ አብይ ነው። የበኩር ልጅን አባይነህ ይሉታል ታላቅ ነህ ማለታቸው ነው። አባይ ከወንዞች ሁሉ ታላቁ ነው። የቀዬው ሰው አባይ ብሎ በአክብሮት ይጥራው እንጂ፣ ስሙ ግዮን ነው። ግዮን በመፅሐፍ ቅዱስ በዘፍጥረት ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 10 እና 13 ላይ ከኤደን ገነት ከሚወጡት አራት ወንዞች አንዱ ሆኖ ተፅፏል። ይህ ወንዝ የኢትዮጵያን ምድር ይከብባል ሲልም ይናገራል።

ghion meaning

ግዮን (Ghion)

ግዮን የሚለው ቃል የግዕዝ ሲሆን በዕብራይስጥ ጊሖን፣በፅርዕ (ግብፅ) ጌዖን ይባላል። ትርጓሜውም “ ዘየሐውር፡ በኃይል፡ ወይርም በድምፀ ማዩ ዐቢይ ወግሩም ማለት ነው።” ወደ አማርኛ ሲገለበጥ “ የውሃውን ብዛት፣ የመልካውን(የወንዙን) ስፋት፣ያካሄዱን ኅይል፣የጩኸቱን ግርማ፣ፏፏቴውንና ተመማውን(አፈሳሰሱ)፣ድምፁ እንደ ነጎድጓድ መሆኑን ያሳያል።”

አባይ ወንዝ ኒል ይባላል(ምናልባት ናይል የሚለውን ከዚህ ወስደው ይሆናል) በግዕዝ ሰማያዊ አይነት፣ወይንም ኑግ ቀለም ኒል ይባላል።


nil meaningተሰማ ኃብተ ሚካኤል ግፀው፣ ከሣቴ ብርሀን በተባለ በ1947 ዓ.ም. በአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት በታተመ መዝገበ ቃላታቸው በገፅ 685 ላይ “ ኒል (NIL) ሰማያዊ ቀለምን መስሎ ከጎጃም ምድር መንጭቶ፣ ጎጃምን አካቦ ወርዶ ሱዳንንም አቋርጦ አራት ሺህ ማይል ዐልፎ፣ ከሜዲትራኒያን ባሕር የሚቀላቀል ኒል፣ ዐባይ” ሲሉ ፅፈዋል። ምንም እንኳን ነጮቹ ናይል የሚለው ስም Neilos ከሚለው ከግሪክ ቃል መጣ ቢሉም፣ ኒል፣ blue ከሚለው ጋር ይስማማልና ዐባይ፣ ግዮን፣ ኒል፣ እኛ ያወጣንለት ስም መሆኑን እንመሰክራለን።


የዓባይ(Abay) ሸለቆ የትውልድ ሐረግ ይህ ነው።

Blue-Nile-River-Ethiopia

Eonile፣ Palenileን ወለደ፣ Palenile፣ Prinileን ወለደ፤ Prinileም የአባይን እናት፣ ታላቁን የአባይ ገደላማ ሸለቆን Neonileን ወለደ።

ባለፉት 6 ሚሊዮን ዓመታት በተለያዩ የመሬት ነውጦች ምክንያት የአባይ ሸለቆ ብዙ ጊዜ ተቀያይሯል። Eonile የተፈጠረው ከ5.4 ሚሊዮን ዓመት ገደማ የሜዲትራኒያን ባሕር ተኖ ኃይለኛ ዝናብ በመከሰቱ ምክንያት በወረደው ዝናብ ነው።

ወደ ሕንድ ውቅያኖስ ይፈስ የነበረው አባይንኳ ከ 5 ሚሊዮን ዓመታት በፊት በተከሰተ የመሬት መናድ ምክንያት አቅጣጫውን ቀይሮ ወደሰሜን መፍሰስ ጀምሯል።የጣና ሐይቅን የፈጠረው እሳተ ገሞራም የዛሬ 2.6 ሚሊዮን ዓመት የተከሰተ ነበር።

Palenile ከ1.8 ሚሊዮን ዓመት በፊት የነበረ ሲሆን ከሰሜን ተራሮች ዝቃጮችን እየጠራረገ ታላቁን ገደል ለአባይ ያሰናዳበት ወቅት ነው።

Prinile የአባይ አያት ሲሆን ከ400 000 ዓመታት በፊት ነበረ። Neonile፣ የዛሬ 12 500 ዓመት ገደማ Prinileን ተከትሎ የመጣ የአባይ እናት እንደማለት ነው።

ከዚህም በኋላ የበረዶ ዘመን ሲጠናቀቅ ለ 6000 ዓመታት የቆየ የዝናብ ዘመን ተከስቶ ነበር።በዚህ ዘመን የነበረው ዶፍ ዝናብ፣ በኢትዮጵያ ከፍታማ ስፍራዎች ቁልቁል መሬቱን እየሸረሸረ አፈሩን እያጠበ፣ኮረቱን እየጠራረገ፣ ቋጥኞችን እየቦረቦረ፣በዘመናት ብዛት የአባይን ወንዝ ከታላቁ የአባይ ሸለቆ ጋር የሚያገናኝ ሸለቆን ፈጠረ።


የአባይ ውኃስ ከየት መጣ?

Semien_Mountains_01

ከሕንድ ውቅያኖስ የሚነሳው እርጥበታማ አየር በኢትዮጵያ ተራራማ ክፍል ሲያልፍ የሙቀትgishen መጠኑ እየቀዘቀዘ ይመጣል። ጉም ምድርን እንደሚያጠጣ፣ ያም ከሕንድ ውቅያኖስ የነፈሰው እርጥበት አዘል አየር፣ ሳይዘንብ የግሸንን ተራራን ያጠጣል።




       ከግሸ ተራራ ስር፣  ከሰቀላ ወረዳ የፈለቀው ምንጭ በግሸን ሜዳ ላይ ግልገል
አባይን ሆኖ ይፈሳል። ግልገል አባይ,  በግሸ ሜዳ ላይ ሮጦ ከጣና ሐይቅ ሲስርግ በጣና ተውጦ አይቀርም። በጣና ላይ ተንሳፎ፣ ወደ አባይ ሸጥ ይንደረደራል።



አባይ (Abay) ከጣና ወጥቶ አርባ ኪሎ ሜትር ከተጓዘ በኋላ የአባይ ፏፏቴጋ ሲደርስ 37 ሜትር ቁልቁል Blue-Nile-River-Ethiopiatisisatቋጥኝ ላይ ይፈጠፈጥና ሽቅብ አየሩ ላይ ተበትኖ ዳግም ቁልቁል ይወርድና ጥልቀቱ 1200 ሜትር፣ ስፋቱ 24ኪ.ሜ ወደሆነው የአባይ ሸለቆ ውስጥ ይገባና በታላቁ የአባይ ገደላማ ሸለቆ፣ በእናቱ በኢትዮጵያ ሆድ ውስጥ 800 ኪሎ ሜትር ይጓዛል። ይህ ዑደት ላለፉት 5000 ዓመታት አልተለወጠም።

የአባይ መነሾን ፍለጋ

በ460 ታሪክ ፀሐፊው ሔረዶቱስ አባይ ከሁለት ትላልቅ ተራሮች እንደሚፈልቅ ያምን ነበር። በኋላም ንጉሠ ነገሥት ኔሮ፣ አሽከሮቹ የአባይን ወንዝ እንዲከተሉ ትዕዛዝ ሰጥቷቸው መልዕክተኞቹ የሱዳን ከተማ የሆነችው ሲናር ሲቲ ከሚገኘው የሱድ ማጥ ደርሰው አባይ ከዛ ነው የሚመነጨው የሚል መልስ ይዘው ተመለሱ። ከአራተኛው እስከ አሥራ ሰባተኛው ክፍለ-ዘመን ድረስ የኢትዮጵያ ተራሮች የአባይ መፍልቂያ መሆናቸውን የገመተ የውጭ ዜጋ አልነበረም።

padez perezበ17ኛው ክፍለ ዘመን ፖርቱጋል ክርስትናን ለመታደግ ሚሲዮናውያንንና ወታደሮችን ወደ ኢትዮጵያ በላከችበት ወቅት ለመጀመሪያ ጊዜ ፓድሬ ፔሬዝ የተባለ ሚሲዮናዊ፣ ጢስ እሳትንና የላይኛውን አባይን ለማየቱ ምስክርነቱን ሰጠ።

James_Bruce

በ18ኛው ክፍለ ዘመን ጄምስ ብሩስ የተባለ የስኮትላንድ ተወላጅ ከካይሮ እስከ ጣና ተጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአባይ መነሾ ጣና ሐይቅ ነው በማለት አወጀ።እስከዚያ ጊዜ ድረስ ማንም የውጭ ዜጋ አባይ (Abay) ከጣና እንደሚነሳ አያውቅም ነበር።

samuel bakerሳሙኤል ቤከር(1821-1893) ሪቻርድ በርተን(1821-1890)ጆን ሀኒንግ ስፔክ (1827-1864) የአባይን መነሻ ፈልገው ወደ ታንጋኒካ ሐይቅ አመሩ እንጂ አንዳቸውም ወደ ኢትዮጵያ አልመጡም።

በ1937 ቡክሀርት ባልደክኼር፣የተባለ የጀርመን ተወላጅ፣ የአባይን ምንጭ ከኢትዮጵያ ተራሮች ስር ማግኘቱን ለአለም አበሰረ።ታሪካችን በነ ባልድክኬርና በብሩስ ሲፃፍ ስታሮቹ እነሱ ናቸው።የታሪካችን ሞተር የሚንቀሳቀሰው በነሱ ነው።

ቢሆንም በ1937 ጀርመናዊው ቡርክኸርት ወደ ኢትዮጵያ ሳይመጣ ኢትዮጵያዊው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ “መፅሐፈ ሰዋሰው ወግስ፡ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚለው በ1929 ባሳተሙት መፅሐፍ በገፅ 313

313“ ከአፍሪቃ ወንዞች ተለይተው፣ ነጭ ኒል፣ ጥቁር ኒል የሚመስሉ፤ በኦሪትም ግዮንና ኤፌሶን የሚባሉ ነጭ አባይና ጥቁር አባይ ናቸው ይባላል። እሊህም ኹለቱ ወንድማማቾች ወንዞች ከየምንጮቻቸው በኅይል ተነስተው፣ ግርማቸውን ለብሰው፣ተሰልፈው፣በየፊታቸው ያለውን ሐይቅ እንደመርከብ ሠንጥቀው አልፈው ሠራዊታቸውን ከፊትና ከኋላ አስከትለው እንደ ኹለት ንጉሥ ካርቱም ላይ ሲገናኙ ሁለትነታቸው ይቀርና፣ አንድ ወንዝ ብቻ ይሆናሉ፤ ከካርቱም ደግሞ እስካትባራ ወርደው ከተከዜ ጋር ይገጥማሉ።ከዚያ በኋላ ግን የሌላ ወንዝ ውኃ ሳይጨምሩ ባንድነት መላ ምድረ ግብፅን ከላይ እስከታች አጠጥተው አጥግበው አርክተው፣ አልፈው ተርፈው ወደ ሰሜን ጎርፈው ሜዲተራኒ ከሚባለው ከታላቁ ባሕር ይገባሉ።” በማለት መፃፋቸውን ሳንጠቅስ አናልፍም።

በ1995 ዓ.ም ግሼ ሜዳ ላይ ከብቶች የሚጠብቅ 11 ዓመት ያልሞላው የውልሰው የተባለ እረኛ አገኘሁና “የአባይ ምንጭ የት ነው ብዬ ስጠይቀው” መሬት ቸክሎ የተደገፈውን በትር ከመሬቱ ላይ ነቅሎ ወደ ግልገል አባይ እያሳየኝ ከዚህ ነዋ አለኝ። አባባሉ ስንት ፈረንጆች የአባይን ምንጭ አገኘን ብለው የቦረቁበት ግኝት አይመስልም።

“ እንዴት አወቅክ?” ስለው “ከብቶቼን የማጠጣ ከዚሁም አይደል? የከተማ ሰው አላዋቂ ነውሳ!” ብሎ ሸረደደኝ። በሆዴ ፈረንጆቹ የአባይን ምንጭ ከአንተ በፊት አገኘን እንደሚሉ ባወቅክ ስል፣ ውስጤን ያነበበ ይመስል፣ “ለፈረንጅ ሁሉ የአባይን ምንጭ እጃቸውን ጎትተን የምናሳይ እኛም አይዶለን እንዴ?” ብሎ አስደመመኝ። ግልገል አባይ ጣና ገብቶ መውጣቱን ያጠኑት ፈረንጆች ካልነገሩት ይህ እረኛ በምን ያውቃል ብዬ በጥያቄ ላፋጥጠው፤ ግልገል አባይ ጣና ገብቶ አባይን ሆኖ መውጣቱን ማን ነገረህ? ስለው “ጣና” “ጣና ነገረኝ” ሲለኝ ያው የተለመደውን የጎጃምን ዘፈን “ነገረኝ ጣና ነገረኝ፡አባይ” የሚለውን ዘፈን ሊዘፍን መስሎኝ ነበር።

ያ የጎጃም እረኛ “ ማስረጃህ ምንድነው?” ስለው በክረምት አባይ ሲደፈርስ ግልገል አባይ የደፈረሰ ውኃ ይዞ ጣና ይገባና ከጣና ተንሳፎ ሲወጣ ጥርት አርጎ ይታያል።” ብሎ እረኛው ጂኦሎጂስት አስገረመኝ። እዚህጋ ባለቅኔው ሎሬት ፀጋዬ ገ/መድህን


“ … የጎጃም እረኛ የት ሄዶ ነው እነሱ(ፈረንጆቹ) የአባይን ምንጭ የሚያገኙት?…” ማለቱን አንረሳም። የኛ ቀን ሲመጣ ልጆቻችን ታሪካቸውን ሲፅፉ፣ ጀምስ ብሩስን ወስዶ አባይጋ ያደረሰውን እረኛ ስሙን ይነግሩናል። እነሉሲ Eonile፣ Palenile፣ Prinile፣ Neonileን ምን ብለው ይጠሯቸው እንደነበረ የሚነግረኝ ኢትዮጲያዊው ታሪክ ፀሐፊ ሲመጣ እኔም የታሪክ ሀ ሁን እቆጥራለሁ። እስከዚያው በነአላን ሙር ሄድ ቋንቋ Eonile፣ Palenileን ወለደ፣ Palenile፣ Prinileን ወለደ፤ …. እያልን ወንድማችንን በፈረንጂኛ እንጠራለን።

(Abay) http://www.abaynileghion.com/