ማክ ግሬንአየርላንድ ልማዳዊ አፈ ታሪክ ዘንድ ከቱዋጣ ዴ ዳናን ወገን የአየርላንድ ከፍተኛ ንጉሥ ነበር። የዳግዳ ልጅ ከርማይት ልጅ ሲሆን ከወንድሞቹ ማክ ኲልማክ ኬክት ጋር አይርላንድን ለ ፳፱ ዓመታት በጋርዮሽ ገዛ። ዕውነተኛ ስሙ ኬጡር ሲሆን ስሙን ማክ ግሬን ስለ አምላኩ ግሬን (ፀሐይ) ወሰደ።

በ1434 ዓክልበ. ማክ ኲል የአባቱን የከርማይት ቂም በቅሎ ንጉሡን ሉግን ገደለው። ከመቶ ዓመታት በኋላ በ1738 ዓክልበ. ንጉሡ ፍያካ ማክ ደልበህ በተገደለበት ጊዜ ማክ ኲልና ፪ ወንድሞቹ ለ29 ዓመታት በጋርዮሽ እንደ ገዙ ይባላል። የፍያካና የእናቱ ኤማስ ሦስት ሴት ልጆች፣ ባንባፎድላኤሪው የከርማይት ልጆች ሚስቶች ሆኑ፤ እነዚህም የአይርላንድ ደሴት ስያሜዎች ሆኑ። የማክ ግሬንም ሚስት ኤሪው ነበረች።

በጥንታዊ ታሪኮች ዘንድ ሦስቱ ወንድማማች እያንዳንዱ የደሴቱን ሲሶ እንደ ገዛ ቢለንም፣ የአይርላንድ ታሪክ የሚባለው መጽሐፍ ግን እንደሚገልጸው፣ እያንዳንዱ ወንድም በመፈራረቅ ከፈተኛ ንጉሥነቱን ለ፩ ዓመት ይይዝ ነበር።

በመጨረሻ በ1305 ዓክልበ. ግ. ሚሌሲያን የተባለው ወገን አይርላንድን ከእስፓንያ ወርረው ሦስቱን የቱዋጣ ደ ዳናን ነገሥታት በታይልቲን ውግያ አሸንፈው ገደላቸው፤ የሚሌሲያንም መጀመርያ ነገስታት ኤቤር ፊን እና ኤሪሞን ተከተሉዋቸው።

የአይርላንድ ታሪክ እንዳለው ሚሌሳውያን በወረሩበት ዓመት በታራው ማክ ግሬን የነገሠበት ዓመት ስለ ሆነ የንግሥቱ ስም «ኤሪው» የደሴቲቱ ዋና ስያሜ ሆነ፤ «አየርላንድ»ም የሚለው ስያሜ ከዚች ንግሥት ስም እንደ መጣ ይላል።

ቀዳሚው
ፍያካ ማክ ደልበህ
አይርላንድ ጋርዮሽ ከፍተኛ ንጉሥ
1334-1305 ዓክልበ. (አፈታሪክ)
ተከታይ
ኤቤር ፊን እና ኤሪሞን