ኻኻውሬ፣ ፫ ሰኑስረት ግብጽን በመካከለኛ መንግሥት (12ኛው ሥርወ መንግሥት) ከ1888 እስከ 1859 ዓክልበ. ግድም ድረስ የገዛ ፈርዖን ነበረ። የአባቱ 2 ሰኑስረት ተከታይ ነበር።

3 ሰኑስረት
የኻኻውሬ ምስል
የኻኻውሬ ምስል
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1888-1859 ዓክልበ.
ቀዳሚ 2 ሰኑስረት
ተከታይ 3 አመነምሃት
ሥርወ-መንግሥት 12ኛው ሥርወ መንግሥት
አባት 2 ሰኑስረት

በኻይከፐሬ 2 ሰኑስረት ዘመነ መንግሥት በ1898 ዓክልበ. ግድም ልጁን ፫ ሰኑስረት ከእርሱ ጋር በጋርዮሽ ወደ ዙፋኑ እንዳስነሣው ይመስላል። አለዚያ በ1898 ዓክልበ. ግድም ፪ ሰኑስረት ዓርፎ ፫ ሰኑስረት በቀጥታ የተከተለው ይሆናል። ያም ሆነ ይህ የ፫ ሰኑስረት ዘመን መጀመርያ ዓመት የሚቆጠር ከ1898 ዓክልበ. ግድም ይሆናል። በጠቅላላ ፴፱ ዓመታት እንደ ገዛ ይታወቃል።

የ፫ ሰኑስረት የ1883 ዓክልበ. ግድም የኩሽ ጠረፍ ድንጋይ

ማኔጦን ለ፪ ሰኑስረት እና ለተከታዩ ፫ ሰኑስረት ፈንታ ለሁለቱ አንድ ስም ብቻ አለው፤ እሱም ሴሶስትሪስ ሲሆን ለ፵፰ ዓመታት እንደ ገዛ ይለናል። ይሄ ሴሶስትሪስ እስከ እስኩቴስ ድረስ የዘመተ በአፈ ታሪክ (ዲዮዶሮስሄሮዶቶስ) ይባላል። ፫ ሰኑስረት ቢያንስ በከነዓን እንደ ዘመተ ይታወቃል፤ ለ፪ ሰኑስረት ግን ምንም ዘመቻ አይታወቅም። የቶሪኖ ቀኖና የሚባለው የፈርዖኖች ዝርዝር ሰነድ ሁለቱንም ይለያል፤ ለ፪ ሰኑስረት ፲፱ ዓመታትና ለ፫ ሰኑስረት ፴ አመታት ይሠጣል።

በ፰ኛው ዓመት ወይም በ1891 ዓክልበ. በኩሽ መንግሥት ላይ ዘመተ፤ ጠረፉን ከ፪ኛው ፏፏቴ ደቡብ አስፋፍቶ አምባ በሰምና መሠረተ። እንደገና በ1889፣ በ1883 እና በ1880 ዓክልበ. በኩሽ ላይ ዘመተ። በ1880 የሆነው ዘመቻ ግን ከኩሽ መሸሽ ነበረበት። ከ1883 በፊት 3 ሰኑስረት ደግሞ በ«መንቱ» (ምድያም)ና በረጨኑ (ከነዓን) ላይ ዘምቶ፣ በ«ሰክመም» (ሴኬም) እንዳሸነፋቸው የሚል የሰበክ-ሁ ጽላት አለ።

በ፳ኛው አመት ወይም በ1879 ዓክልበ. ልጁን 3 አመነምሃት የጋርዮሽ ፈርዖን አደረገው። ከጠቅላይ ሚንስትሮቹ ሶበከምሃትነቢትኽኑምሆተፕ ይታወቃሉ፤ ባጅሮንዱም ኢኸርኖፍረት ይታወቃል።

ቀዳሚው
2 ሰኑስረት
ግብፅ ፈርዖን
1888 (1898)-1859 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
3 አመነምሃት

የውጭ መያያዣ ለማስተካከል