ዲማምስራቅ ጎጃምእነማይ ወረዳ የሚገኝ ከተማ ነው። ይህ ቦታ በተለይ እውቅና እሚያገኘው የዲማ ጊዮርጊስን ቤተክርስቲያንና መናኞችና ሌሎች የሚጠለሉበት ገዳም በማቀፉ ነው።

ዲማ
ከፍታ 2,076 ሜትር
ዲማ is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
ዲማ

10°0′ ሰሜን ኬክሮስ እና 38°29′ ምሥራቅ ኬንትሮስ

በዓፄ ሱሰንዮስ ዘመን የነበሩትን ዓፄ ያዕቆብን ደግፈው ሲዋጉ በጎል ጦርነት ድል የሆኑት ራስ አትናቴዎስ በዲማ ገዳም እንደተጠለሉ በዚያው ዘመን የተጻፉ ድርሳናት ይገልጻሉ[1]። እንዲሁ ደጃዝማች ጎሹ ዘውዴ ልጃቸው ብሩ ጎሹ ሲያምጽ በዲማ ገዳም እንደተጠለሉ እንግሊዙ ሲ ቲ ቤኬ ዘግቦት ይገኛል።

በ19ኛው ክፍለ ዘመን፣ የዲማ ጊዮርጊስጎጃም ውስጥ ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነበር[2]። ቤተ ክርስቲያኑ በ2 ሜትር ከፍታ የድንጋይ አጥር የታጠረ ሲሆን ውስጡ ብዙ ታሪካዊ መጻሕፍትን አካቶ ይዟል። በ1513 ዓ.ም. በአውሮጳውያን ስልት የተሳሉ የዓፄ ናዖድ እና ዓፄ ልብነ ድንግል ምስሎች በቤተርክስቲያኑ በሚገኙ መጽሐፍት ይታያሉ[3]

ማጣቀሻ ለማስተካከል

  1. ^ James Bruce, Travels to Discover the Source of the Nile (1805 edition), vol. 3, p. 280
  2. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2011-06-12. በ2012-02-09 የተወሰደ.
  3. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2011-06-12. በ2012-02-09 የተወሰደ.