ዮኩ ፈይድሌክ (ወይም ዮቃይድ ፈይድሌክ) በአየርላንድ አፈ ታሪክ ከ11 ዓክልበ. እስከ 1 ዓም ድረስ የአየርላንድ ከፍተኛ ነጉሥ ነበር።

የአይርላንድ ታሪኮች እንዳሉት፣ የዮኩ ፈይድሌክ ዘመን ለ፲፪ ዓመታት ቆየ። የላውድ አቆጣጠሮች (1014 ዓም ተቀነባብሮ) ዘንድ፣ የክርስቶስ ልደት ዓመት አኖ ዶሚኒ (ወይም በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር 8 ዓክልበ.) በዮኩ ፈይድሌክ ዘመን ፫ኛ ዓመት ደረሰ።

በኋላ የታየው መጽሐፍ ሌቦር ጋባላ ኤረን እንደቆጠረው ግን የክርስቶስ ልደት በኤቴርስኬል ዘመን ሆነ። ወይም በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፉት ታሪኮች እንዳሉት ደግሞ፣ ክርስቶስ በክሪምጣን ኒያ ናይር ዘመነ መንግሥት ተወለደ። ፕሮፌሰር ዲ. ፒ. ማካርጢ እንዳስረዳው፣ የላውድ አቆጣጠሮች እና የቲገርናቅ ዜና መዋዕል (1080 ዓም ተቀነባብሮ) ስለሚስማሙ እነዚህ የድሮ መቆጠሪያ በታማኝነት ጠበቁ።[1]

  1. ^ የአይርላንድ ነገስታት ልማዶችን ስለ ማስማማት Archived ሜይ 26, 2014 at the Wayback Machine (እንግሊዝኛ)