የዮሐንስ ወንጌል

ክርስቶስ የሚወደው ከሁሉ ታናሽ ሐዋርያ የጻፈው ወንጌል

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ እንደ ጻፈው። ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ይወደው የነበረው የዘብዴዎስ ልጅ ዮሐንስ በፍልስጤም ከፍልስጤምም ውጪ ክርስትና እንድትስፋፋ ያደረገ ጌታ በመስቀል ላይ ሳለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን እንዲያገለግላት አደራ የተቀበለ የእመቤታችን የአደራ ልጅ ነው (ዮሐ. ፲፱፡፳፮)።

ቅ.ዮሐንስ ወንጌላዊው
የወንጌላዊው ዮሐንስ ምስል ስዕል በጉንዳ ጉንዶ ገዳም ወንጌል ፲፭፴፪ ዓ.ም.
የወንጌላዊው ዮሐንስ ምስል ስዕል በጉንዳ ጉንዶ ገዳም ወንጌል ፲፭፴፪ ዓ.ም.
ክርስቶስ የሚወደው ደቀመዝሙር የሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል
የፀሐፊው ስም ዮሐንስ
የተወለደበት ቀን በ፩ኛው ክፍለ ዘመን በ፲ኛው ዓመት
የተወለደበት ቦታ ቤተሳይዳ
ሥራው ወንጌል ሰባኪ ፀሐፊም
ያረፈበት ቀን ሞትን አልቀመሰም
(ተነጥቋል)
ንግሥ ጥር ፬
መታወቂያው
የሚከበረው በመላው የክርስትና እምነት ተከታይ
የጻፈው ወንጌል ፳፩ ምዕራፍ
በተጨማሪ የፃፋቸው የዮሐንስ ራእይ
ታዐምረ ኢየሱስ


ከዚህም ጋር ቅዱስ ጳውሎስ ዕረፍት በኋላ ኢየሩሳሌም ወደ ኤፌሶን ሄዶ በትንሽዋ እሲያ ወንጌልን የሰበከ በሮማዊው ቄሣር በዶሚቲያኖስ ዘመነ መንግሥት ወደ ፍጥሞ ደሴት ተሰዶ በእስር ቤት ሳለ ራእይ የጻፈ ነው ።

ፍጥሞ ቅዱስ ዮሐንስ በግዞት ሳለ የዮሐንስ ራዕዪ የፃፈባት ደሴት
የዮሐንስ ራእይ
ግሪክና አዋሳኝዋ ቱርክ
ፍጥሞ
ኤፌሶን


ከዶሚቴያኖስም ሞት በኋላ ወደ ኤፌሶን ተመልሶ " ልጆቼ እርስበርሳቹህ ተፋቀሩ " እያለ ያስተማረ በስሙ የሚጠሩትን ወንጌልን እና ሦስቱን መልዕክታት የጻፈ ንባቤ መለኮት የሚል ስያሜ የተሰጠው ሐዋርያ ነው። ወንጌሉም ጌታ ከዐረገ በኋላ በሠላሳ ወይም በሠላሳ አምስት ዓመት ኔሮን ቄሣር በነገሠ በስምንት ዓመት በየናኒ ቋንቋ ጻፈው በልሳነ ጽርዕ የሚልም አብነት አለ። ከአራቱ ወንጌል መጨረሻ ላይ የተጻፈ ነው[1]

ምልክቱ ለማስተካከል

ወንጌላዊው ዮሐንስ በንስር ይመሰላል። በሥነ አንስርት(አሞሮች) የሊቃውንት ጥናት እንደሚነገረው ንስር ከሌሎች አዕዋፍ ሁሉ ተለይቶ ወደላይ መጥቆ ይበራል። በላይም ሆኖ በመሬት ላይ ያሉትን ረቂቃን ነገሮችን አጣርቶ ማየት ይችላል። ወንጌላዊው ዮሐንስም ወንጌልን ሲጽፍ ከወንጌላውያኑ አጻጻፍ በተለየ በሚስጥረ ሥላሴ ይጀምራል ስለሥጋዌም ሲጽፍ ወደላይ መጥቆ በማሰብ ቅድመ ዓለም ስለነበረው ቃል ይተርክና "ያቀድሞ የነበረው ቃል ሥጋ ሆነ" በማለት ይጽፋል (ዮሐ.፩፡፲፬)። ንስር ወደላይ መጥቆ እንደሚበርና ወደ ምድር ሲመለከት ረቂቃን የሆኑትን ነገሮች መመልከት እንደሚችል፡ ዮሐንስም ረቂቅና ጥልቅ የሆነውን ትምህርት ያስተምር ነበር። እነዚህም:

የሚሉትና የመሳሰሉት ናቸው።[2]

ማጣቀሻ ለማስተካከል

መጀመርያ ሦስቱ ወንጌላት (የማቴዎስ ወንጌልየማርቆስ ወንጌልየሉቃስ ወንጌል) ስለተመሳሳይነታችው «ሲኖፕቲክ» («አከከታች») ወንጌላት ሲባሉ፣ የዮሐንስ ወንጌል ስለ ኢየሱስ ሕይወት፣ ስብከትና ትምህርት ከነዚህ የተለየ ነፃ አስተያየት ያለውን ድርሰት ያቀርባል። እንደ ሌሎቹም አሁን መጀመርያ የምናውቀው ቅጂ በግሪክኛ ነው።




የዮሐንስ ወንጌል

ምዕራፍ ፩ ለማስተካከል

1፤በመዠመሪያው፡ቃል፡ነበረ፥ቃልም፡በእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ነበረ፥ቃልም፡እግዚአብሔር፡ነበረ። 2፤ይህ፡በመዠመሪያው፡በእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ነበረ። 3፤ዅሉ፡በርሱ፡ኾነ፥ከኾነውም፡አንዳች፡ስንኳ፡ያለርሱ፡አልኾነም። 4፤በርሱ፡ሕይወት፡ነበረች፥ሕይወትም፡የሰው፡ብርሃን፡ነበረች። 5፤ብርሃንም፡በጨለማ፡ይበራል፥ጨለማም፡አላሸነፈውም። 6፤ከእግዚአብሔር፡የተላከ፡ስሙ፡ዮሐንስ፡የሚባል፡አንድ፡ሰው፡ነበረ፤ 7፤ዅሉ፡በርሱ፡በኩል፡እንዲያምኑ፡ይህ፡ስለ፡ብርሃን፡ይመሰክር፡ዘንድ፡ለምስክር፡መጣ። 8፤ስለ፡ብርሃን፡ሊመሰክር፡መጣ፡እንጂ፥ርሱ፡ብርሃን፡አልነበረም። 9፤ለሰው፡ዅሉ፡የሚያበራው፡እውነተኛው፡ብርሃን፡ወደ፡ዓለም፡ይመጣ፡ነበር። 10፤በዓለም፡ነበረ፥ዓለሙም፡በርሱ፡ኾነ፥ዓለሙም፡አላወቀውም። 11፤የርሱ፡ወደኾነው፡መጣ፥የገዛ፡ወገኖቹም፡አልተቀበሉትም። 12፤ለተቀበሉት፡ዅሉ፡ግን፥በስሙ፡ለሚያምኑት፡ለእነርሱ፡የእግዚአብሔር፡ልጆች፡ይኾኑ፡ዘንድ፡ሥልጣንን፡ ሰጣቸው፤ 13፤እነርሱም፡ከእግዚአብሔር፡ተወለዱ፡እንጂ፡ከደም፡ወይም፡ከሥጋ፡ፈቃድ፡ወይም፡ከወንድ፡ፈቃድ፡ አልተወለዱም። 14፤ቃልም፡ሥጋ፡ኾነ፤ጸጋንና፡እውነትንም፡ተመልቶ፡በእኛ፡ዐደረ፥አንድ፡ልጅም፡ከአባቱ፡ዘንድ፡እንዳለው፡ክብር፡የኾነው፡ክብሩን፡አየን። 15፤ዮሐንስ፡ስለ፡ርሱ፡መሰከረ፡እንዲህም፡ብሎ፡ጮኸ፦ከእኔ፡በዃላ፡የሚመጣው፡ርሱ፡ከእኔ፡በፊት፡ ነበረና፡ከእኔ፡ይልቅ፡የከበረ፡ኾኗል፤ስለ፡ርሱ፡ያልኹት፡ይህ፡ነበረ። 16፤እኛ፡ዅላችን፡ከሙላቱ፡ተቀብለን፡በጸጋ፡ላይ፡ጸጋ፡ተሰጥቶናልና፥ሕግ፡በሙሴ፡ተሰጥቶ፡ነበርና፤ 17፤ጸጋና፡እውነት፡ግን፡በኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ኾነ። 18፤መቼም፡ቢኾን፡እግዚአብሔርን፡ያየው፡አንድ፡ስንኳ፡የለም፤በአባቱ፡ዕቅፍ፡ያለ፡አንድ፡ልጁ፡ርሱ፡ ተረከው። 19፤አይሁድም፦አንተ፡ማን፡ነኽ፧ብለው፡ይጠይቁት፡ዘንድ፡ከኢየሩሳሌም፡ካህናትንና፡ሌዋውያንን፡በላኩበት፡ጊዜ፥የዮሐንስ፡ምስክርነት፡ይህ፡ነው። 20፤መሰከረም፡አልካደምም፤እኔ፡ክርስቶስ፡አይደለኹም፡ብሎ፡መሰከረ። 21፤እንኪያስ፡ማን፡ነኽ፧ኤልያስ፡ነኽን፧ብለው፡ጠየቁት፦አይደለኹም፡አለ፦ነቢዩ፡ነኽን፧አይደለኹም፡ ብሎ፡መለሰ። 22፤እንኪያስ፦ማን፡ነኽ፧ለላኩን፡መልስ፡እንድንሰጥ፤ስለ፡ራስኽ፡ምን፡ትላለኽ፧አሉት። 23፤ርሱም፦ነቢዩ፡ኢሳይያስ፡እንዳለ፦የጌታን፡መንገድ፡አቅኑ፡ብሎ፡በምድረ፡በዳ፡የሚጮኽ፡ሰው፡ ድምፅ፡እኔ፡ነኝ፡አለ። 24-25፤የተላኩትም፡ከፈሪሳውያን፡ነበሩና፦እንኪያስ፡አንተ፡ክርስቶስ፡ወይም፡ኤልያስ፡ወይም፡ነቢዩ፡ ካይደለኽ፥ስለ፡ምን፡ታጠምቃለኽ፧ብለው፡ጠየቁት። 26፤ዮሐንስ፡መልሶ፦እኔ፡በውሃ፡አጠምቃለኹ፤ዳሩ፡ግን፡እናንተ፡የማታውቁት፡በመካከላችኹ፡ቆሟል፤27፤እኔ፡የጫማውን፡ጠፍር፡ልፈታ፡የማይገ፟ባ፟ኝ፥ከእኔ፡በዃላ፡የሚመጣው፡ከእኔ፡ይልቅ፡የሚከብር፡ይህ፡ ነው፡አላቸው። 28፤ይህ፡ነገር፡ዮሐንስ፡ያጠምቅበት፡በነበረው፡በዮርዳኖስ፡ማዶ፡በቢታንያ፡በቤተ፡ራባ፡ኾነ። 29፤በነገው፡ዮሐንስ፡ኢየሱስን፡ወደ፡ርሱ፡ሲመጣ፡አይቶ፡እንዲህ፡አለ፦እንሆ፥የዓለምን፡ኀጢአት፡ የሚያስወግድ፡የእግዚአብሔር፡በግ። 30፤አንድ፡ሰው፡ከእኔ፡በዃላ፡ይመጣል፥ከእኔም፡በፊት፡ነበርና፥ከእኔ፡ይልቅ፡የከበረ፡ኾኗል፡ብዬ፡ስለ፡ ርሱ፡ያልኹት፡ይህ፡ነው። 31፤እኔም፡አላውቀውም፡ነበር፥ዳሩ፡ግን፡ለእስራኤል፡ይገለጥ፡ዘንድ፡ስለዚህ፡በውሃ፡እያጠመቅኹ፡እኔ፡ መጣኹ። 32፤ዮሐንስም፡እንዲህ፡ብሎ፡መሰከረ።መንፈስ፡ከሰማይ፡እንደ፡ርግብ፡ኾኖ፡ሲወርድ፡አየኹ፤በርሱ፡ ላይም፡ኖረ። 33፤እኔም፡አላውቀውም፡ነበር፥ዳሩ፡ግን፡በውሃ፡አጠምቅ፡ዘንድ፡የላከኝ፡ርሱ፦መንፈስ፡ሲወርድበትና፡ሲኖርበት፡የምታየው፥በመንፈስ፡ቅዱስ፡የሚያጠምቅ፡ርሱ፡ነው፡አለኝ። 34፤እኔም፡አይቻለኹ፡ርሱም፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡እንደ፡ኾነ፡መስክሬያለኹ። 35፤በነገው፡ደግሞ፡ዮሐንስ፡ከደቀ፡መዛሙርቱም፡ኹለት፡ቆመው፡ነበር፥ 36፤ኢየሱስም፡ሲኼድ፡ተመልክቶ፦እንሆ፥የእግዚአብሔር፡በግ፡አለ። 37፤ኹለቱም፡ደቀ፡መዛሙርት፡ሲናገር፡ሰምተው፡ኢየሱስን፡ተከተሉት። 38፤ኢየሱስም፡ዘወር፡ብሎ፡ሲከተሉትም፡አይቶ፦ምን፡ትፈልጋላችኹ፧አላቸው። 39፤እነርሱም፦ረቢ፥ወዴት፡ትኖራለኽ፧አሉት፤ትርጓሜው፡መምህር፡ሆይ፡ማለት፡ነው። 40፤መጥታችኹ፡እዩ፡አላቸው።መጥተው፡የሚኖርበትን፡አዩ፥በዚያም፡ቀን፡በርሱ፡ዘንድ፡ዋሉ፤ዐሥር፡ ሰዓት፡ያኽል፡ነበረ። 41፤ከዮሐንስ፡ዘንድ፡ሰምተው፡ከተከተሉት፡ከኹለቱ፡አንዱ፡የስምዖን፡ጴጥሮስ፡ወንድም፡እንድርያስ፡ነበረ። 42፤ርሱ፡አስቀድሞ፡የራሱን፡ወንድም፡ስምዖንን፡አገኘውና፦መሲሕን፡አግኝተናል፡አለው፤ትርጓሜውም፡ክርስቶስ፡ማለት፡ነው። 43፤ወደ፡ኢየሱስም፡አመጣው።ኢየሱስም፡ተመልክቶ፦አንተ፡የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ነኽ፤አንተ፡ኬፋ፡ ትባላለኽ፡አለው፤ትርጓሜው፡ጴጥሮስ፡ማለት፡ነው። 44፤በነገው፡ኢየሱስ፡ወደ፡ገሊላ፡ሊወጣ፡ወደደ፥ፊልጶስንም፡አገኘና፦ተከተለኝ፡አለው። 45፤ፊልጶስም፡ከእንድርያስና፡ከጴጥሮስ፡ከተማ፡ከቤተ፡ሳይዳ፡ነበረ። 46፤ፊልጶስ፡ናትናኤልን፡አግኝቶ፦ሙሴ፡በሕግ፡ነቢያትም፡ስለ፡ርሱ፡የጻፉትን፡የዮሴፍን፡ልጅ፡የናዝሬቱን፡ኢየሱስን፡አግኝተነዋል፡አለው። 47፤ናትናኤልም፦ከናዝሬት፡መልካም፡ነገር፡ሊወጣ፡ይችላልን፧አለው።ፊልጶስ፦መጥተኽ፡እይ፡አለው። 48፤ኢየሱስ፡ናትናኤልን፡ወደ፡ርሱ፡ሲመጣ፡አይቶ፡ስለ፡ርሱ፦ተንኰል፡የሌለበት፡በእውነት፡የእስራኤል፡ ሰው፥እንሆ፥አለ። 49፤ናትናኤልም፦ከወዴት፡ታውቀኛለኽ፧አለው።ኢየሱስም፡መልሶ፦ፊልጶስ፡ሳይጠራኽ፥ከበለስ፡በታች፡ ሳለኽ፥አየኹኽ፡አለው። 50፤ናትናኤልም፡መልሶ፦መምህር፡ሆይ፥አንተ፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ነኽ፤አንተ፡የእስራኤል፡ንጉሥ፡ነኽ፡ አለው። 51፤ኢየሱስም፡መልሶ፦ከበለስ፡በታች፡አየኹኽ፡ስላልኹኽ፡አመንኽን፧ከዚህ፡የሚበልጥ፡ነገር፡ታያለኽ፡ አለው። 52፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥ሰማይ፡ሲከፈት፡የእግዚአብሔርም፡መላእክት፡በሰው፡ልጅ፡ላይ፡ ሲወጡና፡ሲወርዱ፡ታያላችኹ፡አለው።

ምዕራፍ ፪ ለማስተካከል

1 በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤ 2 ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ። 3 የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው። 4 ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት። 5 እናቱም ለአገልጋዮቹ፦ የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው። 6 አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር። 7 ኢየሱስም፦ ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው። 8 አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም። 9 አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ፦ 10 ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው። 11 ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ። 12 ከዚህ በኋላ ከእናቱና ከወንድሞቹ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ወደ ቅፍርናሆም ወረደ፥ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ። 13 የአይሁድ ፋሲካም ቀርቦ ነበር፥ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ። 14 በመቅደስም በሬዎችንና በጎችን ርግቦችንም የሚሸጡትን ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፤ 15 የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፥ 16 ርግብ ሻጪዎችንም፦ ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው። 17 ደቀ መዛሙርቱም፦ የቤትህ ቅናት ይበላኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ አሰቡ። 18 ስለዚህ አይሁድ መልሰው፦ ይህን ስለምታደርግ ምን ምልክት ታሳየናለህ? አሉት። 19 ኢየሱስም መልሶ፦ ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው። 20 ስለዚህ አይሁድ፦ ይህ ቤተመቅደስ ከአርባ ስድስት ዓመት ጀምሮ ይሠራ ነበር፥ አንተስ በሦስት ቀን ታነሣዋለህን? አሉት። 21 እርሱ ግን ስለ ሰውነቱ ቤተ መቅደስ ይል ነበር። 22 ስለዚህ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ይህን እንደ ተናገረ አሰቡና መጽሐፍንና ኢየሱስ የተናገረውን ቃል አመኑ። 23 በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ፥ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ ብዙ ሰዎች በስሙ አመኑ፤ 24-25 ነገር ግን ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ ያውቅ ነበር፤ ስለ ሰውም ማንም ሊመሰክር አያስፈልገውም ነበርና አይተማመናቸውም ነበር፤ ራሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና።

ምዕራፍ ፫ ለማስተካከል

 1፤ከፈሪሳውያንም፡ወገን፡የአይሁድ፡አለቃ፡የኾነ፡ኒቆዲሞስ፡የሚባል፡አንድ፡ሰው፡ነበረ፤ርሱም፡በሌሊት፡ ወደ፡ኢየሱስ፡መጥቶ፦ 2፤መምህር፡ሆይ፥እግዚአብሔር፡ከርሱ፡ጋራ፡ከኾነ፡በቀር፡አንተ፡የምታደርጋቸውን፡እነዚህን፡ምልክቶች፡ ሊያደርግ፡የሚችል፡የለምና፡መምህር፡ኾነኽ፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡እንደ፡መጣኽ፡እናውቃለን፡አለው። 3፤ኢየሱስም፡መልሶ፦እውነት፡እውነት፡እልኻለኹ፥ሰው፡ዳግመኛ፡ካልተወለደ፡በቀር፡የእግዚአብሔርን፡ መንግሥት፡ሊያይ፡አይችልም፡አለው። 4፤ኒቆዲሞስም፦ሰው፡ከሸመገለ፡በዃላ፡እንዴት፡ሊወለድ፡ይችላል፧ኹለተኛ፡ወደ፡እናቱ፡ማሕፀን፡ገብቶ፡ ይወለድ፡ዘንድ፡ይችላልን፧አለው። 5፤ኢየሱስም፡መለሰ፥እንዲህ፡ሲል፦እውነት፡እውነት፡እልኻለኹ፥ሰው፡ከውሃና፡ከመንፈስ፡ካልተወለደ፡ በቀር፡ወደእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ሊገባ፡አይችልም። 6፤ከሥጋ፡የተወለደ፡ሥጋ፡ነው፥ከመንፈስም፡የተወለደ፡መንፈስ፡ነው። 7፤ዳግመኛ፡ልትወለዱ፡ያስፈልጋችዃል፡ስላልኹኽ፡አታድንቅ። 8፤ነፋስ፡ወደሚወደ፟ው፡ይነፍሳል፥ድምፁንም፡ትሰማለኽ፥ነገር፡ግን፥ከወዴት፡እንደ፡መጣ፡ወዴትም፡ እንዲኼድ፡አታውቅም፤ከመንፈስ፡የተወለደ፡ዅሉ፡እንዲሁ፡ነው። 9፤ኒቆዲሞስ፡መልሶ፦ይህ፡እንዴት፡ሊኾን፡ይችላል፧አለው። 10፤ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አለው፦አንተ፡የእስራኤል፡መምህር፡ስትኾን፡ይህን፡አታውቅምን፧ 11፤እውነት፡እውነት፡እልኻለኹ፥የምናውቀውን፡እንናገራለን፡ያየነውንም፡እንመሰክራለን፥ምስክራችንንም፡ አትቀበሉትም። 12፤ስለ፡ምድራዊ፡ነገር፡በነገርዃችኹ፡ጊዜ፡ካላመናችኹ፥ስለ፡ሰማያዊ፡ነገር፡ብነግራችኹ፡እንዴት፡ታምናላችኹ፧ 13፤ከሰማይም፡ከወረደ፡በቀር፡ወደ፡ሰማይ፡የወጣ፡ማንም፡የለም፥ርሱም፡በሰማይ፡የሚኖረው፡የሰው፡ልጅ፡ ነው። 14-15፤ሙሴም፡በምድረ፡በዳ፡እባብን፡እንደ፡ሰቀለ፡እንዲሁ፡በርሱ፡የሚያምን፡ዅሉ፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡ እንዲኖረው፡እንጂ፡እንዳይጠፋ፡የሰው፡ልጅ፡ይሰቀል፡ይገ፟ባ፟ዋል። 16፤በርሱ፡የሚያምን፡ዅሉ፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡እንዲኖረው፡እንጂ፡እንዳይጠፋ፡እግዚአብሔር፡አንድያ፡ ልጁን፡እስኪሰጥ፡ድረስ፡ዓለሙን፡እንዲሁ፡ወዷ፟ልና። 17፤ዓለም፡በልጁ፡እንዲድን፡ነው፡እንጂ፥በዓለም፡እንዲፈርድ፡እግዚአብሔር፡ወደ፡ዓለም፡አልላከውምና። 18፤በርሱ፡በሚያምን፡አይፈረድበትም፤በማያምን፡ግን፡በአንዱ፡በእግዚአብሔር፡ልጅ፡ስም፡ስላላመነ፡አኹን፡ ተፈርዶበታል። 19፤ብርሃንም፡ወደ፡ዓለም፡ስለ፡መጣ፡ሰዎችም፡ሥራቸው፡ክፉ፡ነበርና፥ከብርሃን፡ይልቅ፡ጨለማን፡ስለ፡ ወደዱ፡ፍርዱ፡ይህ፡ነው። 20፤ክፉ፡የሚያደርግ፡ዅሉ፡ብርሃንን፡ይጠላልና፥ሥራውም፡እንዳይገለጥ፡ወደ፡ብርሃን፡አይመጣም፤ 21፤እውነትን፡የሚያደርግ፡ግን፡ሥራው፡በእግዚአብሔር፡ተደርጎ፡እንደ፡ኾነ፡ይገለጥ፡ዘንድ፡ወደ፡ብርሃን፡ ይመጣል። 22፤ከዚህ፡በዃላ፡ኢየሱስ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡ወደይሁዳ፡አገር፡መጣ፥በዚያም፡ከነርሱ፡ጋራ፡ ተቀምጦ፡ያጠምቅ፡ነበር። 23፤ዮሐንስም፡ደግሞ፡በሳሌም፡አቅራቢያ፡በሄኖን፡በዚያ፡ብዙ፡ውሃ፡ነበርና፥ያጠምቅ፡ነበር፥ 24፤እየመጡም፡ይጠመቁ፡ነበር፡ዮሐንስ፡ገና፡ወደ፡ወህኒ፡አልተጨመረም፡ነበርና። 25፤ስለዚህም፡በዮሐንስ፡ደቀ፡መዛሙርትና፡በአይሁድ፡መካከል፡ስለ፡ማንጻት፡ክርክር፡ኾነ። 26፤ወደ፡ዮሐንስም፡መጥተው፦መምህር፡ሆይ፥በዮርዳኖስ፡ማዶ፡ከአንተ፡ጋራ፡የነበረው፡አንተም፡ የመሰከርኽለት፥እንሆ፥ርሱ፡ያጠምቃል፡ዅሉም፡ወደ፡ርሱ፡ይመጣሉ፡አሉት። 27፤ዮሐንስ፡መለሰ፥እንዲህ፡ሲል፦ከሰማይ፡ካልተሰጠው፡ሰው፡አንዳች፡ሊቀበል፡አይችልም። 28፤እናንተ፦እኔ፡ክርስቶስ፡አይደለኹም፥ነገር፡ግን፦ከርሱ፡በፊት፡ተልኬያለኹ፡እንዳልኹ፡ራሳችኹ፡ ትመሰክሩልኛላችኹ። 29፤ሙሽራዪቱ፡ያለችው፡ርሱ፡ሙሽራ፡ነው፤ቆሞ፡የሚሰማው፡ሚዜው፡ግን፡በሙሽራው፡ድምፅ፡እጅግ፡ ደስ፡ይለዋል።እንግዲህ፡ይህ፡ደስታዬ፡ተፈጸመ። 30፤ርሱ፡ሊልቅ፡እኔ፡ግን፡ላንስ፡ያስፈልጋል። 31፤ከላይ፡የሚመጣው፡ከዅሉ፡በላይ፡ነው፤ከምድር፡የሚኾነው፡የምድር፡ነው፥የምድሩንም፡ ይናገራል።ከሰማይ፡የሚመጣው፡ከዅሉ፡በላይ፡ነው። 32፤ያየውንና፡የሰማውንም፡ይህን፡ይመሰክራል፥ምስክሩንም፡የሚቀበለው፡የለም። 33፤ምስክሩን፡የተቀበለ፡እግዚአብሔር፡እውነተኛ፡እንደ፡ኾነ፡አተመ። 34፤እግዚአብሔር፡የላከው፡የእግዚአብሔርን፡ቃል፡ይናገራልና፤እግዚአብሔር፡መንፈሱን፡ሰፍሮ፡አይሰጥምና። 35፤አባት፡ልጁን፡ይወዳል፡ዅሉንም፡በእጁ፡ሰጥቶታል። 36፤በልጁ፡የሚያምን፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡አለው፤በልጁ፡የማያምን፡ግን፡የእግዚአብሔር፡ቍጣ፡በርሱ፡ ላይ፡ይኖራል፡እንጂ፡ሕይወትን፡አያይም።

ምዕራፍ ፬ ለማስተካከል

1፤እንግዲህ፦ኢየሱስ፡ከዮሐንስ፡ይልቅ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ያደርጋል፡ያጠምቅማል፡ማለትን፡ፈሪሳውያን፡ እንደ፡ሰሙ፡ጌታ፡ባወቀ፡ጊዜ፥ 2-3፤ይሁዳን፡ትቶ፡ወደ፡ገሊላ፡ደግሞ፡ኼደ፤ዳሩ፡ግን፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡እንጂ፡ኢየሱስ፡ራሱ፡ አላጠመቀም። 4፤በሰማርያም፡ሊያልፍ፡ግድ፡ኾነበት። 5፤ስለዚህ፥ያዕቆብ፡ለልጁ፣ለዮሴፍ፡በሰጠው፡ስፍራ፡አጠገብ፡ወደምትኾን፥ሲካር፡ወደምትባል፡የሰማርያ፡ከተማ፡መጣ፤ 6፤በዚያም፡የያዕቆብ፡ጕድጓድ፡ነበረ።ኢየሱስም፡መንገድ፡ከመኼድ፡ደክሞ፡በጕድጓድ፡አጠገብ፡እንዲህ፡ ተቀመጠ፤ጊዜውም፡ስድስት፡ሰዓት፡ያኽል፡ነበረ። 7፤ከሰማርያ፡አንዲት፡ሴት፡ውሃ፡ልትቀዳ፡መጣች።ኢየሱስም፦ውሃ፡አጠጪኝ፡አላት፤ 8፤ደቀ፡መዛሙርቱ፡ምግብ፡ሊገዙ፡ወደ፡ከተማ፡ኼደው፡ነበርና። 9፤ስለዚህ፥ሳምራዊቲቱ፦አንተ፡የይሁዳ፡ሰው፡ስትኾን፡ሳምራዊት፡ሴት፡ከምኾን፡ከእኔ፡መጠጥ፡እንዴት፡ትለምናለኽ፧አለችው፤አይሁድ፡ከሳምራውያን፡ጋራ፡አይተባበሩም፡ነበርና። 10፤ኢየሱስ፡መልሶ፦የእግዚአብሔርን፡ስጦታና፦ውሃ፡አጠጪኝ፡የሚልሽ፡ማን፡መኾኑንስ፡ ብታውቂ፥አንቺ፡ትለምኚው፡ነበርሽ፡የሕይወትም፡ውሃ፡ይሰጥሽ፡ነበር፡አላት። 11፤ሴቲቱ፦ጌታ፡ሆይ፥መቅጃ፡የለኽም፡ጕድጓዱም፡ጥልቅ፡ነው፤እንግዲህ፡የሕይወት፡ውሃ፡ከወዴት፡ ታገኛለኽ።

 
ኢየሱስ ክርስቶስ ከሳምራዊቷ ሴት ጋር በውሃ ጉድጓዱ ቦታ ሲነጋገር::

12፤በእውኑ፡አንተ፡ይህን፡ጕድጓድ፡ከሰጠን፡ከአባታችን፡ከያዕቆብ፡ትበልጣለኽን፧ራሱም፡ልጆቹም፡ ከብቶቹም፡ከዚህ፡ጠጥተዋል፡አለችው። 13፤ኢየሱስም፡መልሶ፦ከዚህ፡ውሃ፡የሚጠጣ፡ዅሉ፡እንደ፡ገና፡ይጠማል፤ 14፤እኔ፡ከምሰጠው፡ውሃ፡የሚጠጣ፡ዅሉ፡ግን፡ለዘለዓለም፡አይጠማም፥እኔ፡የምሰጠው፡ውሃ፡በርሱ፡ ውስጥ፡ለዘለዓለም፡ሕይወት፡የሚፈልቅ፡የውሃ፡ምንጭ፡ይኾናል፡እንጂ፡አላት። 15፤ሴቲቱ፦ጌታ፡ሆይ፥እንዳልጠማ፡ውሃም፡ልቀዳ፡ወደዚህ፡እንዳልመጣ፡ይህን፡ውሃ፡ስጠኝ፡አለችው። 16፤ኢየሱስም፦ኺጂና፡ባልሽን፡ጠርተሽ፡ወደዚህ፡ነዪ፡አላት። 17፤ሴቲቱ፡መልሳ፦ባል፡የለኝም፡አለችው።ኢየሱስ፦ባል፡የለኝም፡በማለትሽ፡መልካም፡ተናገርሽ፤ 18፤ዐምስት፡ባሎች፡ነበሩሽና፥አኹን፡ከአንቺ፡ጋራ፡ያለው፡ባልሽ፡አይደለም፤በዚህስ፡እውነት፡ተናገርሽ፡ አላት። 19፤ሴቲቱ፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡ነቢይ፡እንደ፡ኾንኽ፡አያለኹ። 20፤አባቶቻችን፡በዚህ፡ተራራ፡ሰገዱ፤እናንተም፦ሰው፡ሊሰግድበት፡የሚገ፟ባ፟ው፡ስፍራ፡በኢየሩሳሌም፡ነው፡ ትላላችኹ፡አለችው። 21፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አላት፦አንቺ፡ሴት፥እመኚኝ፥በዚህ፡ተራራ፡ወይም፡በኢየሩሳሌም፡ለአብ፡ የማትሰግዱበት፡ጊዜ፡ይመጣል። 22፤እናንተስ፡ለማታውቁት፡ትሰግዳላችኹ፤እኛ፡መዳን፡ከአይሁድ፡ነውና፥ለምናውቀው፡እንሰግዳለን። 23፤ነገር፡ግን፥በእውነት፡የሚሰግዱ፡ለአብ፡በመንፈስና፡በእውነት፡የሚሰግዱበት፡ጊዜ፡ይመጣል፡አኹንም፡ ኾኗል፤አብ፡ሊሰግዱለት፡እንደ፡እነዚህ፡ያሉትን፡ይሻልና፤ 24፤እግዚአብሔር፡መንፈስ፡ነው፥የሚሰግዱለትም፡በመንፈስና፡በእውነት፡ሊሰግዱለት፡ያስፈልጋቸዋል። 25፤ሴቲቱ፦ክርስቶስ፡የሚባል፡መሲሕ፡እንዲመጣ፡ዐውቃለኹ፤ርሱ፡ሲመጣ፡ዅሉን፡ይነግረናል፡አለችው። 26፤ኢየሱስ፦የምናገርሽ፡እኔ፡ርሱ፡ነኝ፡አላት። 27፤በዚያም፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡መጡና፡ከሴት፡ጋራ፡በመነጋገሩ፡ተደነቁ፤ነገር፡ግን፦ምን፡ ትፈልጊያለሽ፧ወይም፦ስለ፡ምን፡ትናገራታለኽ፧ያለ፡ማንም፡አልነበረም። 28፤ሴቲቱም፡እንስራዋን፡ትታ፡ወደ፡ከተማ፡ኼደች፡ለሰዎችም፦ 29፤ያደረግኹትን፡ዅሉ፡የነገረኝን፡ሰው፡ኑና፡እዩ፤እንጃ፡ርሱ፡ክርስቶስ፡ይኾንን፧አለች። 30፤ከከተማ፡ወጥተው፡ወደ፡ርሱ፡ይመጡ፡ነበር። 31፤ይህም፡ሲኾን፡ሳለ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፦መምህር፡ሆይ፥ብላ፡ብለው፡ለመኑት። 32፤ርሱ፡ግን፦እናንተ፡የማታውቁት፡የምበላው፡መብል፡ለእኔ፡አለኝ፡አላቸው። 33፤ስለዚህ፥ደቀ፡መዛሙርቱ፦የሚበላው፡አንዳች፡ሰው፡አምጥቶለት፡ይኾንን፧ተባባሉ። 34፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አላቸው፦የእኔስ፡መብል፡የላከኝን፡ፈቃድ፡ኣደርግ፡ዘንድ፡ሥራውንም፡እፈጽም፡ ዘንድ፡ነው። 35፤እናንተ፦ገና፡አራት፡ወር፡ቀርቷል፡መከርም፡ይመጣል፡ትሉ፡ የለምን፧እንሆ፥እላችዃለኹ፥ዐይናችኹን፡አንሡ፡አዝመራውም፡አኹን፡እንደ፡ነጣ፡ዕርሻውን፡ተመልከቱ። 36፤የሚያጭድ፡ደመ፡ወዝን፡ይቀበላል፥የሚዘራና፡የሚያጭድም፡ዐብረው፡ደስ፡እንዲላቸው፡ለዘለዓለም፡ ሕይወት፡ፍሬን፡ይሰበስባል። 37፤አንዱ፡ይዘራል፡አንዱም፡ያጭዳል፡የሚለው፡ቃል፡በዚህ፡እውነት፡ኾኗልና። 38፤እኔም፡እናንተ፡ያልደከማችኹበትን፡ታጭዱ፡ዘንድ፡ሰደድዃችኹ፤ሌላዎች፡ደከሙ፡እናንተም፡ በድካማቸው፡ገባችኹ። 39፤ሴቲቱም፦ያደረግኹትን፡ዅሉ፡ነገረኝ፡ብላ፡ስለመሰከረችው፡ቃል፡ከዚያች፡ከተማ፡የሰማርያ፡ሰዎች፡ ብዙ፡አመኑበት። 40፤የሰማርያ፡ሰዎችም፡ወደ፡ርሱ፡በመጡ፡ጊዜ፡በእነርሱ፡ዘንድ፡እንዲኖር፡ለመኑት፤በዚያም፡ኹለት፡ቀን፡ያኽል፡ኖረ። 41፤ስለ፡ቃሉ፡ከፊተኛዎች፡ይልቅ፡ብዙ፡ሰዎች፡አመኑ፤ 42፤ሴቲቱንም፦አኹን፡የምናምን፡ስለ፡ቃልሽ፡አይደለም፥እኛ፡ራሳችን፡ሰምተነዋልና፤ርሱም፡በእውነት፡ ክርስቶስ፡የዓለም፡መድኀኒት፡እንደ፡ኾነ፡እናውቃለን፡ይሏት፡ነበር። 43፤ከኹለቱ፡ቀኖችም፡በዃላ፡ከዚያ፡ወጥቶ፡ወደ፡ገሊላ፡ኼደ። 44፤ነቢይ፡በገዛ፡አገሩ፡እንዳይከበር፡ኢየሱስ፡ራሱ፡መስክሯልና። 45፤ወደ፡ገሊላም፡በመጣ፡ጊዜ፥የገሊላ፡ሰዎች፡ራሳቸው፡ደግሞ፡ለበዓል፡መጥተው፡ነበርና፥በበዓል፡ በኢየሩሳሌም፡ያደረገውን፡ዅሉ፡ስላዩ፡ተቀበሉት። 46፤ኢየሱስም፡ውሃውን፡የወይን፡ጠጅ፡ወዳደረገባት፡ወደ፡ገሊላ፡ቃና፡ዳግመኛ፡መጣ።በቅፍርናሖምም፡ ልጁ፡የታመመበት፡ከንጉሥ፡ቤት፡አንድ፡ሹም፡ነበረ። 47፤ርሱም፡ኢየሱስ፡ከይሁዳ፡ወደ፡ገሊላ፡እንደ፡መጣ፡ሰምቶ፡ልጁ፡ሊሞት፡ስለ፡አለው፡ወደ፡ርሱ፡ኼደ፡ ወርዶም፡እንዲፈውስለት፡ለመነው። 48፤ስለዚህም፡ኢየሱስ፦ምልክትና፡ድንቅ፡ነገር፡ካላያችኹ፡ከቶ፡አታምኑም፡አለው። 49፤ሹሙም፦ጌታ፡ሆይ፥ብላቴናዬ፡ሳይሞት፡ውረድ፡አለው። 50፤ኢየሱስም፦ኺድ፤ልጅኽ፡በሕይወት፡አለ፡አለው።ሰውዬውም፡ኢየሱስ፡የነገረውን፡ቃል፡አምኖ፡ኼደ። 51፤ርሱም፡ሲወርድ፡ሳለ፡ባሮቹ፡ተገናኙትና፦ብላቴናኽ፡በሕይወት፡አለ፡ብለው፡ነገሩት። 52፤ርሱም፡በጎ፡የኾነበትን፡ሰዓት፡ጠየቃቸው፤እነርሱም፦ትናንት፡በሰባት፡ሰዓት፡ንዳዱ፡ለቀቀው፡አሉት። 53፤አባቱም፥ኢየሱስ፦ልጅኽ፡በሕይወት፡አለ፡ባለው፡በዚያ፡ሰዓት፡እንደ፡ኾነ፡ዐወቀ፤ርሱም፡ከቤተ፡ ሰዎቹ፡ዅሉ፡ጋራ፡አመነ። 54፤ይህም፡ደግሞ፡ኢየሱስ፡ከይሁዳ፡ወደ፡ገሊላ፡መጥቶ፡ያደረገው፡ኹለተኛ፡ምልክት፡ነው።

ምዕራፍ ፭ ለማስተካከል

1፤ከዚህ፡በዃላ፡የአይሁድ፡በዓል፡ነበረ፥ኢየሱስም፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ወጣ። 2፤በኢየሩሳሌምም፡በበጎች፡በር፡አጠገብ፡በዕብራይስጥ፡ቤተ፡ሳይዳ፡የምትባል፡አንዲት፡መጠመቂያ፡ ነበረች፤ዐምስትም፡መመላለሻ፡ነበረባት። 3፤በእነዚህ፡ውስጥ፡የውሃውን፡መንቀሳቀስ፡እየጠበቁ፡በሽተኛዎችና፡ዕውሮች፡ዐንካሳዎችም፡ሰውነታቸውም፡ የሰለለ፡ብዙ፡ሕዝብ፡ይተኙ፡ነበር። 4፤አንዳንድ፡ጊዜ፡የጌታ፡መልአክ፡ወደ፡መጠመቂያዪቱ፡ወርዶ፡ውሃውን፡ያናውጥ፡ነበርና፤እንግዲህ፡ ከውሃው፡መናወጥ፡በዃላ፡በመዠመሪያ፡የገባ፡ከማናቸው፡ካለበት፡ደዌ፡ጤናማ፡ይኾን፡ነበር። 5፤በዚያም፡ከሠላሳ፡ስምንት፡ዓመት፡ዠምሮ፡የታመመ፡አንድ፡ሰው፡ነበረ፤ 6፤ኢየሱስ፡ይህን፡ሰው፡ተኝቶ፡ባየ፡ጊዜ፥እስከ፡አኹን፡ብዙ፡ዘመን፡እንዲሁ፡እንደ፡ነበረ፡ ዐውቆ፦ልትድን፡ትወዳለኽን፧አለው። 7፤ድውዩም፦ጌታ፡ሆይ፥ውሃው፡በተናወጠ፡ጊዜ፡በመጠመቂያዪቱ፡ውስጥ፡የሚያኖረኝ፡ሰው፡ የለኝም፥ነገር፡ግን፥እኔ፡ስመጣ፡ሳለኹ፡ሌላው፡ቀድሞኝ፡ይወርዳል፡ብሎ፡መለሰለት። 8፤ኢየሱስ፦ተነሣና፡ዐልጋኽን፡ተሸክመኽ፡ኺድ፡አለው። 9፤ወዲያውም፡ሰውዬው፡ዳነ፡ዐልጋውንም፡ተሸክሞ፡ኼደ። 10፤ያም፡ቀን፡ሰንበት፡ነበረ።ስለዚህ፡አይሁድ፡የተፈወሰውን፡ሰው፦ሰንበት፡ነው፥ዐልጋኽንም፡ልትሸከም፡ አልተፈቀደልኽም፡አሉት። 11፤ርሱ፡ግን፦ያዳነኝ፡ያ፡ሰው፦ዐልጋኽን፡ተሸክመኽ፡ኺድ፡አለኝ፡ብሎ፡መለሰላቸው። 12፤እነርሱም፦ዐልጋኽን፡ተሸክመኽ፡ኺድ፡ያለኽ፡ሰው፡ማን፡ነው፧ብለው፡ጠየቁት። 13፤ዳሩ፡ግን፡በዚያ፡ስፍራ፡ሕዝብ፡ሰለ፡ነበሩ፡ኢየሱስ፡ፈቀቅ፡ብሎ፡ነበርና፥የተፈወሰው፡ሰው፡ማን፡ እንደ፡ኾነ፡አላወቀም። 14፤ከዚህ፡በዃላ፡ኢየሱስ፡በመቅደስ፡አገኘውና፦እንሆ፥ድነኻል፤ከዚህ፡የሚብስ፡እንዳይደርስብኽ፡ወደ፡ ፊት፡ኀጢአት፡አትሥራ፡አለው። 15፤ሰውዬው፡ኼዶ፡ያዳነው፡ኢየሱስ፡እንደ፡ኾነ፡ለአይሁድ፡ነገረ። 16፤ስለዚህም፡በሰንበት፡ይህን፡ስላደረገ፡አይሁድ፡ኢየሱስን፡ያሳድዱት፡ነበር፡ሊገድሉትም፡ይፈልጉ፡ነበር። 17፤ኢየሱስ፡ግን፦አባቴ፡እስከ፡ዛሬ፡ይሠራል፡እኔም፡ደግሞ፡እሠራለኹ፡ብሎ፡መለሰላቸው። 18፤እንግዲህ፡ሰንበትን፡ስለ፡ሻረ፡ብቻ፡አይደለም፥ነገር፡ግን፥ደግሞ፡ራሱን፡ከእግዚአብሔር፡ጋራ፡ አስተካክሎ፦እግዚአብሔር፡አባቴ፡ነው፡ስለ፡አለ፥ስለዚህ፡አይሁድ፡ሊገድሉት፡አብዝተው፡ይፈልጉት፡ነበር። 19፤ስለዚህ፥ኢየሱስ፡መለሰ፥እንዲህም፡አላቸው፦እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥አብ፡ሲያደርግ፡ያየውን፡ ነው፡እንጂ፡ወልድ፡ከራሱ፡ሊያደርግ፡ምንም፡አይችልም፤ያ፡የሚያደርገውን፡ዅሉ፡ወልድ፡ደግሞ፡ይህን፡ እንዲሁ፡ያደርጋልና። 20፤አብ፡ወልድን፡ይወዳልና፥የሚያደርገውንም፡ዅሉ፡ያሳየዋል፤እናንተም፡ትደነቁ፡ዘንድ፡ከዚህ፡የሚበልጥ፡ ሥራ፡ያሳየዋል። 21፤አብ፡ሙታንን፡እንደሚያነሣ፡ሕይወትም፡እንደሚሰጣቸው፥እንዲሁ፡ወልድ፡ደግሞ፡ለሚወዳቸው፡ሕይወትን፡ይሰጣቸዋል። 22-23፤ሰዎች፡ዅሉ፡አብን፡እንደሚያከብሩት፡ወልድን፡ያከብሩት፡ዘንድ፥ፍርድን፡ዅሉ፡ለወልድ፡ሰጠው፡ እንጂ፡አብ፡ባንድ፡ሰው፡ስንኳ፡አይፈርድም።ወልድን፡የማያከብር፡የላከውን፡አብን፡አያከብርም። 24፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥ቃሌን፡የሚሰማ፡የላከኝንም፡የሚያምን፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡ አለው፥ከሞትም፡ወደ፡ሕይወት፡ተሻገረ፡እንጂ፡ወደ፡ፍርድ፡አይመጣም። 25፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥ሙታን፡የእግዚአብሔርን፡ልጅ፡ድምፅ፡የሚሰሙበት፡ሰዓት፡ይመጣል፡ ርሱም፡አኹን፡ነው፤የሚሰሙትም፡በሕይወት፡ይኖራሉ። 26፤አብ፡በራሱ፡ሕይወት፡እንዳለው፡እንዲሁ፡ደግሞ፡ለወልድ፡በራሱ፡ሕይወት፡እንዲኖረው፡ሰጥቶታልና። 27፤የሰው፡ልጅም፡ስለ፡ኾነ፡ይፈርድ፡ዘንድ፡ሥልጣን፡ሰጠው። 28-29፤በመቃብር፡ያሉቱ፡ዅሉ፡ድምፁን፡የሚሰሙበት፡ሰዓት፡ይመጣል፤መልካምም፡ያደረጉ፡ለሕይወት፡ ትንሣኤ፡ክፉም፡ያደረጉ፡ለፍርድ፡ትንሣኤ፡ይወጣሉና፡በዚህ፡አታድንቁ። 30፤እኔ፡ከራሴ፡አንዳች፡ላደርግ፡አይቻለኝም፤እንደ፡ሰማኹ፡እፈርዳለኹ፡ፍርዴም፡ቅን፡ነው፥የላከኝን፡ ፈቃድ፡እንጂ፡ፈቃዴን፡አልሻምና። 31፤እኔ፡ስለ፡እኔ፡ስለ፡ራሴ፡ብመሰክር፡ምስክሬ፡እውነት፡አይደለም፤ 32፤ስለ፡እኔ፡የሚመሰክር፡ሌላ፡ነው፥ርሱም፡ስለ፡እኔ፡የሚመሰክረው፡ምስክር፡እውነት፡እንደ፡ኾነ፡ ዐውቃለኹ። 33፤እናንተ፡ወደ፡ዮሐንስ፡ልካችዃል፡ርሱም፡ለእውነት፡መስክሯል። 34፤እኔ፡ግን፡ከሰው፡ምስክር፡አልቀበልም፥እናንተ፡እንድትድኑ፡ይህን፡እላለኹ፡እንጂ። 35፤ርሱ፡የሚነድና፡የሚያበራ፡መብራት፡ነበረ፥እናንተም፡ጥቂት፡ዘመን፡በብርሃኑ፡ደስ፡ሊላችኹ፡ ወደዳችኹ። 36፤እኔ፡ግን፡ከዮሐንስ፡ምስክር፡የሚበልጥ፡ምስክር፡አለኝ፤አብ፡ልፈጽመው፡የሰጠኝ፡ሥራ፥ይህ፡ የማደርገው፡ሥራ፥አብ፡እንደ፡ላከኝ፡ስለ፡እኔ፡ይመሰክራልና። 37፤የላከኝ፡አብም፡ርሱ፡ስለ፡እኔ፡መስክሯል።ድምፁን፡ከቶ፡አልሰማችኹም፥መልኩንም፡አላያችኹም፤ 38፤ርሱም፡የላከውን፡እናንተ፡አታምኑምና፡በእናንተ፡ዘንድ፡የሚኖር፡ቃሉ፡የላችኹም። 39፤እናንተ፡በመጻሕፍት፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡እንዳላችኹ፡ይመስላችዃልና፥እነርሱን፡ ትመረምራላችኹ፤እነርሱም፡ስለ፡እኔ፡የሚመሰክሩ፡ናቸው፤ 40፤ነገር፡ግን፥ሕይወት፡እንዲኾንላችኹ፡ወደ፡እኔ፡ልትመጡ፡አትወዱም። 41-42፤ከሰው፡ክብርን፡አልቀበልም፤ዳሩ፡ግን፡የእግዚአብሔር፡ፍቅር፡በራሳችኹ፡እንደ፡ሌላችኹ፡ ዐውቃችዃለኹ። 43፤እኔ፡በአባቴ፡ስም፡መጥቻለኹ፡አልተቀበላችኹኝምም፤ሌላው፡በራሱ፡ስም፡ቢመጣ፡ርሱን፡ ትቀበሉታላችኹ። 44፤እናንተ፡ርስ፡በርሳችኹ፡ክብር፡የምትቀባበሉ፡ከአንዱም፡ከእግዚአብሔር፡ያለውን፡ክብር፡ የማትፈልጉ፥እንዴት፡ልታምኑ፡ትችላላችኹ፧ 45፤እኔ፡በአብ፡ዘንድ፡የምከሳችኹ፡አይምሰላችኹ፤የሚከሳችኹ፡አለ፤ርሱም፡ተስፋ፡የምታደርጉት፡ሙሴ፡ነው። 46፤ሙሴንስ፡ብታምኑት፡እኔን፡ባመናችኹ፡ነበር፤ርሱ፡ስለ፡እኔ፡ጽፏልና። 47፤መጻሕፍትን፡ካላመናችኹ፡ግን፡ቃሌን፡እንዴት፡ታምናላችኹ።

ምዕራፍ ፮ ለማስተካከል

 1፤ከዚህ፡በዃላ፡ኢየሱስ፡ወደገሊላ፡ባሕር፡ማዶ፡ተሻገረ፤ርሱም፡የጥብርያዶስ፡ባሕር፡ነው። 2፤በበሽተኛዎችም፡ያደረገውን፡ምልክቶች፡ስላዩ፡ብዙ፡ሕዝብ፡ተከተሉት። 3፤ኢየሱስም፡ወደ፡ተራራ፡ወጣና፡በዚያ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡ተቀመጠ። 4፤የአይሁድ፡በዓልም፡ፋሲካ፡ቀርቦ፡ነበር። 5፤ኢየሱስም፡ዐይኖቹን፡አንሥቶ፡ብዙ፡ሕዝብ፡ወደ፡ርሱ፡ሲመጣ፡አየና፡ፊልጶስን፦እነዚህ፡እንዲበሉ፡እንጀራ፡ከወዴት፡እንገዛለን፧አለው። 6፤ራሱ፡ሊያደርግ፡ያለውን፡ያውቅ፡ነበርና፥ሊፈትነው፡ይህን፡ተናገረ። 7፤ፊልጶስ፦እያንዳንዳቸው፡ትንሽ፡ትንሽ፡እንኳ፡እንዲቀበሉ፡የኹለት፡መቶ፡ዲናር፡እንጀራ፡አይበቃቸውም፡ ብሎ፡መለሰለት። 8፤ከደቀ፡መዛሙርቱ፡አንዱ፡የስምዖን፡ጴጥሮስ፡ወንድም፡እንድርያስ። 9፤ዐምስት፡የገብስ፡እንጀራና፡ኹለት፡ዓሣ፡የያዘ፡ብላቴና፡በዚህ፡አለ፤ነገር፡ግን፥እነዚህን፡ለሚያኽሉ፡ሰዎች፡ይህ፡ምን፡ይኾናል፧አለው። 10፤ኢየሱስም፦ሰዎቹን፡እንዲቀመጡ፡አድርጉ፡አለ።በዚያም፡ስፍራ፡ብዙ፡ሣር፡ነበረበት።ወንዶችም፡ ተቀመጡ፡ቍጥራቸውም፡ዐምስት፡ሺሕ፡የሚያኽል፡ነበር። 11፤ኢየሱስም፡እንጀራውን፡ያዘ፥አመስግኖም፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ሰጠ፥ደቀ፡መዛሙርቱም፡ለተቀመጡት፡ ሰዎች፡ሰጧቸው፡እንዲሁም፡ከዓሣው፡በፈለጉት፡መጠን። 12፤ከጠገቡም፡በዃላ፡ደቀ፡መዛሙርቱን፦አንድ፡ስንኳ፡እንዳይጠፋ፡የተረፈውን፡ቍርስራሽ፡አከማቹ፡ አላቸው። 13፤ሰለዚህ፡አከማቹ፥ከበሉትም፡ከዐምስቱ፡የገብስ፡እንጀራ፡የተረፈውን፡ቍርስራሽ፡ዐሥራ፡ኹለት፡መሶብ፡ ሞሉ። 14፤ከዚህ፡የተነሣ፡ሰዎቹ፡ኢየሱስ፡ያደረገውን፡ምልክት፡ባዩ፡ጊዜ፦ይህ፡በእውነት፡ወደ፡ዓለም፡ የሚመጣው፡ነቢይ፡ነው፡አሉ። 15፤በዚህም፡ምክንያት፡ኢየሱስ፡ያነግሡት፡ዘንድ፡ሊመጡና፡ሊነጥቁት፡እንዳላቸው፡ዐውቆ፡ደግሞ፡ወደ፡ተራራ፡ብቻውን፡ፈቀቅ፡አለ። 16፤በመሸም፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ወደ፡ባሕር፡ወረዱ፥ 17፤በታንኳም፡ገብተው፡በባሕር፡ማዶ፡ወደ፡ቅፍርናሖም፡ይመጡ፡ነበር።አኹንም፡ጨልሞ፡ነበር፤ኢየሱስም፡ ገና፡ወደ፡እነርሱ፡አልመጣም፡ነበር፤ 18፤ብርቱ፡ነፋስም፡ስለ፡ነፈሰ፡ባሕሩ፡ተናወጠ። 19፤ኻያ፡ዐምስት፡ወይም፡ሠላሳ፡ምዕራፍ፡ከቀዘፉ፡በዃላም፥ኢየሱስ፡በባሕር፡ላይ፡እየኼደ፡ወደ፡ታንኳዪቱ፡ ሲቀርብ፡አይተው፡ፈሩ። 20፤ርሱ፡ግን፦እኔ፡ነኝ፤አትፍሩ፡አላቸው። 21፤ስለዚህ፥በታንኳዪቱ፡ሊቀበሉት፡ወደዱ፤ወዲያውም፡ታንኳዪቱ፡ወደሚኼዱበት፡ምድር፡ደረሰች። 22፤በነገው፡በባሕር፡ማዶ፡ቆመው፡የነበሩ፡ሕዝቡ፡ከአንዲት፡ጀልባ፡በቀር፡በዚያ፡ሌላ፡ጀልባ፡ እንዳልነበረች፥ደቀ፡መዛሙርቱም፡ለብቻቸው፡እንደ፡ኼዱ፡እንጂ፡ኢየሱስ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡ወደ፡ ታንኳዪቱ፡እንዳልገባ፡አዩ፤ 23፤ዳሩ፡ግን፡ሌላዎች፡ጀልባዎች፡ጌታ፡የባረከውን፡እንጀራ፡ወደበሉበት፡ስፍራ፡አጠገብ፡ከጥብርያዶስ፡ መጡ። 24፤ሕዝቡም፡ኢየሱስ፡ወይም፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡በዚያ፡እንዳልነበሩ፡ባዩ፡ጊዜ፥ራሳቸው፡በጀልባዎቹ፡ ገብተው፡ኢየሱስን፡እየፈለጉ፡ወደ፡ቅፍርናሖም፡መጡ። 25፤በባሕር፡ማዶም፡ሲያገኙት።መምህር፡ሆይ፥ወደዚህ፡መቼ፡መጣኽ፧አሉት። 26፤ኢየሱስም፡መልሶ፦እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥የምትፈልጉኝ፡እንጀራን፡ስለ፡በላችኹና፡ስለ፡ ጠገባችኹ፡ነው፡እንጂ፡ምልክቶችን፡ስላያችኹ፡አይደለም። 27፤ለሚጠፋ፡መብል፡አትሥሩ፤ነገር፡ግን፥ለዘለዓለም፡ሕይወት፡ለሚኖር፡መብል፡የሰው፡ልጅ፡ ለሚሰጣችኹ፡ሥሩ፤ርሱን፡እግዚአብሔር፡አብ፡ዐትሞታልና። 28፤እንግዲህ፦የእግዚአብሔርን፡ሥራ፡እንድንሠራ፡ምን፡እናድርግ፧አሉት። 29፤ኢየሱስ፡መልሶ፦ይህ፡የእግዚአብሔር፡ሥራ፡ርሱ፡በላከው፡እንድታምኑ፡ነው፡አላቸው። 30፤እንግዲህ፦እንኪያ፡አይተን፡እንድናምንኽ፡አንተ፡ምን፡ምልክት፡ታደርጋለኽ፧ምንስ፡ትሠራለኽ። 31፤ይበሉ፡ዘንድ፡ከሰማይ፡እንጀራ፡ሰጣቸው፡ተብሎ፡እንደ፡ተጻፈ፥አባቶቻችን፡በምድረ፡በዳ፡መና፟፡በሉ፡ አሉት። 32፤ኢየሱስም፦እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥እውነተኛ፡እንጀራ፡ከሰማይ፡የሚሰጣችኹ፡አባቴ፡ነው፡ እንጂ፡ከሰማይ፡እንጀራ፡የሰጣችኹ፡ሙሴ፡አይደለም፤ 33፤የእግዚአብሔር፡እንጀራ፡ከሰማይ፡የሚወርድ፡ለዓለምም፡ሕይወትን፡የሚሰጥ፡ነውና፥አላቸው። 34፤ስለዚህ፦ጌታ፡ሆይ፥ይህን፡እንጀራ፡ዘወትር፡ስጠን፡አሉት። 35፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አላቸው፦የሕይወት፡እንጀራ፡እኔ፡ነኝ፤ወደ፡እኔ፡የሚመጣ፡ከቶ፡አይራብም፡በእኔ፡ የሚያምንም፡ዅልጊዜ፡ከቶ፡አይጠማም። 36፤ነገር፡ግን፥አይታችኹኝ፡እንዳላመናችኹ፡አልዃችኹ። 37፤አብ፡የሚሰጠኝ፡ዅሉ፡ወደ፡እኔ፡ይመጣል፥ወደ፡እኔም፡የሚመጣውን፡ከቶ፡ወደ፡ውጭ፡አላወጣውም፤ 38፤ፈቃዴን፡ለማድረግ፡አይደለም፡እንጂ፡የላከኝን፡ፈቃድ፡ለማድረግ፡ከሰማይ፡ወርጃለኹና። 39፤ከሰጠኝም፡ዅሉ፡አንድን፡ስንኳ፡እንዳላጠፋ፡በመጨረሻው፡ቀን፡እንዳስነሣው፡እንጂ፡የላከኝ፡የአብ፡ ፈቃድ፡ይህ፡ነው። 40፤ልጅንም፡አይቶ፡በርሱ፡የሚያምን፡ዅሉ፡የዘለዓለም፡ሕይወትን፡እንዲያገኝ፡የአባቴ፡ፈቃድ፡ይህ፡ ነው፥እኔም፡በመጨረሻው፡ቀን፡አስነሣዋለኹ። 41፤እንግዲህ፡አይሁድ፦ከሰማይ፡የወረደ፡እንጀራ፡እኔ፡ነኝ፡ስለ፡አለ፡ስለ፡ርሱ፡አንጐራጐሩና፦ 42፤አባቱንና፡እናቱን፡የምናውቃቸው፡ይህ፡የዮሴፍ፡ልጅ፡ኢየሱስ፡አይደለምን፧እንግዲህ፦ከሰማይ፡ ወርጃለኹ፡እንዴት፡ይላል፧አሉ። 43፤ኢየሱስ፡መለሰ፡አላቸውም፦ርስ፡በርሳችኹ፡አታንጐራጕሩ። 44፤የላከኝ፡አብ፡ከሳበው፡በቀር፡ወደ፡እኔ፡ሊመጣ፡የሚችል፡የለም፥እኔም፡በመጨረሻው፡ቀን፡ አስነሣዋለኹ። 45፤ዅሉም፡ከእግዚአብሔር፡የተማሩ፡ይኾናሉ፡ተብሎ፡በነቢያት፡ተጽፏል፤እንግዲህ፡ከአብ፡የሰማ፡ የተማረም፡ዅሉ፡ወደ፡እኔ፡ይመጣል። 46፤አብን፡ያየ፡ማንም፡የለም፤ከእግዚአብሔር፡ከኾነ፡በቀር፥ርሱ፡አብን፡አይቷል። 47፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፡በእኔ፡የሚያምን፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡አለው። 48፤የሕይወት፡እንጀራ፡እኔ፡ነኝ። 49፤አባቶቻችኹ፡በምድረ፡በዳ፡መና፟፡በሉ፥ሞቱም፤ 50፤ሰው፡ከርሱ፡በልቶ፡እንዳይሞት፡ከሰማይ፡አኹን፡የወረደ፡እንጀራ፡ይህ፡ነው። 51፤ከሰማይ፡የወረደ፡ሕያው፡እንጀራ፡እኔ፡ነኝ፤ሰው፡ከዚህ፡እንጀራ፡ቢበላ፡ለዘለዓለም፡ይኖራል፤እኔም፡ ስለዓለም፡ሕይወት፡የምሰጠው፡እንጀራ፡ሥጋዬ፡ነው። 52፤እንግዲህ፡አይሁድ፦ይህ፡ሰው፡ሥጋውን፡ልንበላ፡ይሰጠን፡ዘንድ፡እንዴት፡ይችላል፧ብለው፡ርስ፡ በርሳቸው፡ተከራከሩ። 53፤ስለዚህ፥ኢየሱስ፡እንዲህ፡አላቸው፦እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥የሰውን፡ልጅ፡ሥጋ፡ካልበላችኹ፡ ደሙንም፡ካልጠጣችኹ፡በራሳችኹ፡ሕይወት፡የላችኹም። 54፤ሥጋዬን፡የሚበላ፡ደሜንም፡የሚጠጣ፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡አለው፥እኔም፡በመጨረሻው፡ቀን፡ አስነሣዋለኹ። 55፤ሥጋዬ፡እውነተኛ፡መብል፡ደሜም፡እውነተኛ፡መጠጥ፡ነውና። 56፤ሥጋዬን፡የሚበላ፡ደሜንም፡የሚጠጣ፡በእኔ፡ይኖራል፡እኔም፡በርሱ፡እኖራለኹ። 57፤ሕያው፡አብ፡እንደ፡ላከኝ፡እኔም፡ከአብ፡የተነሣ፡ሕያው፡እንደምኾን፥እንዲሁ፡የሚበላኝ፡ደግሞ፡ከእኔ፡ የተነሣ፡ሕያው፡ይኾናል። 58፤ከሰማይ፡የወረደ፡እንጀራ፡ይህ፡ነው፤አባቶቻችኹ፡መና፟፡በልተው፡እንደ፡ሞቱ፡አይደለም፤ይህን፡እንጀራ፡የሚበላ፡ለዘለዓለም፡ይኖራል፡ 59፤በቅፍርናሖም፡ሲያስተምር፡ይህን፡በምኵራብ፡አለ። 60፤ከደቀ፡መዛሙርቱም፡ብዙዎች፡በሰሙ፡ጊዜ፦ይህ፡የሚያስጨንቅ፡ንግግር፡ነው፤ማን፡ሊሰማው፡ ይችላል፧አሉ። 61፤ኢየሱስ፡ግን፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ስለዚህ፡እንዳንጐራጐሩ፡በልቡ፡ዐውቆ፡አላቸው፦ይህ፡ያሰናክላችዃልን፧ 62፤እንግዲህ፡የሰው፡ልጅ፡አስቀድሞ፡ወደነበረበት፡ሲወጣ፡ብታዩ፡እንዴት፡ይኾናል፧ 63፤ሕይወትን፡የሚሰጥ፡መንፈስ፡ነው፤ሥጋ፡ምንም፡አይጠቅምም፤እኔ፡የነገርዃችኹ፡ቃል፡መንፈስ፡ነው፡ ሕይወትም፡ነው። 64፤ነገር፡ግን፥ከእናንተ፡የማያምኑ፡አሉ።ኢየሱስ፡የማያምኑት፡እነማን፡እንደ፡ኾኑ፡አሳልፎ፡የሚሰጠውም፡ ማን፡እንደ፡ኾነ፡ከመዠመሪያ፡ያውቅ፡ነበርና። 65፤ደግሞ፦ስለዚህ፡አልዃችኹ፥ከአብ፡የተሰጠው፡ካልኾነ፡ወደ፡እኔ፡ሊመጣ፡የሚችል፡የለም፡አለ። 66፤ከዚህም፡የተነሣ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ብዙዎች፡ወደ፡ዃላ፡ተመለሱ፤ወደ፡ፊትም፡ከርሱ፡ጋራ፡ አልኼዱም። 67፤ኢየሱስም፡ለዐሥራ፡ኹለቱ፦እናንተ፡ደግሞ፡ልትኼዱ፡ትወዳላችኹን፧አለ። 68፤ስምዖን፡ጴጥሮስ፦ጌታ፡ሆይ፥ወደ፡ማን፡እንኼዳለን፧አንተ፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡ቃል፡አለኽ፤ 69፤እኛስ፡አንተ፡ክርስቶስ፡የሕያው፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡እንደ፡ኾንኽ፡አምነናል፡ዐውቀናልም፡ብሎ፡ መለሰለት። 70፤ኢየሱስም፦እኔ፡እናንተን፡ዐሥራ፡ኹለታችኹን፡የመረጥዃችኹ፡አይደለምን፧ከእናንተም፡አንዱ፡ ዲያብሎስ፡ነው፡ብሎ፡መለሰላቸው። 71፤ስለስምዖንም፡ልጅ፡ስለአስቆሮቱ፡ይሁዳ፡ተናገረ፤ከዐሥራ፡ኹለቱ፡አንዱ፡የኾነ፡ርሱ፡አሳልፎ፡ይሰጠው፡ ዘንድ፡አለውና።

ምዕራፍ ፯ ለማስተካከል

 1፤ከዚህም፡በዃላ፡ኢየሱስ፡አይሁድ፡ሊገድሉት፡ይፈልጉ፡ስለ፡ነበር፡በይሁዳ፡ሊመላለስ፡አይወድም፡ ነበርና፥በገሊላ፡ይመላለስ፡ነበር። 2፤የአይሁድም፡የዳስ፡በዓል፡ቀርቦ፡ነበር። 3፤እንግዲህ፡ወንድሞቹ፦ደቀ፡መዛሙርትኽ፡ደግሞ፡የምታደርገውን፡ሥራ፡እንዲያዩ፡ከዚህ፡ተነሣና፡ወደ፡ ይሁዳ፡ኺድ፤ 4፤ራሱ፡ሊገለጥ፡እየፈለገ፡በስውር፡የሚሠራ፡የለምና።እነዚህን፡ብታደርግ፥ራስኽን፡ለዓለም፡ግለጥ፡አሉት። 5፤ወንድሞቹ፡ስንኳ፡አላመኑበትም፡ነበርና። 6፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡አላቸው፦ጊዜዬ፡ገና፡አልደረሰም፥ጊዜያችኹ፡ግን፡ዘወትር፡የተመቸ፡ነው። 7፤ዓለም፡እናንተን፡ሊጠላ፡አይቻለውም፤እኔ፡ግን፡ሥራው፡ክፉ፡መኾኑን፡እመሰክርበታለኹና፡እኔን፡ ይጠላኛል። 8፤እናንተ፡ወደዚህ፡በዓል፡ውጡ፤እኔስ፡ጊዜዬ፡ገና፡ስላልተፈጸመ፡ወደዚህ፡በዓል፡ገና፡አልወጣም።9፤ይህንም፡አላቸውና፡በገሊላ፡ቀረ። 10፤ወንድሞቹ፡ግን፡ወደ፡በዓሉ፡ከወጡ፡በዃላ፡በዚያን፡ጊዜ፡ርሱ፡ደግሞ፡በግልጥ፡ሳይኾን፡ተሰውሮ፡ ወጣ። 11፤አይሁድም፦ርሱ፡ወዴት፡ነው፧እያሉ፡በበዓሉ፡ይፈልጉት፡ነበር። 12፤በሕዝብም፡መካከል፡ስለ፡ርሱ፡ብዙ፡ማንጐራጐር፡ነበረ፤አንዳንዱም፦ደግ፡ሰው፡ነው፤ሌላዎች፡ ግን፦አይደለም፥ሕዝቡን፡ግን፡ያስታል፡ይሉ፡ነበር። 13፤ዳሩ፡ግን፡አይሁድን፡ስለ፡ፈሩ፡ማንም፡ስለ፡ርሱ፡በግልጥ፡አይናገርም፡ነበር። 14፤አኹንም፡በበዓሉ፡እኩሌታ፡ኢየሱስ፡ወደ፡መቅደስ፡ወጥቶ፡ያስተምር፡ነበር። 15፤አይሁድም፦ይህ፡ሰው፡ሳይማር፡መጻሕፍትን፡እንዴት፡ያውቃል፧ብለው፡ይደነቁ፡ነበር። 16፤ስለዚህ፥ኢየሱስ፡መለሰ፥እንዲህም፡አላቸው፦ትምህርቴስ፡ከላከኝ፡ነው፡እንጂ፡ከእኔ፡አይደለም፤ 17፤ፈቃዱን፡ሊያደርግ፡የሚወድ፡ቢኖር፥ርሱ፡ይህ፡ትምህርት፡ከእግዚአብሔር፡ቢኾን፡ወይም፡እኔ፡ከራሴ፡ የምናገር፡ብኾን፡ያውቃል። 18፤ከራሱ፡የሚናገር፡የራሱን፡ክብር፡ይፈልጋል፤የላከውን፡ክብር፡የሚፈልግ፡ግን፡ርሱ፡እውነተኛ፡ ነው፥በርሱም፡ዐመፃ፡የለበትም። 19፤ሙሴ፡ሕግን፡አልሰጣችኹምን፧ከእናንተ፡ግን፡ሕግን፡የሚያደርግ፡አንድ፡ስንኳ፡የለም።ልትገድሉኝ፡ስለ፡ምን፡ትፈልጋላችኹ፧ 20፤ሕዝቡ፡መለሱና፦ጋኔን፡አለብኽ፤ማን፡ሊገድልኽ፡ይፈልጋል፧አሉት። 21፤ኢየሱስ፡መለሰ፡አላቸውም፦አንድ፡ሥራ፡አደረግኹ፡ዅላችኹም፡ታደንቃላችኹ። 22፤ስለዚህ፥ሙሴ፡መገረዝን፡ሰጣችኹ፤ከአባቶችም፡ነው፡እንጂ፡ከሙሴ፡አይደለም፤በሰንበትም፡ሰውን፡ ትገርዛላችኹ። 23፤የሙሴ፡ሕግ፡እንዳይሻር፡ሰው፡በሰንበት፡መገረዝን፡የሚቀበል፡ከኾነስ፡ሰውን፡ዅለንተናውን፡በሰንበት፡ ጤናማ፡ስላደረግኹ፡ትቈጡኛላችኹን፧ 24፤ቅን፡ፍርድ፡ፍረዱ፡እንጂ፥በመልክ፡አትፍረዱ። 25፤እንግዲህ፡ከኢየሩሳሌም፡ሰዎች፡አንዳንዶቹ፡እንዲህ፡አሉ፦ሊገድሉት፡የሚፈልጉት፡ይህ፡አይደለምን። 26፤እንሆም፥በግልጥ፡ይናገራል፥አንዳችም፡አይሉትም።አለቃዎቹ፥ይህ፡ሰው፡በእውነት፡ክርስቶስ፡እንደ፡ ኾነ፡በእውነት፡ዐወቁን፧ 27፤ነገር፡ግን፥ይህን፡ከወዴት፡እንደ፡ኾነ፡ዐውቀናል፤ክርስቶስ፡ሲመጣ፡ግን፡ከወዴት፡እንደ፡ኾነ፡ማንም፡ አያውቅም። 28፤እንግዲህ፡ኢየሱስ፡በመቅደስ፡ሲያስተምር፦እኔንም፡ታውቁኛላችኹ፡ከወዴትም፡እንደ፡ኾንኹ፡ ታውቃላችኹ፤እኔም፡በራሴ፡አልመጣኹም፥ነገር፡ግን፥እናንተ፡የማታውቁት፡የላከኝ፡እውነተኛ፡ነው፤ 29፤እኔ፡ግን፡ከርሱ፡ዘንድ፡ነኝ፡ርሱም፡ልኮኛልና፥ዐውቀዋለኹ፡ብሎ፡ጮኸ። 30፤ስለዚህ፥ሊይዙት፡ይፈልጉ፡ነበር፤ነገር፡ግን፥ጊዜው፡ገና፡ስላልደረሰ፡ማንም፡እጁን፡አልጫነበትም። 31፤ከሕዝቡ፡ግን፡ብዙዎች፡አመኑበትና፦ክርስቶስ፡በመጣ፡ጊዜ፡ይህ፡ካደረጋቸው፡ምልክቶች፡ይልቅ፡ ያደርጋልን፧አሉ። 32፤ፈሪሳውያንም፡ሕዝቡ፡ሰለ፡ርሱ፡እንደዚህ፡ሲያንጐራጕሩ፡ሰሙ፤የካህናት፡አለቃዎችም፡ፈሪሳውያም፡ሊይዙት፡ሎሌዎችን፡ላኩ። 33፤ኢየሱስም፦ገና፡ጥቂት፡ጊዜ፡ከእናንተ፡ጋራ፡እቈያለኹ፡ወደላከኝም፡እኼዳለኹ። 34፤ትፈልጉኛላችኹ፡አታገኙኝምም፤እኔም፡ወዳለኹበት፡እናንተ፡ልትመጡ፡አትችሉም፡አለ። 35፤እንግዲህ፡አይሁድ፦እኛ፡እንዳናገኘው፡ይህ፡ወዴት፡ይኼድ፡ዘንድ፡አለው፧በግሪክ፡ሰዎች፡መካከል፡ ተበትነው፡ወደሚኖሩት፡ሊኼድና፡የግሪክን፡ሰዎች፡ሊያስተምር፡አለውን፧ 36፤ርሱ፦ትፈልጉኛላችኹ፡አታገኙኝምም፡እኔም፡ወዳለኹበት፡እናንተ፡ልትመጡ፡አትችሉም፡የሚለው፡ይህ፡ ቃል፡ምንድር፡ነው፧ብለው፡ርስ፡በርሳቸው፡ተነጋገሩ። 37፤ከበዓሉም፡በታላቁ፡በዃለኛው፡ቀን፡ኢየሱስ፡ቆሞ፦ማንም፡የተጠማ፡ቢኖር፡ወደ፡እኔ፡ይምጣና፡ ይጠጣ። 38፤በእኔ፡የሚያምን፡መጽሐፍ፡እንዳለ፥የሕይወት፡ውሃ፡ወንዝ፡ከሆዱ፡ይፈልቃል፡ብሎ፡ጮኸ። 39፤ይህን፡ግን፡በርሱ፡የሚያምኑ፡ሊቀበሉት፡ስላላቸው፡ስለ፡መንፈስ፡ተናገረ፤ኢየሱስ፡ገና፡ ስላልከበረ፥መንፈስ፡ገና፡አልወረደም፡ነበርና። 40፤ስለዚህ፥ከሕዝቡ፡ዐያሌ፡ሰዎች፡ይህን፡ቃል፡ሲሰሙ፦ይህ፡በእውነት፡ነቢዩ፡ነው፡አሉ፤ 41፤ሌላዎች፦ይህ፡ክርስቶስ፡ነው፡አሉ፤ሌላዎች፡ግን፦ክርስቶስ፡በእውኑ፡ከገሊላ፡ይመጣልን፧ 42፤ክርስቶስ፡ከዳዊት፡ዘር፡ዳዊትም፡ከነበረባት፡መንደር፡ከቤተ፡ልሔም፡እንዲመጣ፡መጽሐፍ፡ አላለምን፧አሉ። 43፤እንግዲህ፡ከርሱ፡የተነሣ፡በሕዝቡ፡መካከል፡መለያየት፡ኾነ፤ 44፤ከነርሱም፡አንዳንዶቹ፡ሊይዙት፡ወደዱ፥ነገር፡ግን፥እጁን፡ማንም፡አልጫነበትም። 45፤ሎሌዎቹም፡ወደ፡ካህናት፡አለቃዎችና፡ወደ፡ፈሪሳውያን፡መጡ፤እነዚያም፦ያላመጣችኹት፡ስለ፡ምን፡ ነው፧አሏቸው። 46፤ሎሌዎቹ፦እንደዚህ፡ሰው፡ማንም፡እንዲሁ፡ከቶ፡አልተናገረም፡ብለው፡መለሱ። 47፤እንግዲህ፡ፈሪሳውያን፦እናንተ፡ደግሞ፡ሳታችኹን፧ 48፤ከአለቃዎች፡ወይስ፡ከፈሪሳውያን፡በርሱ፡ያመነ፡አለን፧ 49፤ነገር፡ግን፥ሕግን፡የማያውቀው፡ይህ፡ሕዝብ፡ርጉም፡ነው፡ብለው፡መለሱላቸው። 50፤ከነርሱ፡አንዱ፡በሌሊት፡ቀድሞ፡ወደ፡ርሱ፡መጥቶ፡የነበረ፡ኒቆዲሞስ። 51፤ሕጋችን፡አስቀድሞ፡ከርሱ፡ሳይሰማ፡ምንስ፡እንዳደረገ፡ሳያውቅ፡በሰው፡ይፈርዳልን፧አላቸው። 52፤እነርሱም፡መለሱና፦አንተም፡ደግሞ፡ከገሊላ፡ነኽን፧ነቢይ፡ከገሊላ፡እንዳይነሣ፡መርምርና፡እይ፡አሉት። 53፤እያንዳንዱም፡ወደ፡ቤቱ፡ኼደ።

ምዕራፍ ፰ ለማስተካከል

 1፤ኢየሱስ፡ግን፡ወደ፡ደብረ፡ዘይት፡ኼደ። 2፤ማለዳም፡ደግሞ፡ወደ፡መቅደስ፡ደረሰ፥ሕዝቡም፡ዅሉ፡ወደ፡ርሱ፡መጡ።ተቀምጦም፡ያስተምራቸው፡ ነበር። 3፤ጻፊዎችና፡ፈሪሳውያንም፡በምንዝር፡የተያዘችን፡ሴት፡ወደ፡ርሱ፡አመጡ፡በመካከልም፡ርሱዋን፡አቁመው። 4፤መምህር፡ሆይ፥ይህች፡ሴት፡ስታመነዝር፡ተገኝታ፡ተያዘች። 5፤ሙሴም፡እንደነዚህ፡ያሉት፡እንዲወገሩ፡በሕግ፡አዘዘን፤አንተስ፡ስለ፡ርሷ፡ምን፡ትላለኽ፧አሉት። 6፤የሚከሱበትንም፡እንዲያገኙ፡ሊፈትኑት፡ይህን፡አሉ።ኢየሱስ፡ግን፡ጐንበስ፡ብሎ፡በጣቱ፡በምድር፡ላይ፡ ጻፈ፤ 7፤መላልሰው፡በጠየቁት፡ጊዜ፡ግን፡ቀና፡ብሎ፦ከእናንተ፡ኀጢአት፡የሌለበት፡አስቀድሞ፡በድንጋይ፡ ይውገራት፡አላቸው። 8፤ደግሞም፡ጐንበስ፡ብሎ፡በጣቱ፡በምድር፡ላይ፡ጻፈ። 9፤እነርሱም፡ይህን፡ሲሰሙ፡ኅሊናቸው፡ወቀሳቸውና፡ከሽማግሌዎች፡ዠምረው፡እስከ፡ዃለኛዎች፡አንድ፡ አንድ፡እያሉ፡ወጡ፤ኢየሱስም፡ብቻውን፡ቀረ፥ሴቲቱም፡በመካከል፡ቆማ፡ነበር። 10፤ኢየሱስም፡ቀና፡ብሎ፡ከሴቲቱ፡በቀር፡ማንንም፡ባላየ፡ጊዜ፦አንቺ፡ሴት፥እነዚያ፡ከሳሾችሽ፡ወዴት፡ አሉ፧የፈረደብሽ፡የለምን፧አላት። 11፤ርሷም፦ጌታ፡ሆይ፥አንድ፡ስንኳ፡አለች።ኢየሱስም፦እኔም፡አልፈርድብሽም፤ኺጂ፥ካኹንም፡ዠምሮ፡ ደግመሽ፡ኀጢአት፡አትሥሪ፡አላት። 12፤ደግሞም፡ኢየሱስ፦እኔ፡የዓለም፡ብርሃን፡ነኝ፤የሚከተለኝ፡የሕይወት፡ብርሃን፡ይኾንለታል፡እንጂ፡ በጨለማ፡አይመላለስም፡ብሎ፡ተናገራቸው። 13፤ፈሪሳውያንም፦አንተ፡ስለ፡ራስኽ፡ትመሰክራለኽ፤ምስክርነትኽ፡እውነት፡አይደለም፡አሉት። 14፤ኢየሱስ፡መለሰ፥አላቸውም፦እኔ፡ስለ፡ራሴ፡ምንም፡እንኳ፡ብመሰክር፡ከወዴት፡እንደመጣኹ፡ወዴትም፡እንድኼድ፡ዐውቃለኹና፡ምስክርነቴ፡እውነት፡ነው፤እናንተ፡ግን፡ከወዴት፡እንደ፡መጣኹ፡ወዴትም፡ እንድኼድ፡አታውቁም። 15፤እናንተ፡ሥጋዊ፡ፍርድን፡ትፈርዳላችኹ፤እኔ፡ባንድ፡ሰው፡ስንኳ፡አልፈርድም። 16፤የላከኝ፡አብ፡ከእኔ፡ጋራ፡ነው፡እንጂ፡ብቻዬን፡አይደለኹምና፡እኔ፡ብፈርድ፡ፍርዴ፡እውነት፡ነው። 17፤የኹለት፡ሰዎችም፡ምስክርነት፡እውነት፡እንደ፡ኾነ፡በሕጋችኹ፡ተጽፏል። 18፤ስለ፡ራሴ፡የምመሰክር፡እኔ፡ነኝ፥የላከኝም፡አብ፡ስለ፡እኔ፡ይመሰክራል። 19፤እንግዲህ፦አባትኽ፡ወዴት፡ነው፧አሉት።ኢየሱስ፡መልሶ፦እኔንም፡ወይም፡አባቴንም፡ አታውቁም፤እኔንስ፡ብታውቁኝ፡አባቴን፡ደግሞ፡ባወቃችኹ፡ነበር፡አላቸው። 20፤ኢየሱስ፡በመቅደስ፡ሲያስተምር፡በግምጃ፡ቤት፡አጠገብ፡ይህን፡ነገር፡ተናገረ፤ጊዜው፡ገና፡አልደረሰምና፡ ማንም፡አልያዘውም። 21፤ኢየሱስም፡ደግሞ፦እኔ፡እኼዳለኹ፡ትፈልጉኛላችኹም፡በኀጢአታችኹም፡ትሞታላችኹ፡እኔ፡ ወደምኼድበት፡እናንተ፡ልትመጡ፡አትችሉም፡አላቸው። 22፤አይሁድም፦እኔ፡ወደምኼድበት፡እናንተ፡ልትመጡ፡አትችሉም፡ማለቱ፡ራሱን፡ይገድላልን፧እንጃ፡አሉ። 23፤እናንተ፡ከታች፡ናችኹ፥እኔ፡ከላይ፡ነኝ፤እናንተ፡ከዚህ፡ዓለም፡ናችኹ፥እኔ፡ከዚህ፡ዓለም፡ አይደለኹም። 24፤እንግዲህ፦በኀጢአታችኹ፡ትሞታላችኹ፡አልዃችኹ፤እኔ፡እንደኾንኹ፡ባታምኑ፡በኀጢአታችኹ፡ ትሞታላችኹና፡አላቸው። 25፤እንግዲህ፦አንተ፡ማን፡ነኽ፧አሉት።ኢየሱስም፦ከመዠመሪያ፡ለእናንተ፡የተናገርኹት፡ነኝ። 26፤ስለ፡እናንተ፡የምናገረው፡የምፈርደውም፡ብዙ፡ነገር፡አለኝ፤ዳሩ፡ግን፡የላከኝ፡እውነተኛ፡ነው፥እኔም፡ ከርሱ፡የሰማኹትን፡ይህን፡ለዓለም፡እናገራለኹ፡አላቸው። 27፤ስለ፡አብ፡እንደ፡ነገራቸው፡አላስተዋሉም። 28፤ስለዚህም፡ኢየሱስ፦የሰውን፡ልጅ፡ከፍ፡ከፍ፡ባደረጋችኹት፡ጊዜ፡እኔ፡እኾን፡ዘንድ፡አባቴም፡ እንዳስተማረኝ፡እነዚህን፡እናገር፡ዘንድ፡እንጂ፡ከራሴ፡አንዳች፡እንዳላደርግ፡በዚያን፡ጊዜ፡ታውቃላችኹ። 29፤የላከኝም፡ከእኔ፡ጋራ፡ነው፤እኔ፡ደስ፡የሚያሠኘውን፡ዘወትር፡አደርጋለኹና፡አብ፡ብቻዬን፡አይተወኝም፡ አላቸው። 30፤ይህን፡ሲናገር፡ብዙዎች፡በርሱ፡አመኑ። 31፤ኢየሱስም፡ያመኑትን፡አይሁድ፦እናንተ፡በቃሌ፡ብትኖሩ፡በእውነት፡ደቀ፡መዛሙርቴ፡ናችኹ፤ 32፤እውነትንም፡ታውቃላችኹ፡እውነትም፡ሐራነት፡ያወጣችዃል፡አላቸው። 33፤እነርሱም፡መልሰው፦የአብርሃም፡ዘር፡ነን፡ለአንድም፡ስንኳ፡ከቶ፡ባሪያዎች፡ አልኾንም፤አንተ፦ሐራነት፡ትወጣላችኹ፡እንዴት፡ትላለኽ፧አሉት። 34፤ኢየሱስ፡መለሰ፥እንዲህ፡ሲል፦እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥ኀጢአት፡የሚያደርግ፡ዅሉ፡የኀጢአት፡ ባሪያ፡ነው። 35፤ባሪያም፡ለዘለዓለም፡በቤት፡አይኖርም፤ልጁ፡ለዘለዓለም፡ይኖራል። 36፤እንግዲህ፡ልጁ፡ሐራነት፡ቢያወጣችኹ፡በእውነት፡ሐራነት፡ትወጣላችኹ። 37፤የአብርሃም፡ዘር፡መኾናችኹንስ፡ዐውቃለኹ፥ነገር፡ግን፥ቃሌ፡በእናንተ፡አይኖርምና፡ልትገድሉኝ፡ ትፈልጋላችኹ። 38፤እኔ፡በአባቴ፡ዘንድ፡ያየኹትን፡እናገራለኹ፤እናንተም፡ደግሞ፡በአባታችኹ፡ዘንድ፡ያያችኹትን፡ ታደርጋላችኹ። 39፤መልሰውም፦አባታችንስ፡አብርሃም፡ነው፡አሉት።ኢየሱስም፦የአብርሃም፡ልጆች፡ብትኾኑ፡የአብርሃምን፡ ሥራ፡ባደረጋችኹ፡ነበር። 40፤ነገር፡ግን፥አኹን፡ከእግዚአብሔር፡የሰማኹትን፡እውነት፡የነገርዃችኹን፡ሰው፡ልትገድሉኝ፡ ትፈልጋላችኹ፤አብርሃም፡እንዲህ፡አላደረገም። 41፤እናንተ፡የአባታችኹን፡ሥራ፡ታደርጋላችኹ፡አላቸው፦እኛስ፡ከዝሙት፡አልተወለድንም፤አንድ፡አባት፡አለን፥ርሱም፡እግዚአብሔር፡ነው፡አሉት። 42፤ኢየሱስም፡አላቸው፦እግዚአብሔርስ፡አባታችኹ፡ከኾነ፡በወደዳችኹኝ፡ነበር፤እኔ፡ከእግዚአብሔር፡ ወጥቼ፡መጥቻለኹና፤ርሱ፡ላከኝ፡እንጂ፡ከራሴ፡አልመጣኹምና። 43፤ንግግሬን፡የማታስተውሉ፡ስለ፡ምንድር፡ነው፧ቃሌን፡ልትሰሙ፡ስለማትችሉ፡ነው። 44፤እናንተ፡ከአባታችኹ፡ከዲያብሎስ፡ናችኹ፡የአባታችኹንም፡ምኞት፡ልታደርጉ፡ትወዳላችኹ።ርሱ፡ ከመዠመሪያ፡ነፍሰ፡ገዳይ፡ነበረ፤እውነትም፡በርሱ፡ስለሌለ፡በእውነት፡አልቆመም።ሐሰትን፡ሲናገር፡ከራሱ፡ ይናገራል፥ሐሰተኛ፡የሐሰትም፡አባት፡ነውና። 45፤እኔ፡ግን፡እውነትን፡የምናገር፡ስለ፡ኾንኹ፡አታምኑኝም። 46፤ከእናንተ፡ስለ፡ኀጢአት፡የሚወቅሰኝ፡ማን፡ነው፧እውነት፡የምናገር፡ከኾንኹ፡እናንተ፡ስለ፡ምን፡ አታምኑኝም፧ 47፤ከእግዚአብሔር፡የኾነ፡የእግዚአብሔርን፡ቃል፡ይሰማል፤እናንተ፡ከእግዚአብሔር፡አይደላችኹምና፡ስለዚህ፡ አትሰሙም። 48፤አይሁድ፡መልሰው፦ሳምራዊ፡እንደ፡ኾንኽ፡ጋኔንም፡እንዳለብኽ፡በማለታችን፡እኛ፡መልካም፡እንል፡ የለምን፧አሉት። 49፤ኢየሱስም፡መለሰ፥እንዲህ፡ሲል፦እኔስ፡ጋኔን፡የለብኝም፥ነገር፡ግን፥አባቴን፡አከብራለኹ፡እናንተም፡ ታዋርዱኛላችኹ። 50፤እኔ፡ግን፡የራሴን፡ክብር፡አልፈልግም፤የሚፈልግ፡የሚፈርድም፡አለ። 51፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥ቃሌን፡የሚጠብቅ፡ቢኖር፡ለዘለዓለም፡ሞትን፡አያይም። 52፤አይሁድ፦ጋኔን፡እንዳለብኽ፡አኹን፡ዐወቅን።አብርሃም፡ስንኳ፡ሞተ፥ነቢያትም፤አንተም፦ቃሌን፡ የሚጠብቅ፡ቢኖር፡ለዘለዓለም፡ሞትን፡አይቀምስም፡ትላለኽ። 53፤በእውኑ፡አንተ፡ከሞተው፡ከአባታችን፡ከአብርሃም፡ትበልጣለኽን፧ነቢያትም፡ሞቱ፤ራስኽን፡ማንን፡ ታደርጋለኽ፧አሉት። 54፤ኢየሱስም፡መለሰ፥አለም፦እኔ፡ራሴን፡ባከብር፡ክብሬ፡ከንቱ፡ነው፤የሚያከብረኝ፡እናንተ፡አምላካችን፡ የምትሉት፡አባቴ፡ነው፤ 55፤አላወቃችኹትምም፥እኔ፡ግን፡ዐውቀዋለኹ።አላውቀውም፡ብል፡እንደናንተ፡ሐሰተኛ፡በኾንኹ፤ዳሩ፡ግን፡ ዐውቀዋለኹ፡ቃሉንም፡እጠብቃለኹ። 56፤አባታችኹ፡አብርሃም፡ቀኔን፡ያይ፡ዘንድ፡ሐሤት፡አደረገ፥አየም፡ደስም፡አለው። 57፤አይሁድም፦ገና፡ዐምሳ፡ዓመት፡ያልኾነኽ፡አብርሃምን፡አይተኻልን፧አሉት። 58፤ኢየሱስም፦እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥አብርሃም፡ሳይወለድ፡እኔ፡አለኹ፡አላቸው። 59፤ስለዚህ፥ሊወግሩት፡ድንጋይ፡አነሡ፤ኢየሱስ፡ግን፡ተሰወራቸው፥ከመቅደስም፡ወጥቶ፡በመካከላቸው፡ዐልፎ፡ኼደ።

ምዕራፍ ፱ ለማስተካከል

 1፤ሲያልፍም፡ከመወለዱ፡ዠምሮ፡ዕውር፡የኾነውን፡ሰው፡አየ። 2፤ደቀ፡መዛሙርቱም፦መምህር፡ሆይ፥ይህ፡ሰው፡ዕውር፡ኾኖ፡እንዲወለድ፡ኀጢአት፡የሠራ፡ማን፡ ነው፧ርሱ፡ወይስ፡ወላጆቹ፧ብለው፡ጠየቁት። 3፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡ብሎ፡መለሰ፦የእግዚአብሔር፡ሥራ፡በርሱ፡እንዲገለጥ፡ነው፡እንጂ፡ርሱ፡ወይም፡ ወላጆቹ፡ኀጢአት፡አልሠሩም። 4፤ቀን፡ሳለ፡የላከኝን፡ሥራ፡ላደርግ፡ይገ፟ባ፟ኛል፤ማንም፡ሊሠራ፡የማይችልባት፡ሌሊት፡ትመጣለች። 5፤በዓለም፡ሳለኹ፡የዓለም፡ብርሃን፡ነኝ። 6፤ይህን፡ብሎ፡ወደ፡መሬት፡እንትፍ፡አለ፡በምራቁም፡ጭቃ፡አድርጎ፡በጭቃው፡የዕውሩን፡ዐይኖች፡ቀባና፦ 7፤ኺድና፡በሰሊሖም፡መጠመቂያ፡ታጠብ፡አለው፤(ትርጓሜው፡'የተላከ'፡ነው)።ስለዚህ፡ኼዶ፡ ታጠበ፥እያየም፡መጣ። 8፤ጎረቤቶቹም፡ቀድሞም፡ሲለምን፡አይተውት፡የነበሩ፦ይህ፡ተቀምጦ፡ይለምን፡የነበረ፡አይደለምን፧አሉ። 9፤ሌላዎች፦ርሱ፡ነው፡አሉ፤ሌላዎች፦አይደለም፡ርሱን፡ይመስላል፡እንጂ፡አሉ፤ርሱ፦እኔ፡ነኝ፡አለ። 10፤ታድያ፦ዐይኖችኽ፡እንዴት፡ተከፈቱ፧አሉት። 11፤ርሱ፡መልሶ፦ኢየሱስ፡የሚባለው፡ሰው፡ጭቃ፡አድርጎ፡አይኖቼን፡ቀባና፦ወደሰሊሖም፡መጠመቂያ፡ ኼደኽ፡ታጠብ፡አለኝ፤ኼጄ፡ታጥቤም፡አየኹ፡አለ። 12፤ያ፡ሰው፡ወዴት፡ነው፧አሉት፦አላውቅም፡አለ። 13፤በፊት፡ዕውር፡የነበረውን፡ሰው፡ወደ፡ፈሪሳውያን፡ወሰዱት። 14፤ኢየሱስም፡ጭቃ፡አድርጎ፡ዐይኖቹን፡የከፈተበት፡ቀን፡ሰንበት፡ነበረ። 15፤ስለዚህ፥ፈሪሳውያን፡ደግሞ፡እንዴት፡እንዳየ፡እንደ፡ገና፡ጠየቁት።ርሱም፦ጭቃ፡በዐይኖቼ፡ አኖረ፥ታጠብኹም፥አያለኹም፡አላቸው። 16፤ከፈሪሳውያንም፡አንዳንዶቹ፦ይህ፡ሰው፡ሰንበትን፡አያከብርምና፡ከእግዚአብሔር፡አይደለም፡አሉ።ሌላዎች፡ ግን፦ኀጢአትኛ፡ሰው፡እንደነዚህ፡ያሉ፡ምልክቶች፡ሊያደርግ፡እንዴት፡ይችላል፧አሉ። 17፤በመካከላቸውም፡መለያየት፡ኾነ።ከዚህም፡የተነሣ፡ዕውሩን፦አንተ፡ዐይኖችኽን፡ስለከፈተ፡ስለ፡ርሱ፡ ምን፡ትላለኽ፧ደግሞ፡አሉት።ርሱም፦ነቢይ፡ነው፡አለ። 18፤አይሁድ፡የዚያን፡ያየውን፡ወላጆች፡እስኪጠሩ፡ድረስ፡ዕውር፡እንደ፡ነበረ፡እንዳየም፡ስለ፡ርሱ፡ አላመኑም፥ 19፤እነርሱንም፦እናንተ፡ዕውር፡ኾኖ፡ተወለደ፡የምትሉት፡ልጃችኹ፡ይህ፡ነውን፧ታድያ፡አኹን፡እንዴት፡ ያያል፧ብለው፡ጠየቋቸው። 20፤ወላጆቹም፡መልሰው፦ይህ፡ልጃችን፡እንደ፡ኾነ፡ዕውርም፡ኾኖ፡እንደ፡ተወለደ፡እናውቃለን፤ 21፤ዳሩ፡ግን፡አኹን፡እንዴት፡እንዳየ፡አናውቅም፥ወይም፡ዐይኖቹን፡ማን፡እንደ፡ከፈተ፡እኛ፡ አናውቅም፤ጠይቁት፡ርሱ፡ሙሉ፡ሰው፡ነው፤ርሱ፡ስለ፡ራሱ፡ይናገራል፡አሉ። 22፤ወላጆቹ፡አይሁድን፡ስለ፡ፈሩ፡ይህን፡አሉ፤ርሱ፡ክርስቶስ፡ነው፡ብሎ፡የሚመሰክር፡ቢኖር፡ከምኵራብ፡ እንዲያወጡት፡አይሁድ፡ከዚህ፡በፊት፡ተስማምተው፡ነበርና። 23፤ስለዚህ፥ወላጆቹ፦ሙሉ፡ሰው፡ነው፥ጠይቁት፡አሉ። 24፤ስለዚህ፥ዕውር፡የነበረውን፡ሰው፡ኹለተኛ፡ጠርተው፦እግዚአብሔርን፡አክብር፤ይህ፡ሰው፡ኀጢአተኛ፡ መኾኑን፡እኛ፡እናውቃለን፡አሉት። 25፤ርሱም፡መልሶ፦ኀጢአተኛ፡መኾኑን፡አላውቅም፤ዕውር፡እንደ፡ነበርኹ፡አኹንም፡እንዳይ፡ይህን፡አንድ፡ ነገር፡ዐውቃለኹ፡አለ። 26፤ደግመውም፦ምን፡አደረገልኽ፧እንዴትስ፡ዐይኖችኽን፡ከፈተ፧አሉት። 27፤ርሱም፡መልሶ፦አስቀድሜ፡ነገርዃችኹ፡አልሰማችኹምም፤ስለ፡ምን፡ዳግመኛ፡ልትሰሙ፡ ትወዳላችኹ፧እናንተ፡ደግሞ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ልትኾኑ፡ትወዳላችኹን፧አላቸው። 28፤ተሳድበውም፦አንተ፡የርሱ፡ደቀ፡መዝሙር፡ነኽ፥እኛ፡ግን፡የሙሴ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ነን፤ 29፤እግዚአብሔር፡ሙሴን፡እንደ፡ተናገረው፡እኛ፡እናውቃለን፥ይህ፡ሰው፡ግን፡ከወዴት፡እንደ፡ኾነ፡ አናውቅም፡አሉት። 30፤ሰውዬው፡መለሰ፡እንዲህም፡አላቸው፦ከወዴት፡እንደ፡ኾነ፡እናንተ፡አለማወቃችኹ፡ይህ፡ድንቅ፡ነገር፡ነው፥ዳሩ፡ግን፡ዐይኖቼን፡ከፈተ። 31፤እግዚአብሔርን፡የሚፈራ፡ፈቃዱንም፡የሚያደርግ፡ቢኖር፡ያንን፡እግዚአብሔር፡ይሰማዋል፡እንጂ፡ ኀጢአተኛዎችን፡እንዳይሰማ፡እናውቃለን። 32፤ዕውር፡ኾኖ፡የተወለደውን፡ዐይኖች፡ማንም፡እንደ፡ከፈተ፡ዓለም፡ከተፈጠረ፡ዠምሮ፡አልተሰማም፤ 33፤ይህ፡ሰው፡ከእግዚአብሔር፡ባይኾን፡ምንም፡ሊያደርግ፡ባልቻለም፡ነበር። 34፤መልሰው፦አንተ፡ዅለንተናኽ፡በኀጢአት፡ተወለድኽ፥አንተም፡እኛን፡ታስተምረናለኽን፧አሉት።ወደ፡ ውጭም፡አወጡት። 35፤ኢየሱስም፡ወደ፡ውጭ፡እንዳወጡት፡ሰማ፤ሲያገኘውም፦አንተ፡በእግዚአብሔር፡ልጅ፡ ታምናለኽን፧አለው። 36፤ርሱም፡መልሶ፦ጌታ፡ሆይ፥በርሱ፡አምን፡ዘንድ፡ማን፡ነው፧አለ። 37፤ኢየሱስም፦አይተኸዋልም፡ከአንተ፡ጋራም፡የሚናገረው፡ርሱ፡ነው፡አለው። 38፤ርሱም፦ጌታ፡ሆይ፥አምናለኹ፡አለ፤ሰገደለትም። 39፤ኢየሱስም፦የማያዩ፡እንዲያዩ፡የሚያዩም፡እንዲታወሩ፡እኔ፡ወደዚህ፡ዓለም፡ለፍርድ፡መጣኹ፡አለ። 40፤ከፈሪሳውያንም፡ከርሱ፡ጋራ፡የነበሩት፡ይህን፡ሰምተው፦እኛ፡ደግሞ፡ዕውሮች፡ነንን፧አሉት። 41፤ኢየሱስም፡አላቸው፦ዕውሮችስ፡ብትኾኑ፡ኀጢአት፡ባልኾነባችኹም፡ነበር፤አኹን፡ግን፦እናያለን፡ ትላላችኹ፤ኀጢአታችኹ፡ይኖራል።

ምዕራፍ ፲ ለማስተካከል

 1፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥ወደበጎች፡በረት፡በበሩ፡የማይገባ፡በሌላ፡መንገድ፡ግን፡የሚወጣ፡ርሱ፡ ሌባ፡ወንበዴም፡ነው፤ 2፤በበሩ፡የሚገባ፡ግን፡የበጎች፡እረኛ፡ነው። 3፤ለርሱ፡በረኛው፡ይከፍትለታል፤በጎቹም፡ድምፁን፡ይሰሙታል፥የራሱንም፡በጎች፡በየስማቸው፡ጠርቶ፡ ይወስዳቸዋል። 4፤የራሱንም፡ዅሉ፡ካወጣቸ4፤የራሱንም፡ዅሉ፡ካወጣቸው፡በዃላ፡በፊታቸው፡ይኼዳል፥በጎቹም፡ድምፁን፡ያውቃሉና፡ይከተሉታል፤ 5፤ከሌላው፡ግን፡ይሸሻሉ፡እንጂ፡አይከተሉትም፥የሌላዎችን፡ድምፅ፡አያውቁምና። 6፤ኢየሱስ፡ይህን፡ምሳሌ፡ነገራቸው፤እነርሱ፡ግን፡የነገራቸው፡ምን፡እንደ፡ኾነ፡አላስተዋሉም። 7፤ኢየሱስም፡ደግሞ፡አላቸው፦እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥እኔ፡የበጎች፡በር፡ነኝ። 8፤ከእኔ፡በፊት፡የመጡ፡ዅሉ፡ሌባዎችና፡ወንበዴዎች፡ናቸው፤ዳሩ፡ግን፡በጎቹ፡አልሰሟቸውም። 9፤በሩ፡እኔ፡ነኝ፤በእኔ፡የሚገባ፡ቢኖር፡ይድናል፥ይገባልም፡ይወጣልም፡መሰማሪያም፡ያገኛል። 10፤ሌባው፡ሊሰርቅና፡ሊያርድ፡ሊያጠፋም፡እንጂ፡ስለ፡ሌላ፡አይመጣም፤እኔ፡ሕይወት፡እንዲኾንላቸው፡ እንዲበዛላቸውም፡መጣኹ። 11፤መልካም፡እረኛ፡እኔ፡ነኝ።መልካም፡እረኛ፡ነፍሱን፡ስለ፡በጎቹ፡ያኖራል። 12፤እረኛ፡ያልኾነው፡በጎቹም፡የርሱ፡ያልኾኑ፡ሞያተኛ፡ግን፥ተኵላ፡ሲመጣ፡ባየ፡ጊዜ፥በጎቹን፡ትቶ፡ ይሸሻል፤ተኵላም፡ይነጥቃቸዋል፡በጎቹንም፡ይበትናቸዋል። 13፤ሞያተኛ፡ስለ፡ኾነ፡ለበጎቹም፡ስለማይገደው፡ሞያተኛው፡ይሸሻል። 14-15፤መልካም፡እረኛ፡እኔ፡ነኝ፥አብም፡እንደሚያውቀኝ፡እኔም፡አብን፡እንደማውቀው፡የራሴን፡በጎች፡ ዐውቃለኹ፡የራሴም፡በጎች፡ያውቁኛል፤ነፍሴንም፡ስለ፡በጎች፡አኖራለኹ። 16፤ከዚህም፡በረት፡ያልኾኑ፡ሌላዎች፡በጎች፡አሉኝ፤እነርሱን፡ደግሞ፡ላመጣ፡ይገ፟ባ፟ኛል፥ድምፄንም፡ ይሰማሉ፥አንድም፡መንጋ፡ይኾናሉ፥እረኛውም፡አንድ። 17፤ነፍሴን፡ደግሞ፡አነሣት፡ዘንድ፡አኖራለኹና፡ስለዚህ፡አብ፡ይወደኛል። 18፤እኔ፡በፈቃዴ፡አኖራታለኹ፡እንጂ፡ከእኔ፡ማንም፡አይወስዳትም።ላኖራት፡ሥልጣን፡አለኝ፡ደግሞም፡ ላነሣት፡ሥልጣን፡አለኝ፡ይህችን፡ትእዛዝ፡ከአባቴ፡ተቀበልኹ። 19፤እንግዲህ፡ከዚህ፡ቃል፡የተነሣ፡በአይሁድ፡መካከል፡እንደ፡ገና፡መለያየት፡ኾነ። 20፤ከነርሱም፡ብዙዎች፦ጋኔን፡አለበት፡አብዷልም፤ስለ፡ምንስ፡ትሰሙታላችኹ፧አሉ። 21፤ሌላዎችም፦ይህ፡ጋኔን፡ያለበት፡ሰው፡ቃል፡አይደለም፤ጋኔን፡የዕውሮችን፡ዐይኖች፡ሊከፍት፡ ይችላልን፧አሉ። 22፤በኢየሩሳሌምም፡የመቅደስ፡መታደስ፡በዓል፡ኾነ፤ 23፤ክረምትም፡ነበረ።ኢየሱስም፡በመቅደስ፡በሰሎሞን፡ደጅ፡መመላለሻ፡ይመላለስ፡ነበር። 24፤አይሁድም፡ርሱን፡ከበ፟ው፦እስከ፡መቼ፡ድረስ፡በጥርጣሪ፡ታቈየናለኽ፧አንተ፡ክርስቶስ፡እንደ፡ኾንኽ፡ ገልጠኽ፡ንገረን፡አሉት። 25፤ኢየሱስም፡መለሰላቸው፥እንዲህ፡ሲል፦ነገርዃችኹ፡አታምኑምም፡እኔ፡በአባቴ፡ስም፡የማደርገው፡ሥራ፡ ይህ፡ስለ፡እኔ፡ይመሰክራል፤26፤እናንተ፡ግን፡እንደ፡ነገርዃችኹ፡ከበጎቼ፡ስላልኾናችኹ፡አታምኑም። 27፤በጎቼ፡ድምፄን፡ይሰማሉ፡እኔም፡ዐውቃቸዋለኹ፡ይከተሉኝማል፤ 28፤እኔም፡የዘለዓለም፡ሕይወትን፡እሰጣቸዋለኹ፥ለዘለዓለምም፡አይጠፉም፥ከእጄም፡ማንም፡አይነጥቃቸውም። 29፤የሰጠኝ፡አባቴ፡ከዅሉ፡ይበልጣል፥ከአባቴም፡እጅ፡ሊነጥቃቸው፡ማንም፡አይችልም። 30፤እኔና፡አብ፡አንድ፡ነን። 31፤አይሁድ፡ሊወግሩት፡ደግመው፡ድንጋይ፡አነሡ። 32፤ኢየሱስ፦ከአባቴ፡ብዙ፡መልካም፡ሥራ፡አሳየዃችኹ፤ከነርሱ፡ስለ፡ማናቸው፡ሥራ፡ትወግሩኛላችኹ፧ብሎ፡መለሰላቸው። 33፤አይሁድም፦ስለ፡መልካም፡ሥራ፡አንወግርኽም፤ስለ፡ስድብ፤አንተም፡ሰው፡ስትኾን፡ራስኽን፡አምላክ፡ ስለ፡ማድረግኽ፡ነው፡እንጂ፡ብለው፡መለሱለት። 34፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡ብሎ፡መለሰላቸው፦እኔ፦አማልክት፡ናችኹ፡አልኹ፡ተብሎ፡በሕጋችኹ፡የተጻፈ፡ አይደለምን፧ 35፤መጽሐፉ፡ሊሻር፡አይቻልምና፡እነዚያን፡የእግዚአብሔር፡ቃል፡የመጣላቸውን፡አማልክት፡ካላቸው፥ 36፤የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ነኝ፡ስላልኹ፡እናንተ፡አብ፡የቀደሰውን፡ወደ፡ዓለምም፡የላከውን፦ትሳደባለኽ፡ ትሉታላችኹን፧ 37፤እኔ፡የአባቴን፡ሥራ፡ባላደርግ፡አትመኑኝ፤ 38፤ባደርገው፡ግን፥እኔን፡ስንኳ፡ባታምኑ፡አብ፡በእኔ፡እንደ፡ኾነ፡እኔም፡በአብ፡እንደ፡ኾንኹ፡ታውቁና፡ ታስተውሉ፡ዘንድ፡ሥራውን፡እመኑ። 39፤እንግዲህ፡ደግመው፡ሊይዙት፡ፈለጉ፤ከእጃቸውም፡ወጣ። 40፤ዮሐንስም፡በመዠመሪያ፡ያጠምቅበት፡ወደነበረው፡ስፍራ፡ወደዮርዳኖስ፡ማዶ፡እንደ፡ገና፡ኼደ፡በዚያም፡ ኖረ። 41፤ብዙ፡ሰዎችም፡ወደ፡ርሱ፡መጥተው፦ዮሐንስ፡አንድ፡ምልክት፡ስንኳ፡አላደረገም፥ነገር፡ግን፥ዮሐንስ፡ ስለዚህ፡ሰው፡የተናገረው፡ዅሉ፡እውነት፡ነበረ፡አሉ። 42፤በዚያም፡ብዙዎች፡በርሱ፡አመኑ።

ምዕራፍ ፲፩ ለማስተካከል

 1፤ከማርያምና፡ከእኅቷ፡ከማርታ፡መንደር፡ከቢታንያ፡የኾነ፡አልዓዛር፡የሚባል፡አንድ፡ሰው፡ታሞ፡ነበር። 2፤ማርያምም፡ጌታን፡ሽቱ፡የቀባችው፡እግሩንም፡በጠጕሯ፡ያበሰችው፡ነበረች፤ወንድሟም፡አልዓዛር፡ታሞ፡ ነበር። 3፤ስለዚህ፥እኅቶቹ፦ጌታ፡ሆይ፥እንሆ፥የምትወደ፟ው፡ታሟል፡ብለው፡ወደ፡ርሱ፡ላኩ። 4፤ኢየሱስም፡ሰምቶ፦ይህ፡ሕመም፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡በርሱ፡ይከብር፡ዘንድ፡ስለእግዚአብሔር፡ክብር፡ ነው፡እንጂ፡ለሞት፡አይደለም፡አለ። 5፤ኢየሱስም፡ማርታንና፡እኅቷን፡አልዓዛርንም፡ይወድ፡ነበር። 6፤እንደ፡ታመመም፡በሰማ፡ጊዜ፡ያን፡ጊዜ፡በነበረበት፡ስፍራ፡ኹለት፡ቀን፡ዋለ፤ 7፤ከዚህም፡በዃላ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፦ወደ፡ይሁዳ፡ደግሞ፡እንኺድ፡አላቸው። 8፤ደቀ፡መዛሙርቱ፦መምህር፡ሆይ፥አይሁድ፡ከጥቂት፡ጊዜ፡በፊት፡ሊወግሩኽ፡ይፈልጉ፡ነበር፥ደግሞም፡ ወደዚያ፡ትኼዳለኽን፧አሉት። 9፤ኢየሱስም፡መልሶ፦ቀኑ፡ዐሥራ፡ኹለት፡ሰዓት፡አይደለምን፧በቀን፡የሚመላለስ፡ቢኖር፡የዚህን፡ዓለም፡ ብርሃን፡ያያልና፥አይሰናከልም፤ 10፤በሌሊት፡የሚመላለስ፡ቢኖር፡ግን፡ብርሃን፡በርሱ፡ስለሌለ፡ይሰናከላል፡አላቸው። 11፤ይህን፡ተናገረ፤ከዚህም፡በዃላ፦ወዳጃችን፡አልዓዛር፡ተኝቷል፤ነገር፡ግን፥ከእንቅልፉ፡ላስነሣው፡ እኼዳለኹ፡አላቸው። 12፤እንግዲህ፡ደቀ፡መዛሙርቱ፦ጌታ፡ሆይ፥ተኝቶስ፡እንደ፡ኾነ፡ይድናል፡አሉት። 13፤ኢየሱስስ፡ስለ፡ሞቱ፡ተናግሮ፡ነበር፤እነርሱ፡ግን፡ስለ፡እንቅልፍ፡መተኛት፡እንደ፡ተናገረ፡መሰላቸው። 14፤እንግዲህ፡ያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡በግልጥ፦አልዓዛር፡ሞተ፤ 15፤እንድታምኑም፡በዚያ፡ባለመኖሬ፡ስለ፡እናንተ፡ደስ፡ይለኛል፤ነገር፡ግን፥ወደ፡ርሱ፡እንኺድ፡አላቸው። 16፤ስለዚህ፥ዲዲሞስ፡የሚሉት፡ቶማስ፥ለባልንጀራዎቹ፣ለደቀ፡መዛሙርት፦ከርሱ፡ጋራ፡እንሞት፡ዘንድ፡ እኛ፡ደግሞ፡እንኺድ፡አለ። 17፤ኢየሱስም፡በመጣ፡ጊዜ፡በመቃብር፡እስከ፡አኹን፡አራት፡ቀን፡ኾኖት፡አገኘው። 18፤ቢታንያም፡ዐሥራ፡ዐምስት፡ምዕራፍ፡ያኽል፡ለኢየሩሳሌም፡ቅርብ፡ነበረች። 19፤ከአይሁድም፡ብዙዎች፡ስለ፡ወንድማቸው፡ሊያጽናኗቸው፡ወደ፡ማርታና፡ወደ፡ማርያም፡መጥተው፡ነበር። 20፤ማርታም፡ኢየሱስ፡እንደ፡መጣ፡በሰማች፡ጊዜ፡ልትቀበለው፡ወጣች፤ማርያም፡ግን፡በቤት፡ተቀምጣ፡ነበር። 21፤ማርታም፡ኢየሱስን፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡በዚህ፡ኖረኽ፡ብትኾን፡ወንድሜ፡ባልሞተም፡ነበር፤ 22፤አኹንም፡ከእግዚአብሔር የምትለምነውን፡ዅሉ፡እግዚአብሔር፡እንዲሰጥኽ፡ዐውቃለኹ፡አለችው። 23፤ኢየሱስም፦ወንድምሽ፡ይነሣል፡አላት። 24፤ማርታም፦በመጨረሻው፡ቀን፡በትንሣኤ፡እንዲነሣ፡ዐውቃለኹ፡አለችው። 25፤ኢየሱስም፦ትንሣኤና፡ሕይወት፡እኔ፡ነኝ፤የሚያምንብኝ፡ቢሞት፡እንኳ፡ሕያው፡ይኾናል፤ 26፤ሕያው፡የኾነም፡የሚያምንብኝም፡ዅሉ፡ለዘለዓለም፡አይሞትም፤ይህን፡ታምኚያለሽን፧አላት። 27፤ርሷም፦አዎን፡ጌታ፡ሆይ፤አንተ፡ወደ፡ዓለም፡የሚመጣው፡ክርስቶስ፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡እንደ፡ ኾንኽ፡እኔ፡አምናለኹ፡አለችው። 28፤ይህንም፡ብላ፡ኼደች፥እኅቷንም፡ማርያምን፡በስውር፡ጠርታ፦መምህሩ፡መጥቷል፡ይጠራሽማል፡ አለቻት። 29፤ርሷም፡በሰማች፡ጊዜ፡ፈጥና፡ተነሣች፡ወደ፡ርሱም፡መጣች፤ 30፤ኢየሱስም፡ማርታ፡በተቀበለችበት፡ስፍራ፡ነበረ፡እንጂ፡ገና፡ወደ፡መንደሩ፡አልገባም፡ነበር። 31፤ሲያጽናኗት፡ከርሷ፡ጋራ፡በቤት፡የነበሩ፡አይሁድም፡ማርያም፡ፈጥና፡እንደ፡ተነሣችና፡እንደ፡ወጣች፡ባዩ፡ ጊዜ፥ወደ፡መቃብር፡ኼዳ፡በዚያ፡ልታለቅስ፡መስሏቸው፡ተከተሏት። 32፤ማርያምም፡ኢየሱስ፡ወዳለበት፡መጥታ፡ባየችው፡ጊዜ፡በእግሩ፡ላይ፡ወድቃ፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡በዚህ፡ ኖረኽ፡ብትኾን፡ወንድሜ፡ባልሞተም፡ነበር፡አለችው። 33፤ኢየሱስም፡ርሷ፡ስታለቅስ፡ከርሷም፡ጋራ፡የመጡት፡አይሁድ፡ሲያለቅሱ፡አይቶ፡በመንፈሱ፡ዐዘነ፡በራሱም፡ ታወከ፤ 34፤ወዴት፡አኖራችኹት፧አለም።እነርሱም፦ ጌታ፡ሆይ፥መጥተኽ፡እይ፡አሉት። 35፤ኢየሱስም፡እንባውን፡አፈሰሰ። 36፤ስለዚህ፥አይሁድ፦እንዴት፡ይወደ፟ው፡እንደ፡ነበረ፡እዩ፡አሉ። 37፤ከነርሱ፡ግን፡አንዳንዶቹ፦ይህ፡የዕውሩን፡ዐይኖች፡የከፈተ፡ይህን፡ደግሞ፡እንዳይሞት፡ያደርግ፡ዘንድ፡ ባልቻለም፡ነበርን፧አሉ። 38፤ኢየሱስም፡በራሱ፡ዐዝኖ፡ወደ፡መቃብሩ፡መጣ፤ርሱም፡ዋሻ፡ነበረ፤ድንጋይም፡ተገጥሞበት፡ነበር። 39፤ኢየሱስ፦ድንጋዩን፡አንሡ፡አለ።የሞተውም፡እኅት፡ማርታ፦ጌታ፡ሆይ፥ከሞተ፡አራት፡ቀን፡ኾኖታልና፥አኹን፡ይሸታል፡አለችው። 40፤ኢየሱስ፦ብታምኚስ፡የእግዚአብሔርን፡ክብር፡እንድታዪ፡አልነገርኹሽምን፧አላት። 41፤ድንጋዩንም፡አነሡት።ኢየሱስም፡ዐይኖቹን፡ወደ፡ላይ፡አንሥቶ፦አባት፡ሆይ፥ስለ፡ሰማኸኝ፡ አመሰግንኻለኹ። 42፤ዅልጊዜም፡እንድትሰማኝ፡ዐወቅኹ፤ነገር፡ግን፥አንተ፡እንደ፡ላክኸኝ፡ያምኑ፡ዘንድ፡በዚህ፡ዙሪያ፡ስለቆሙት፡ሕዝብ፡ተናገርኹ፡አለ። 43፤ይህንም፡ብሎ፡በታላቅ፡ድምፅ፦አልዓዛር፡ሆይ፥ወደ፡ውጭ፡ና፡ብሎ፡ጮኸ። 44፤የሞተውም፡እጆቹና፡እግሮቹ፡በመግነዝ፡እንደ፡ተገነዙ፡ወጣ፤ፈቱም፡በጨርቅ፡እንደ፡ተጠመጠመ፡ ነበር።ኢየሱስም፦ፍቱትና፡ይኺድ፡ተዉት፡አላቸው። 45፤ስለዚህ፥ወደ፡ማርያም፡ከመጡት፥ኢየሱስም፡ያደረገውን፡ካዩት፡ከአይሁድ፡ብዙዎች፡በርሱ፡አመኑ፤ 46፤ከነርሱ፡አንዳንዶቹ፡ግን፡ወደ፡ፈሪሳውያን፡ኼደው፡ኢየሱስ፡ያደረገውን፡ነገሯቸው። 47፤እንግዲህ፡የካህናት፡አለቃዎችና፡ፈሪሳውያን፡ሸንጎ፡ሰብስበው፦ምን፡እናድርግ፧ይህ፡ሰው፡ብዙ፡ ምልክቶች፡ያደርጋልና። 48፤እንዲሁ፡ብንተወው፡ዅሉ፡በርሱ፡ያምናሉ፤የሮሜም፡ሰዎች፡መጥተው፡አገራችንን፡ወገናችንንም፡ ይወስዳሉ፡አሉ። 49፤በዚያችም፡ዓመት፡ሊቀ፡ካህናት፡የነበረ፡ቀያፋ፡የሚሉት፡ከነርሱ፡አንዱ፦እናንተ፡ምንም፡አታውቁም፤ 50፤ሕዝቡም፡ዅሉ፡ከሚጠፋ፡አንድ፡ሰው፡ስለ፡ሕዝቡ፡ይሞት፡ዘንድ፡እንዲሻለን፡አታስቡም፡አላቸው። 51፤ይህንም፡የተናገረ፡ከራሱ፡አይደለም፥ነገር፡ግን፥በዚያች፡ዓመት፡ሊቀ፡ካህናት፡ነበረና፡ኢየሱስ፡ስለ፡ ሕዝቡ፡ሊሞት፡እንዳለው፡ትንቢት፡ተናገረ፤ 52፤ስለ፡ሕዝቡም፡ዅሉ፡አይደለም፥ነገር፡ግን፥የተበተኑትን፡የእግዚአብሔርን፡ልጆች፡ደግሞ፡በአንድነት፡ እንዲሰበስባቸው፡ነው፡እንጂ። 53፤እንግዲህ፡ከዚያ፡ቀን፡ዠምረው፡ሊገድሉት፡ተማከሩ። 54፤ከዚያ፡ወዲያም፡ኢየሱስ፡በአይሁድ፡መካከል፡ተገልጦ፡አልተመላለሰም፤ነገር፡ግን፥ከዚያ፡በምድረ፡በዳ፡ አጠገብ፡ወዳለች፡ምድር፥ኤፍሬም፡ወደምትባል፡ከተማ፡ኼደ፤በዚያም፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡ተቀመጠ። 55፤የአይሁድም፡ፋሲካ፡ቀርቦ፡ነበር።ብዙ፡ሰዎችም፡ራሳቸውን፡ያነጹ፡ዘንድ፡ከፋሲካ፡በፊት፡ከአገሩ፡ወደ፡ ኢየሩሳሌም፡ወጡ። 56፤ኢየሱስንም፡ይፈልጉት፡ነበር፤በመቅደስም፡ቆመው፡ርስ፡በርሳቸው፦ምን፡ይመስላችዃል፧ወደ፡በዓሉ፡ አይመጣም፡ይኾንን፧ተባባሉ። 57፤የካህናት፡አለቃዎችም፡ፈሪሳውያንም፡ይይዙት፡ዘንድ፥ርሱ፡ያለበትን፡ስፍራ፡የሚያውቀው፡ሰው፡ቢኖር፡ እንዲያመለክታቸው፡አዘ፟ው፡ነበር።

ምዕራፍ ፲፪ ለማስተካከል

1፣ከፋሲካም በፊት በስድስተኛው ቀን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ። 2፣በዚያም እራት አደረጉለት፤ ማርታም ታገለግል ነበር፤ አልዓዛር ግን ከእርሱ ጋር ከተቀመጡት አንዱ ነበረ። 3፣ማርያምም ዋጋው እጅግ የከበረ የጥሩ ናርዶስ ሽቱ ንጥር ወስዳ የኢየሱስን እግር ቀባች፤ በጠጕርዋም እግሩን አበሰች፤ ቤቱም ከናርዶስ ሽቱ ሞላ። 4፣ነገር ግን ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ አሳልፎ ሊሰጠው ያለው የስምዖን ልጅ የአስቆሮቱ ይሁዳ፦ 5፣ይህ ሽቱ ለሦስት መቶ ዲናር ተሽጦ ለድሆች ያልተሰጠ ስለ ምን ነው? አለ። 6፣ይህንም የተናገረ ሌባ ስለ ነበረ ነው እንጂ ለድሆች ተገድዶላቸው አይደለም፤ ከረጢትም ይዞ በውስጡ ከሚገባው ይወስድ ስለ ነበረ ነው። 7፣ኢየሱስም፦ ለምቀበርበት ቀን እንድትጠብቀው ተውአት፤ 8፣ድሆችስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም አለ። 9፣ከአይሁድም ብዙ ሕዝብ በዚያ እንደ ነበረ አውቀው መጡ፥ ከሙታንም ያስነሣውን አልዓዛርን ደግሞ እንዲያዩ ነበረ እንጂ ስለ ኢየሱስ ብቻ አይደለም። 10፣የካህናት አለቆችም አልዓዛርን ደግሞ ሊገድሉት ተማከሩ፥ 11፣ከአይሁድ ብዙዎች ከእርሱ የተነሣ ሄደው በኢየሱስ ያምኑ ነበርና። 12፣በማግሥቱ ወደ በዓሉ መጥተው የነበሩ ብዙ ሕዝብ ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲመጣ በሰሙ ጊዜ፥ 13፣የዘንባባ ዛፍ ዝንጣፊ ይዘው ሊቀበሉት ወጡና፦ ሆሣዕና፤ በጌታ ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው እያሉ ጮኹ። 14-15፣አንቺ የጽዮን ልጅ አትፍሪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ በአህያ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ይመጣል ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ኢየሱስ የአህያ ውርንጫ አግኝቶ በእርሱ ተቀመጠ። 16፣ደቀ መዛሙርቱም ይህን ነገር በመጀመሪያ አላስተዋሉም፤ ነገር ግን ኢየሱስ ከከበረ በኋላ በዚያን ጊዜ ይህ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈ ይህንም እንዳደረጉለት ትዝ አላቸው። 17፣አልዓዛርንም ከመቃብር ጠርቶ ከሙታን ሲያስነሣው ከእርሱ ጋር የነበሩት ሕዝብ ይመሰክሩለት ነበር። 18፣ስለዚህ ደግሞ ሕዝቡ ይህን ምልክት እንዳደረገ ስለ ሰሙ ሊቀበሉት ወጡ። 19፣ስለዚህ ፈሪሳውያን እርስ በርሳቸው፦ አንድ ስንኳ ልታደርጉ እንዳይቻላችሁ ታያላችሁን? እነሆ፥ ዓለሙ በኋላው ተከትሎት ሄዶአል ተባባሉ። 20፣በበዓሉም ሊሰግዱ ከወጡት አንዳንዶቹ የግሪክ ሰዎች ነበሩ፤ 21፣እነርሱም ከገሊላ ቤተ ሳይዳ ወደሚሆን ወደ ፊልጶስ መጥተው፦ ጌታ ሆይ፥ ኢየሱስን ልናይ እንወዳለን ብለው ለመኑት። 22፣ፊልጶስም መጥቶ ለእንድርያስ ነገረው፤ እንድርያስና ፊልጶስ መጥተው ለኢየሱስ ነገሩት። 23፣ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል፦ የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል። 24፣እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የስንዴ ቅንጣት በምድር ወድቃ ካልሞተች ብቻዋን ትቀራለች፤ ብትሞት ግን ብዙ ፍሬ ታፈራለች። 25፣ነፍሱን የሚወድ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም በዚህ ዓለም የሚጠላ ለዘላለም ሕይወት ይጠብቃታል። 26፣የሚያገለግለኝ ቢኖር ይከተለኝ፥ እኔም ባለሁበት አገልጋዬ ደግሞ በዚያ ይሆናል፤ የሚያገለግለኝም ቢኖር አብ ያከብረዋል። 27፣አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ። 28፣አባት ሆይ፥ ስምህን አክብረው። ስለዚህም፦ አከበርሁት ደግሞምአከብረዋለሁ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ። 29፣በዚያ ቆመው የነበሩትም ሕዝብ በሰሙ ጊዜ፦ ነጐድጓድ ነው አሉ፤ ሌሎች፦ መልአክ ተናገረው አሉ። 30፣ኢየሱስም መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ ይህ ድምፅ ስለ እናንተ መጥቶአል እጂ ስለ እኔ አይደለም። 31፣አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል፤ 32፣እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ። 33፣በምን ዓይነትም ሞት ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲያመለክታቸው ይህን ተናገረ። 34፣እንግዲህ ሕዝቡ፦ እኛስ ክርስቶስ ለዘላለም እንዲኖር ከሕጉ ሰምተናል፤ አንተስ የሰው ልጅ ከፍ ከፍ ይል ዘንድ እንዲያስፈልገው እንዴት ትላላህ? ይህ የሰው ልጅ ማን ነው? ብለው መለሱለት። 35፣ኢየሱስም፦ ገና ጥቂት ጊዜ ብርሃን ከእናንተ ጋር ነው። ጨለማ እንዳይደርስባችሁ ብርሃን ሳለላችሁ ተመላለሱ፤ በጨለማም የሚመላለስ ወዴት እንዲሄድ አያውቅም። 36፣የብርሃን ልጆች እንድትሆኑ ብርሃን ሳለላችሁ በብርሃኑ እመኑ አላቸው። ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ሄደና ተሰወረባቸው። 37-38፣ነገር ግን ይህን ያህል ምልክት በፊታቸው ምንም ቢያደርግ፤ ነቢዩ ኢሳይያስ፦ጌታ ሆይ፥ ማን ምስክርነታችንን አመነ? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገለጠ? ብሎ የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ በእርሱ አላመኑም። 39-40፣ኢሳይያስ ደግሞ፦በዓይኖቻቸው እንዳያዩ፥ በልባቸውም እንዳያስተውሉ፥ እንዳይመለሱም፥ እኔም እንዳልፈውሳቸው፥ ዓይኖቻቸውን አሳወረ ልባቸውንም አደነደነ ብሎአልና ስለዚህ ማመን አቃታቸው። 41፣ክብሩን ስለ አየ ኢሳይያስ ይህን አለ፥ ስለ እርሱም ተናገረ። 42፣ከዚህም ጋር ከአለቆች ደግሞ ብዙዎች በእርሱ አመኑ፤ ነገር ግን ከምኵራብ እንዳያስወጡአቸው በፈሪሳውያን ምክንያት አልመሰከሩለትም፤ 43፣ከእግዚአብሔር ክብር ይልቅ የሰውን ክብር ወደዋልና። 44፣ኢየሱስም ጮኸ፥ እንዲህም አለ፦ በእኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በእኔ አይደለም፤ 45፣እኔንም የሚያይ የላከኝን ያያል። 46፣በእኔ የሚያምን ሁሉ በጨለማ እንዳይኖር እኔ ብርሃን ሆኜ ወደ ዓለም መጥቻለሁ። 47፣ዓለምን ላድን እንጂ በዓለም ልፈርድ አልመጣሁምና ቃሌን ሰምቶ የማይጠብቀው ቢኖር የምፈርድበት እኔ አይደለሁም። 48፣የሚጥለኝ ቃሌንም እናገራለሁ።

ምዕራፍ ፲፫ ለማስተካከል

1፣ኢየሱስም ከፋሲካ በዓል በፊት፥ ከዚህ ዓለም ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ አውቆ፥ በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው። 2፣እራትም ሲበሉ ዲያብሎስ በስምዖን ልጅ በአስቆሮቱ በይሁዳ ልብ አሳልፎ እንዲሰጠው አሳብ ካገባ በኋላ፥3 ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ 4፣ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ 5፣በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ። 6፣ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው። 7፣ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው። 8፣ጴጥሮስም፦ የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ኢየሱስም፦ ካላጠብሁህ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም ብሎ መለሰለት። 9፣ስምዖን ጴጥሮስም፦ ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው። 10፣ኢየሱስም፦ የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥ ነገር ግን ሁላችሁ አይደላችሁምአለው። 11፣አሳልፎ የሚሰጠውን ያውቅ ነበርና፤ ስለዚህ፦ ሁላችሁ ንጹሐን አይደላችሁም አለው። 12፣እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው፦ ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን? 13፣እናንተ መምህርና ጌታትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። 14፣እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። 15፣እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። 16፣እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። 17፣ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ። 18፣ስለ ሁላችሁ አልናገርም፤ እኔ የመረጥኋቸውን አውቃለሁ፤ ነገር ግን መጽሐፍ፦ እንጀራዬን የሚበላ በእኔ ላይ ተረከዙን አነሣብኝ ያለው ይፈጸም ዘንድ ነው። 19፣በሆነ ጊዜ እኔ እንደ ሆንሁ ታምኑ ዘንድ፥ ከአሁን ጀምሬ አስቀድሞ ሳይሆን እነግራችኋለሁ። 20፣እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ማናቸውን የምልከውን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። 21፣ኢየሱስ ይህን ብሎ በመንፈሱ ታወከ መስክሮም፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይሰጠኛል አለ። 22፣ደቀ መዛሙርቱ ስለ ማን እንደ ተናገረ አመንትተው እርስ በርሳቸው ተያዩ። 23፣ኢየሱስም ይወደው የነበረ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ በኢየሱስ ደረት ላይ ተጠጋ፤ 24፣ስለዚህ ስምዖን ጴጥሮስ እርሱን ጠቅሶ፦ ስለማን እንደ ተናገረ ንገረን አለው። 25፣እርሱም በኢየሱስ ደረት እንዲህ ተጠግቶ፦ ጌታ ሆይ፥ ማን ነው? አለው። 26፣ኢየሱስም፦ እኔ ቍራሽ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው ብሎ መለሰለት። ቍራሽም አጥቅሶ ለአስቆሮቱ ለስምዖን ልጅ ለይሁዳ ሰጠው። 27፣ቍራሽም ከተቀበለ በኋላ ያን ጊዜ ሰይጣን ገባበት። እንግዲህ ኢየሱስ፦ የምታደርገውን ቶሎ ብለህ አድርግ አለው። 28፣ነገር ግን ከተቀመጡት ስለ ምን ይህን እንዳለው ማንም አላወቀም፤ 29፣ይሁዳ ከረጢቱን የያዘ ስለ ሆነ፥ ኢየሱስ፦ ለበዓሉ የሚያስፈልገንን ግዛ፥ ወይም ለድሆች ምጽዋት እንዲሰጥ ያለው ለአንዳንዱ መስሎአቸው ነበርና። 30፣እርሱም ቍራሹን ከተቀበለ በኋላ ወዲያው ወጣ፤ ሌሊትም ነበረ። 31፣ከወጣም በኋላ ኢየሱስ እንዲ አለ፦ አሁን የሰው ልጅ ከበረ እግዚአብሔርም ስለ እርሱ ከበረ፤ 32፣እግዚአብሔር ስለ እርሱ የከበረ ከሆነ፥ እግዚአብሔር ደግሞ እርሱን ራሱን ያከብረዋል ወዲያውም ያከብረዋል። 33፣ልጆች ሆይ፥ ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፤ ትፈልጉኛላችሁ፤ ለአይሁድም፦ እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አይቻላችሁም እንዳልኋቸው፥ አሁን ለእናንተ ደግሞ እላችኋለሁ። 34፣እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ፥ እንደ ወደድኋችሁ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ። 35፣እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ። 36፣ስምዖን ጴጥሮስም፦ ጌታ ሆይ፥ ወዴት ትሄዳለህ? አለው። ኢየሱስም፦ ወደምሄድበት አሁን ልትከተለኝ አትችልም፥ ነገር ግን በኋላ ትከተለኛለህ ብሎ መለሰለት። 37፣ጴጥሮስም፦ ጌታ ሆይ፥ አሁን ልከተልህ አለመቻሌ ስለ ምንድር ነው? ነፍሴን ስንኳ ስለ አንተ እሰጣለሁ አለው። 38፣ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰለት፦ ነፍስህን ስለ እኔ ትሰጣለህን? እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዶሮ አይጮኽም።

ምዕራፍ ፲፬ ለማስተካከል

 1፤ልባችኹ፡አይታወክ፤በእግዚአብሔር፡እመኑ፥በእኔም፡ደግሞ፡እመኑ። 2፤በአባቴ፡ቤት፡ብዙ፡መኖሪያ፡አለ፤እንዲህስ፡ባይኾን፡ባልዃችኹ፡ነበር፤ስፍራ፡አዘጋጅላችኹ፡ዘንድ፡ እኼዳለኹና፤ 3፤ኼጄም፡ስፍራ፡ባዘጋጅላችኹ፥እኔ፡ባለኹበት፡እናንተ፡ደግሞ፡እንድትኾኑ፡ኹለተኛ፡እመጣለኹ፡ወደ፡ እኔም፡እወስዳችዃለኹ። 4፤ወደምኼድበትም፡ታውቃላችኹ፥መንገዱንም፡ታውቃላችኹ። 5፤ቶማስም፦ጌታ፡ሆይ፥ወደምትኼድበት፡አናውቅም፤እንዴትስ፡መንገዱን፡እናውቃለን፧አለው። 6፤ኢየሱስም፦እኔ፡መንገድና፡እውነት፡ሕይወትም፡ነኝ፤በእኔ፡በቀር፡ወደ፡አብ፡የሚመጣ፡የለም። 7፤እኔንስ፡ብታውቁኝ፡አባቴን፡ደግሞ፡ባወቃችኹ፡ነበር።ካኹንም፡ዠምራችኹ፡ታውቁታላችኹ፡ አይታችኹትማል፡አለው። 8፤ፊልጶስ፦ጌታ፡ሆይ፥አብን፡አሳየንና፡ይበቃናል፡አለው። 9፤ኢየሱስም፡አለው፦አንተ፡ፊልጶስ፥ይህን፡ያኽል፡ዘመን፡ከእናንተ፡ጋራ፡ስኖር፡አታውቀኝምን፧እኔን፡ ያየ፡አብን፡አይቷል፤እንዴትስ፡አንተ፦አብን፡አሳየን፡ትላለኽ፧ 10፤እኔ፡በአብ፡እንዳለኹ፡አብም፡በእኔ፡እንዳለ፡አታምንምን፧እኔ፡የምነግራችኹን፡ቃል፡ከራሴ፡ አልናገረውም፤ነገር፡ግን፥በእኔ፡የሚኖረው፡አብ፡ርሱ፡ሥራውን፡ይሠራል። 11፤እኔ፡በአብ፡እንዳለኹ፡አብም፡በእኔ፡እንዳለ፡እመኑኝ፤ባይኾንስ፡ስለ፡ራሱ፡ስለ፡ሥራው፡እመኑኝ። 12፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥በእኔ፡የሚያምን፡እኔ፡የማደርገውን፡ሥራ፡ርሱ፡ደግሞ፡ ያደርጋል፤ከዚህም፡የሚበልጥ፡ያደርጋል፥ 13፤እኔ፡ወደ፡አብ፡እኼዳለኹና፤አብም፡ስለ፡ወልድ፡እንዲከበር፡በስሜ፡የምትለምኑትን፡ዅሉ፡ አደርገዋለኹ። 14፤ማናቸውንም፡ነገር፡በስሜ፡ብትለምኑ፡እኔ፡አደርገዋለኹ። 15-16፤ብትወዱኝ፡ትእዛዜን፡ጠብቁ።እኔም፡አብን፡እለምናለኹ፡ለዘለዓለምም፡ከእናንተ፡ጋራ፡እንዲኖር፡ሌላ፡ አጽናኝ፡ይሰጣችዃል፤ 17፤ርሱም፡ዓለም፡የማያየውና፡የማያውቀው፡ስለ፡ኾነ፡ሊቀበለው፡የማይቻለው፡የእውነት፡መንፈስ፡ ነው፤ነገር፡ግን፥ከእናንተ፡ዘንድ፡ስለሚኖር፡በውስጣችኹም፡ስለሚኾን፡እናንተ፡ታውቃላችኹ። 18፤ወላጆች፡እንደ፡ሌላቸው፡ልጆች፡አልተዋችኹም፤ወደ፡እናንተ፡እመጣለኹ። 19፤ገና፡ጥቂት፡ዘመን፡አለ፡ከዚህም፡በዃላ፡ዓለም፡አያየኝም፤እናንተ፡ግን፡ታዩኛላችኹ፤እኔ፡ሕያው፡ ነኝና፡እናንተ፡ደግሞ፡ሕያዋን፡ትኾናላችኹ። 20፤እኔ፡በአባቴ፡እንዳለኹ፡እናንተም፡በእኔ፡እንዳላችኹ፡እኔም፡በእናንተ፡እንዳለኹ፡በዚያን፡ቀን፡ ታውቃላችኹ። 21፤ትእዛዜ፡በርሱ፡ዘንድ፡ያለችው፡የሚጠብቃትም፡የሚወደኝ፡ርሱ፡ነው፤የሚወደኝንም፡አባቴ፡ይወደዋል፡ እኔም፡እወደዋለኹ፡ራሴንም፡እገልጥለታለኹ። 22፤የአስቆሮቱ፡ያይደለ፡ይሁዳ፦ጌታ፡ሆይ፥ለዓለም፡ሳይኾን፡ራስኽን፡ለእኛ፡ልትገልጥ፡ያለኽ፡እንዴት፡ ነው፧አለው። 23፤ኢየሱስም፡መለሰ፥አለውም፦የሚወደኝ፡ቢኖር፡ቃሌን፡ይጠብቃል፤አባቴም፡ይወደዋል፡ወደ፡ርሱም፡ እንመጣለን፡በርሱም፡ዘንድ፡መኖሪያ፡እናደርጋለን። 24፤የማይወደኝ፡ቃሌን፡አይጠብቅም፤የምትሰሙትም፡ቃል፡የላከኝ፡የአብ፡ነው፡እንጂ፡የእኔ፡አይደለም። 25፤ከእናንተ፡ዘንድ፡ስኖር፡ይህን፡ነግሬያችዃለኹ፤ 26፤አብ፡በስሜ፡የሚልከው፡ግን፡መንፈስ፡ቅዱስ፡የኾነው፡አጽናኝ፡ርሱ፡ዅሉን፡ያስተምራችዃል፥እኔም፡ የነገርዃችኹን፡ዅሉ፡ያሳስባችዃል። 27፤ሰላምን፡እተውላችዃለኹ፥ሰላሜን፡እሰጣችዃለኹ፤እኔ፡የምሰጣችኹ፡ዓለም፡እንደሚሰጥ፡ አይደለም።ልባችኹ፡አይታወክ፡አይፍራም። 28፤እኔ፡እኼዳለኹ፡ወደ፡እናንተም፡እመጣለኹ፡እንዳልዃችኹ፡ሰማችኹ።የምትወዱኝስ፡ብትኾኑ፡ከእኔ፡ አብ፡ይበልጣልና፥ወደ፡አብ፡በመኼዴ፡ደስ፡ባላችኹ፡ነበር። 29፤ከኾነም፡በዃላ፡ታምኑ፡ዘንድ፡አኹን፡አስቀድሞ፡ሳይኾን፡ነግሬያችዃለኹ። 30፤ከእንግዲህ፡ወዲህ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ብዙ፡አልናገርም፥የዚህ፡ዓለም፡ገዢ፡ይመጣልና፤በእኔ፡ላይም፡ አንዳች፡የለውም፤ 31፤ነገር፡ግን፥አብን፡እንድወድ፡ዓለም፡ሊያውቅ፥አብም፡እንዳዘዘኝ፥እንዲሁ፡አደርጋለኹ።ተነሡ፤ከዚህ፡ እንኺድ።

ምዕራፍ ፲፭ ለማስተካከል

1፤እውነተኛ፡የወይን፡ግንድ፡እኔ፡ነኝ፤ገበሬውም፡አባቴ፡ነው። 2፤ፍሬ፡የማያፈራውን፡በእኔ፡ያለውን፡ቅርንጫፍ፡ዅሉ፡ያስወግደዋል፤ፍሬ፡የሚያፈራውንም፡ዅሉ፡አብዝቶ፡ እንዲያፈራ፡ያጠራዋል። 3፤እናንተ፡ስለነገርዃችኹ፡ቃል፡አኹን፡ንጹሓን፡ናችኹ፤ 4፤በእኔ፡ኑሩ፡እኔም፡በእናንተ።ቅርንጫፍ፡በወይኑ፡ግንድ፡ባይኖር፡ከራሱ፡ፍሬ፡ሊያፈራ፡ እንዳይቻለው፥እንዲሁ፡እናንተ፡ደግሞ፡በእኔ፡ባትኖሩ፡አትችሉም። 5፤እኔ፡የወይን፡ግንድ፡ነኝ፡እናንተም፡ቅርንጫፎች፡ናችኹ።ያለእኔ፡ምንም፡ልታደርጉ፡አትችሉምና፡በእኔ፡ የሚኖር፡እኔም፡በርሱ፥ርሱ፡ብዙ፡ፍሬ፡ያፈራል። 6፤በእኔ፡የማይኖር፡ቢኾን፡እንደ፡ቅርንጫፍ፡ወደ፡ውጭ፡ይጣላል፡ይደርቅማል፤እነርሱንም፡ሰብስበው፡ወደ፡ እሳት፡ይጥሏቸዋል፥ያቃጥሏቸውማል። 7፤በእኔ፡ብትኖሩ፡ቃሎቼም፡በእናንተ፡ቢኖሩ፡የምትወዱትን፡ዅሉ፡ለምኑ፡ይኾንላችኹማል። 8፤ብዙ፡ፍሬ፡ብታፈሩና፡ደቀ፡መዛሙርቴ፡ብትኾኑ፡በዚህ፡አባቴ፡ይከበራል። 9፤አብ፡እንደ፡ወደደኝ፡እኔ፡ደግሞ፡ወደድዃችኹ፤በፍቅሬ፡ኑሩ። 10፤እኔ፡የአባቴን፡ትእዛዝ፡እንደ፡ጠበቅኹ፡በፍቅሩም፡እንደምኖር፥ትእዛዜን፡ብትጠብቁ፡በፍቅሬ፡ ትኖራላችኹ። 11፤ደስታዬም፡በእናንተ፡እንዲኾን፡ደስታችኹም፡እንዲፈጸም፡ይህን፡ነግሬያችዃለኹ። 12፤እኔ፡እንደ፡ወደድዃችኹ፡ርስ፡በርሳችኹ፡ትዋደዱ፡ዘንድ፡ትእዛዜ፡ይህች፡ናት። 13፤ነፍሱን፡ስለ፡ወዳጆቹ፡ከመስጠት፡ይልቅ፡ከዚህ፡የሚበልጥ፡ፍቅር፡ለማንም፡የለውም። 14፤እኔ፡ያዘዝዃችኹን፡ዅሉ፡ብታደርጉ፡እናንተ፡ወዳጆቼ፡ናችኹ። 15፤ከእንግዲህ፡ወዲህ፡ባሪያዎች፡አልላችኹም፤ባሪያ፡ጌታው፡የሚያደርገውን፡አያውቅምና፤ወዳጆች፡ግን፡ ብያችዃለኹ፥ከአባቴ፡የሰማኹትን፡ዅሉ፡ለእናንተ፡አስታውቄያችዃለኹና። 16፤እኔ፡መረጥዃችኹ፡እንጂ፡እናንተ፡አልመረጣችኹኝም፤አብም፡በስሜ፡የምትለምኑትን፡ዅሉ፡ እንዲሰጣችኹ፥ልትኼዱና፡ፍሬ፡ልታፈሩ፡ፍሬያችኹም፡ሊኖር፡ሾምዃችኹ። 17፤ርስ፡በርሳችኹ፡እንድትዋደዱ፡ይህን፡አዛችዃለኹ። 18፤ዓለም፡ቢጠላችኹ፡ከእናንተ፡በፊት፡እኔን፡እንደ፡ጠላኝ፡ዕወቁ። 19፤ከዓለምስ፡ብትኾኑ፡ዓለም፡የራሱ፡የኾነውን፡ይወድ፡ነበር፤ነገር፡ግን፥እኔ፡ከዓለም፡መረጥዃችኹ፡ እንጂ፡ከዓለም፡ስላይደላችኹ፡ስለዚህ፡ዓለም፡ይጠላችዃል። 20፤ባሪያ፡ከጌታው፡አይበልጥም፡ብዬ፡የነገርዃችኹን፡ቃል፡ዐስቡ።እኔን፡አሳደውኝ፡እንደ፡ኾኑ፡እናንተን፡ ደግሞ፡ያሳድዷችዃል፤ቃሌን፡ጠብቀው፡እንደ፡ኾኑ፡ቃላችኹን፡ደግሞ፡ይጠብቃሉ። 21፤ዳሩ፡ግን፡የላከኝን፡አያውቁምና፡ይህን፡ዅሉ፡ሰለ፡ስሜ፡ያደርጉባችዃል። 22፤እኔ፡መጥቼ፡ባልነገርዃቸውስ፡ኀጢአት፡ባልኾነባቸውም፡ነበር፤አኹን፡ግን፡ለኀጢአታቸው፡ምክንያት፡ የላቸውም። 23፤እኔን፡የሚጠላ፡አባቴን፡ደግሞ፡ይጠላል። 24፤ሌላ፡ሰው፡ያላደረገውን፡ሥራ፡በመካከላቸው፡ባላደረግኹ፥ኀጢአት፡ባልኾነባቸውም፡ነበር፤አኹን፡ግን፡ እኔንም፡አባቴንም፡አይተውማል፡ጠልተውማል። 25፤ነገር፡ግን፥በሕጋቸው።በከንቱ፡ጠሉኝ፡ተብሎ፡የተጻፈው፡ቃል፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ነው። 26፤ዳሩ፡ግን፡እኔ፡ከአብ፡ዘንድ፡የምልክላችኹ፡አጽናኝ፡ርሱም፡ከአብ፡የሚወጣ፡የእውነት፡መንፈስ፡ በመጣ፡ጊዜ፥ርሱ፡ስለ፡እኔ፡ይመሰክራል፤ 27፤እናንተም፡ደግሞ፡ከመዠመሪያ፡ከእኔ፡ጋራ፡ኖራችዃልና፥ትመሰክራላችኹ።

ምዕራፍ ፲፮ ለማስተካከል

1፤እንዳትሰናከሉ፡ይህን፡ተናግሬያችዃለኹ። 2፤ከምኵራባቸው፡ያወጧችዃል፤ከዚህ፡በላይ፡ደግሞ፡የሚገድላችኹ፡ዅሉ፡እግዚአብሔርን፡እንደሚያገለግል፡ የሚመስልበት፡ጊዜ፡ይመጣል። 3፤ይህንም፡የሚያደርጉባችኹ፡አብንና፡እኔን፡ስላላወቁ፡ነው። 4፤ነገር፡ግን፥ጊዜው፡ሲደርስ፡እኔ፡እንደ፡ነገርዃችኹ፡ታስቡ፡ዘንድ፡ይህን፡ተናግሬያችዃለኹ።ከእንናንተም፡ ጋራ፡ስለ፡ነበርኹ፡በመዠመሪያ፡ይህን፡አልነገርዃችኹም። 5፤አኹን፡ግን፡ወደላከኝ፡እኼዳለኹ፡ከእናንተም፦ወዴት፡ትኼዳለኽ፧ብሎ፡የሚጠይቀኝ፡የለም። 6፤ነገር፡ግን፥ይህን፡ስለ፡ተናገርዃችኹ፡ሐዘን፡በልባችኹ፡ሞልቷል። 7፤እኔ፡ግን፡እውነት፡እነግራችዃለኹ፤እኔ፡እንድኼድ፡ይሻላችዃል።እኔ፡ባልኼድ፡አጽናኙ፡ወደ፡እናንተ፡ አይመጣምና፤እኔ፡ብኼድ፡ግን፡ርሱን፡እልክላችዃለኹ። 8፤ርሱም፡መጥቶ፡ስለ፡ኀጢአት፡ስለ፡ጽድቅም፡ስለ፡ፍርድም፡ዓለምን፡ይወቅሳል፤ 9-10፤ስለ፡ኀጢአት፥በእኔ፡ስለማያምኑ፡ነው፤ስለ፡ጽድቅም፥ወደ፡አብ፡ስለምኼድ፡ከዚህም፡በዃላ፡ ስለማታዩኝ፡ነው፤ 11፤ስለ፡ፍርድም፥የዚህ፡ዓለም፡ገዢ፡ስለ፡ተፈረደበት፡ነው። 12፤የምነግራችኹ፡ገና፡ብዙ፡አለኝ፥ነገር፡ግን፥አኹን፡ልትሸከሙት፡አትችሉም። 13፤ግን፡ርሱ፡የእውነት፡መንፈስ፡በመጣ፡ጊዜ፡ወደ፡እውነት፡ዅሉ፡ይመራችዃል፤የሚሰማውን፡ዅሉ፡ ይናገራል፡እንጂ፡ከራሱ፡አይነግርምና፤የሚመጣውንም፡ይነግራችዃል። 14፤ርሱ፡ያከብረኛል፥ለእኔ፡ካለኝ፡ወስዶ፡ይነግራችዃልና። 15፤ለአብ፡ያለው፡ዅሉ፡የእኔ፡ነው፤ስለዚህ፦ለእኔ፡ካለኝ፡ወስዶ፡ይነግራችዃል፡አልኹ። 16፤ጥቂት፡ጊዜ፡አለ፥አታዩኝምም፤ደግሞም፡ጥቂት፡ጊዜ፡አለ፥ታዩኛላችኹም፥እኔ፡ወደ፡አብ፡ እኼዳለኹና። 17፤ከደቀ፡መዛሙርቱም፡አንዳንዶቹ፡ርስ፡በርሳቸው፦ጥቂት፡ጊዜ፡አለ፥አታዩኝምም፤ደግሞም፡ጥቂት፡ጊዜ፡ አለ፥ታዩኛላችኹም፤ደግሞ፦ወደ፡አብ፡እኼዳለኹና፡የሚለን፡ይህ፡ምንድር፡ነው፧ተባባሉ። 18፤እንግዲህ፦ጥቂት፡የሚለው፡ይህ፡ምንድር፡ነው፧የሚናገረውን፡አናውቅም፡አሉ። 19፤ኢየሱስም፡ሊጠይቁት፡እንደ፡ወደዱ፡ዐውቆ፡እንዲህ፡አላቸው፦ጥቂት፡ጊዜ፡ አለ፥አታዩኝምም፤ደግሞም፡ጥቂት፡ጊዜ፡አለ፥ታዩኛላችኹ፡ስላልኹ፥ስለዚህ፡ርስ፡በርሳችኹ፡ ትመራመራላችኹን፧ 20፤እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥እናንተ፡ታለቅሳላችኹ፡ሙሾም፡ታወጣላችኹ፥ዓለም፡ግን፡ደስ፡ ይለዋል፤እናንተም፡ታዝናላችኹ፥ነገር፡ግን፥ሐዘናችኹ፡ወደ፡ደስታ፡ይለወጣል። 21፤ሴት፡በምትወልድበት፡ጊዜ፡ወራቷ፡ስለ፡ደረሰ፡ታዝናለች፤ነገር፡ግን፥ሕፃን፡ከወለደች፡በዃላ፥ሰው፡ በዓለም፡ተወልዷልና፥ስለ፡ደስታዋ፡መከራዋን፡ዃላ፡አታስበውም። 22፤እንግዲህ፡እናንተ፡ደግሞ፡አኹን፡ታዝናላችኹ፤ነገር፡ግን፥እንደ፡ገና፡አያችዃለኹ፡ልባችኹም፡ደስ፡ይለዋል፥ደስታችኹንም፡የሚወስድባችኹ፡የለም። 23፤በዚያን፡ቀንም፡ከእኔ፡አንዳች፡አትለምኑም።እውነት፡እውነት፡እላችዃለኹ፥አብ፡በስሜ፡የምትለምኑትን፡ ዅሉ፡ይሰጣችዃል። 24፤እስከ፡አኹን፡በስሜ፡ምንም፡አልለመናችኹም፤ደስታችኹ፡ፍጹም፡እንዲኾን፡ለምኑ፡ትቀበሉማላችኹ። 25፤ይህን፡በምሳሌ፡ነግሬያችዃለኹ፤ነገር፡ግን፥ስለ፡አብ፡ለእናንተ፡በግልጥ፡የምናገርበት፡እንጂ፡ከዚያ፡ ወዲያ፡በምሳሌ፡የማልናገርበት፡ሰዓት፡ይመጣል። 26፤በዚያን፡ቀን፡በስሜ፡ትለምናላችኹ፤እኔም፡ስለ፡እናንተ፡አብን፡እንድለምን፡የምላችኹ፡አይደለኹም፤ 27፤እናንተ፡ስለ፡ወደዳችኹኝ፡ከእግዚአብሔርም፡ዘንድ፡እኔ፡እንደ፡ወጣኹ፡ስላመናችኹ፡አብ፡ርሱ፡ራሱ፡ ይወዳችዃልና። 28፤ከአብ፡ወጥቼ፡ወደ፡ዓለም፡መጥቻለኹ፤ደግሞ፡ዓለምን፡እተወዋለኹ፡ወደ፡አብም፡እኼዳለኹ። 29፤ደቀ፡መዛሙርቱ፦እንሆ፥አኹን፡በግልጥ፡ትናገራለኽ፡በምሳሌም፡ምንም፡አትነግርም። 30፤ዅሉን፡እንድታውቅ፥ማንምም፡ሊጠይቅኽ፡እንዳትፈልግ፡አኹን፡እናውቃለን፤ስለዚህ፥ከእግዚአብሔር፡ እንደ፡ወጣኽ፡እናምናለን፡አሉት። 31፤ኢየሱስም፡እንዲህ፡ብሎ፡መለሰላቸው።አኹን፡ታምናላችኹን፧ 32፤እንሆ፥እያንዳንዳችኹ፡ወደ፡ቤት፡የምትበታተኑበት፡እኔንም፡ለብቻዬ፡የምትተዉበት፡ሰዓት፡ ይመጣል፥አኹንም፡ደርሷል፤ነገር፡ግን፥አብ፡ከእኔ፡ጋራ፡ስለ፡ኾነ፡ብቻዬን፡አይደለኹም። 33፤በእኔ፡ሳላችኹ፡ሰላም፡እንዲኾንላችኹ፡ይህን፡ተናግሬያችዃለኹ።በዓለም፡ሳላችኹ፡መከራ፡ አለባችኹ፤ነገር፡ግን፥አይዟችኹ፤እኔ፡ዓለምን፡አሸንፌዋለኹ።

ምዕራፍ ፲፯ ለማስተካከል

1-2፤ኢየሱስም፡ይህን፡ተናግሮ፡ወደ፡ሰማይ፡ዐይኖቹን፡አነሣና፡እንዲህ፡አለ፦አባት፡ሆይ፥ሰዓቱ፡ ደርሷል፤ልጅኽ፡ያከብርኽ፡ዘንድ፥በሥጋም፡ዅሉ፡ላይ፡ሥልጣን፡እንደ፡ሰጠኸው፥ለሰጠኸው፡ዅሉ፡ የዘለዓለምን፡ሕይወት፡ይሰጣቸው፡ዘንድ፡ልጅኽን፡አክብረው። 3፤እውነተኛ፡አምላክ፡ብቻ፡የኾንኽ፡አንተን፡የላክኸውንም፡ኢየሱስ፡ክርስቶስን፡ያውቁ፡ዘንድ፡ይህች፡ የዘለዓለም፡ሕይወት፡ናት። 4፤እኔ፡ላደርገው፡የሰጠኸኝን፡ሥራ፡ፈጽሜ፡በምድር፡አከበርኹኽ፤ 5፤አኹንም፥አባት፡ሆይ፥ዓለም፡ሳይፈጠር፡ባንተ፡ዘንድ፡በነበረኝ፡ክብር፡አንተ፡በራስኽ፡ዘንድ፡አክብረኝ። 6፤ከዓለም፡ለሰጠኸኝ፡ሰዎች፡ስምኽን፡ገለጥኹላቸው።የአንተ፡ነበሩ፡ለኔም፡ሰጠኻቸው፤ 7፤ቃልኽንም፡ጠብቀዋል።የሰጠኸኝ፡ዅሉ፡ከአንተ፡እንደ፡ኾነ፡አኹን፡ያውቃሉ፤ 8፤የሰጠኸኝን፡ቃል፡ሰጥቻቸዋለኹና፤እነርሱም፡ተቀበሉት፥ከአንተም፡ዘንድ፡እንደ፡ወጣኹ፡በእውነት፡ ዐወቁ፥አንተም፡እንደ፡ላክኸኝ፡አመኑ። 9፤እኔ፡ስለ፡እነዚህ፡እለምናለኹ፤ስለ፡ዓለም፡አልለምንም፡ስለሰጠኸኝ፡እንጂ፤የአንተ፡ናቸውና፤ 10፤የእኔም፡የኾነ፡ዅሉ፡የአንተ፡ነው፡የአንተውም፡የእኔ፡ነው፤እኔም፡ስለ፡እነርሱ፡ከብሬያለኹ። 11፤ከዚህም፡በዃላ፡በዓለም፡አይደለኹም፥እነርሱም፡በዓለም፡ናቸው፥እኔም፡ወዳንተ፡እመጣለኹ።ቅዱስ፡ አባት፡ሆይ፥እነዚህን፡የሰጠኸኝን፡እንደ፡እኛ፡አንድ፡እንዲኾኑ፡በስምኽ፡ጠብቃቸው። 12፤ከነርሱ፡ጋራ፡በዓለም፡ሳለኹ፡የሰጠኸኝን፡በስምኽ፡እኔ፡እጠብቃቸው፡ነበር፤ጠበቅዃቸውም፡መጽሐፉም፡እንዲፈጸም፡ከጥፋት፡ልጅ፡በቀር፡ከነርሱ፡ማንም፡አልጠፋም። 13፤አኹንም፡ወዳንተ፡እመጣለኹ፤በእነርሱም፡ዘንድ፡ደስታዬ፡የተፈጸመ፡እንዲኾንላቸው፡ይህን፡በዓለም፡ እናገራለኹ። 14፤እኔ፡ቃልኽን፡ሰጥቻቸዋለኹ፤እኔም፡ከዓለም፡እንዳይደለኹ፡ከዓለም፡አይደሉምና፡ዓለም፡ጠላቸው። 15፤ከክፉ፡እንድትጠብቃቸው፡እንጂ፡ከዓለም፡እንድታወጣቸው፡አልለምንም። 16፤እኔ፡ከዓለም፡እንዳይደለኹ፡ከዓለም፡አይደሉም። 17፤በእውነትኽ፡ቀድሳቸው፤ቃልኽ፡እውነት፡ነው። 18፤ወደ፡ዓለም፡እንደ፡ላክኸኝ፡እንዲሁ፡እኔ፡ወደ፡ዓለም፡ላክዃቸው፤ 19፤እነርሱም፡ደግሞ፡በእውነት፡የተቀደሱ፡እንዲኾኑ፡እኔ፡ራሴን፡ስለ፡እነርሱ፡እቀድሳለኹ። 20-21፤ዅሉም፡አንድ፡ይኾኑ፡ዘንድ፥ከቃላቸው፡የተነሣ፡በእኔ፡ስለሚያምኑ፡ደግሞ፡እንጂ፡ስለ፡እነዚህ፡ ብቻ፡አልለምንም፤አንተ፡እንደ፡ላክኸኝ፡ዓለም፡ያምን፡ዘንድ፥አንተ፥አባት፡ሆይ፥በእኔ፡እንዳለኽ፡እኔም፡ ባንተ፥እነርሱ፡ደግሞ፡በእኛ፡አንድ፡ይኾኑ፡ዘንድ፡እለምናለኹ። 22-23፤እኛም፡አንድ፡እንደ፡ኾን፟፡አንድ፡ይኾኑ፡ዘንድ፤እኔም፡በእነርሱ፡አንተም፡በእኔ፡ስትኾን፥ባንድ፡ ፍጹማን፡እንዲኾኑ፥የሰጠኸኝን፡ክብር፡እኔ፡ሰጥቻቸዋለኹ፤እንዲሁም፡ዓለም፡አንተ፡እንደ፡ላክኸኝ፡ በወደድኸኝም፡መጠን፡እነርሱን፡እንደ፡ወደድኻቸው፡ያውቃል። 24፤አባት፡ሆይ፥ዓለም፡ሳይፈጠር፡ስለ፡ወደድኸኝ፡የሰጠኸኝን፡ክብሬን፡እንዲያዩ፡እኔ፡ባለኹበት፡የሰጠኸኝ፡ እነርሱ፡ደግሞ፡ከእኔ፡ጋራ፡ይኾኑ፡ዘንድ፡እወዳለኹ። 25፤ጻድቅ፡አባት፡ሆይ፥ዓለም፡አላወቀኽም፥እኔ፡ግን፡ዐወቅኹኽ፡እነዚህም፡አንተ፡እንደ፡ላክኸኝ፡ዐወቁ፤26፤እኔንም፡የወደድኽባት፡ፍቅር፡በእነርሱ፡እንድትኾን፡እኔም፡በእነርሱ፥ስምኽን፡አስታወቅዃቸው፡ አስታውቃቸውማለኹ።

ምዕራፍ ፲፰ ለማስተካከል

1፤ኢየሱስም፡ይህን፡ብሎ፡አትክልት፡ወዳለበት፡ስፍራ፡ወደቄድሮን፡ወንዝ፡ማዶ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ጋራ፡ ወጣ፤ርሱም፡ደቀ፡መዛሙርቱም፡በዚያ፡ገቡ። 2፤ኢየሱስም፡ደቀ፡መዛሙርቱም፡ብዙ፡ጊዜ፡ወደዚያ፡ስለ፡ተሰበሰቡ፡አሳልፎ፡የሰጠው፡ይሁዳ፡ደግሞ፡ ስፍራውን፡ያውቅ፡ነበር። 3፤ስለዚህ፥ይሁዳ፡ጭፍራዎችንና፥ከካህናት፡አለቃዎች፣ከፈሪሳውያንም፡ሎሌዎችን፡ተቀብሎ፥በችቦና፡ በፋና፣በጋሻ፡ጦርም፡ወደዚያ፡መጣ። 4፤ኢየሱስም፥የሚመጣበትን፡ዅሉ፡ዐውቆ፡ወጣና፦ማንን፡ትፈልጋላችኹ፡አላቸው። 5፤የናዝሬቱን፡ኢየሱስን፡ብለው፡መለሱለት።ኢየሱስ፦እኔ፡ነኝ፡አላቸው።አሳልፎ፡የሰጠውም፡ይሁዳ፡ ደግሞ፡ከነርሱ፡ጋራ፡ቆሞ፡ነበር። 6፤እንግዲህ፦እኔ፡ነኝ፡ባላቸው፡ጊዜ፥ወደ፡ዃላ፡አፈግፍገው፡በምድር፡ወደቁ። 7፤ደግሞም፦ማንን፡ትፈልጋላችኹ፧ብሎ፡ጠየቃቸው።እነርሱም፦የናዝሬቱን፡ኢየሱስን፡አሉት። 8፤ኢየሱስ፡መልሶ፦እኔ፡ነኝ፡አልዃችኹ፤እንግዲህ፡እኔን፡ትፈልጉ፡እንደ፡ኾናችኹ፡እነዚህ፡ይኺዱ፡ ተዉአቸው፡አለ፤ 9፤ይህም፦ከነዚህ፡ከሰጠኸኝ፡አንዱን፡ስንኳ፡አላጠፋኹም፡ያለው፡ቃል፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ነው። 10፤ስምዖን፡ጴጥሮስም፡ሰይፍ፡ስለ፡ነበረው፡መዘዘው፥የሊቀ፡ካህናቱንም፡ባሪያ፡መቶ፟፡ቀኝ፡ዦሮውን፡ ቈረጠ፤የባሪያውም፡ስም፡ማልኮስ፡ነበረ። 11፤ኢየሱስም፡ጴጥሮስን፦ሰይፍኽን፡ወደ፡ሰገባው፡ክተተው፤አብ፡የሰጠኝን፡ጽዋ፡አልጠጣትምን፧አለው። 12፤እንግዲህ፡የሻለቃውና፡ጭፍራዎቹ፡የአይሁድም፡ሎሌዎች፡ኢየሱስን፡ይዘው፡አሰሩት፥ 13፤አስቀድመውም፡ወደ፡ሐና፡ወሰዱት፤በዚያች፡ዓመት፡ሊቀ፡ካህናት፡ለነበረው፡ለቀያፋ፡ዐማቱ፡ነበርና። 14፤ቀያፋም፦አንድ፡ሰው፡ስለ፡ሕዝብ፡ይሞት፡ዘንድ፡ይሻላል፡ብሎ፡ለአይሁድ፡የመከራቸው፡ነበረ። 15፤ስምዖን፡ጴጥሮስም፡ሌላውም፡ደቀ፡መዝሙር፡ኢየሱስን፡ተከተሉ።ያም፡ደቀ፡መዝሙር፡በሊቀ፡ካህናቱ፡ ዘንድ፡የታወቀ፡ነበረ፥ወደሊቀ፡ካህናቱም፡ግቢ፡ከኢየሱስ፡ጋራ፡ገባ፤ 16፤ጴጥሮስ፡ግን፡በውጭ፡በበሩ፡ቆሞ፡ነበር።እንግዲህ፡በሊቀ፡ካህናቱ፡ዘንድ፡የታወቀው፡ሌላው፡ደቀ፡መዝሙር፡ወጣ፥ለበረኛዪቱም፡ነግሮ፡ጴጥሮስን፡አስገባው። 17፤በረኛ፡የነበረችዪቱም፡ገረድ፡ጴጥሮስን፦አንተ፡ደግሞ፡ከዚህ፡ሰው፡ደቀ፡መዛሙርት፡አንዱ፡ አይደለኽምን፧አለችው።ርሱ፦አይደለኹም፡አለ። 18፤ብርድ፡ነበረና፡ባሪያዎችና፡ሎሌዎች፡የፍም፡እሳት፡አንድደው፡ቆሙ፡ይሞቁም፡ነበር፤ጴጥሮስም፡ደግሞ፡ ከነርሱ፡ጋራ፡ቆሞ፡ይሞቅ፡ነበር። 19፤ሊቀ፡ካህናቱም፡ኢየሱስን፡ስለ፡ደቀ፡መዛሙርቱና፡ስለ፡ትምህርቱ፡ጠየቀው። 20፤ኢየስስም፡መልሶ፦እኔ፡በግልጥ፡ለዓለም፡ተናገርኹ፤አይሁድ፡ዅሉ፡በሚሰበሰቡበት፡በምኵራብና፡ በመቅደስ፡እኔ፡ዅልጊዜ፡አስተማርኹ፥በስውርም፡ምንም፡አልተናገርኹም። 21፤ስለምን፡ትጠይቀኛለኽ፧ለእነርሱ፡የተናገርኹትን፡የሰሙትን፡ጠይቅ፤እንሆ፥እነዚህ፡እኔ፡የነገርኹትን፡ ያውቃሉ፡አለው። 22፤ይህንም፡ሲል፡በዚያ፡ቆሞ፡የነበረው፡ከሎሌዎች፡አንዱ፦ለሊቀ፡ካህናቱ፡እንዲህ፡ትመልሳለኽን፧ብሎ፡ ኢየሱስን፡በጥፊ፡መታው። 23፤ኢየሱስም፡መልሶ፦ክፉ፡ተናግሬ፡እንደ፡ኾንኹ፡ስለ፡ክፉ፡መስክር፤መልካም፡ተናግሬ፡እንደ፡ኾንኹ፡ ግን፡ሰለ፡ምን፡ትመታኛለኽ፧አለው። 24፤ስለዚህ፥ሐና282፥እንደ፡ታሰረ፥ወደ፡ሊቀ፡ካህናቱ፣ወደ፡ቀያፋ፡ሰደደው። 25፤ስምዖን፡ጴጥሮስም፡ቆሞ፡እሳት፡ይሞቅ፡ነበር።እንግዲህ፦አንተ፡ደግሞ፡ከደቀ፡መዛሙርቱ፡ አይደለኽምን፧አሉት።ርሱም፦አይደለኹም፡ብሎ፡ካደ። 26፤ጴጥሮስ፡ዦሮውን፡የቈረጠው፡ዘመድ፡የኾነ፡ከሊቀ፡ካህናቱ፡ባሪያዎች፡አንዱ፦በአትክልቱ፡ከርሱ፡ጋራ፡ እኔ፡አይቼኽ፡አልነበረምን፧አለው። 27፤ጴጥሮስም፡እንደ፡ገና፡ካደ፥ወዲያውም፡ዶሮ፡ጮኸ። 28፤ኢየሱስንም፡ከቀያፋ፡ወደገዢው፡ግቢ፡ወሰዱት፤ማለዳም፡ነበረ፤እነርሱም፡የፋሲካ፡በግ፡ይበሉ፡ዘንድ፡ እንጂ፡እንዳይረክሱ፡ወደገዢው፡ግቢ፡አልገቡም። 29፤ስለዚህ፥ጲላጦስ፡ወደ፡ውጭ፣ወደ፡እነርሱ፡ወጥቶ፦ይህን፡ሰው፡ስለ፡ምን፡ትከሱታላችኹ፡አላቸው። 30፤እነርሱም፡መልሰው፦ይህስ፡ክፉ፡አድራጊ፡ባይኾን፡ወዳንተ፡አሳልፈን፡ባልሰጠነውም፡ነበር፡አሉት። 31፤ጲላጦስም፦እናንተ፡ወስዳችኹ፡እንደ፡ሕጋችኹ፡ፍረዱበት፡አላቸው።አይሁድም፦ለእኛስ፡ማንንም፡ልንገድል፡አልተፈቀደልንም፡አሉት፤ 32፤ኢየሱስ፡በምን፡ዐይነት፡ሞት፡ሊሞት፡እንዳለው፡ሲያመለክት፡የተናገረው፡ቃል፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ነው። 33፤ጲላጦስም፡እንደ፡ገና፡ወደገዢው፡ግቢ፡ገባና፡ኢየሱስን፡ጠርቶ፦የአይሁድ፡ንጉሥ፡አንተ፡ ነኽን፧አለው። 34፤ኢየሱስም፡መልሶ፦አንተ፡ይህን፡የምትለው፡ከራስኽ፡ነውን፡ወይስ፡ሌላዎች፡ስለ፡እኔ፡ ነገሩኽን፧አለው። 35፤ጲላጦስ፡መልሶ፦እኔ፡አይሁዳዊ፡ነኝን፧ወገኖችኽና፡የካህናት፡አለቃዎች፡ለእኔ፡አሳልፈው፡ ሰጡኽ፤ምን፡አድርገኻል፧አለው። 36፤ኢየሱስም፡መልሶ፦መንግሥቴ፡ከዚህ፡ዓለም፡አይደለችም፤መንግሥቴስ፡ከዚህ፡ዓለም፡ብትኾን፥ወደ፡ አይሁድ፡እንዳልሰጥ፡ሎሌዎቼ፡ይዋጉልኝ፡ነበር፤አኹን፡ግን፡መንግሥቴ፡ከዚህ፡አይደለችም፡አለው። 37፤ጲላጦስም፦እንግዲያ፡ንጉሥ፡ነኽን፧አለው።ኢየሱስም፡መልሶ፦እኔ፡ንጉሥ፡እንደ፡ኾንኹ፡አንተ፡ ትላለኽ።እኔ፡ለእውነት፡ልመሰክር፡ስለዚህ፡ተወልጃለኹ፡ስለዚህም፡ወደ፡ዓለም፡መጥቻለኹ፤ከእውነት፡ የኾነ፡ዅሉ፡ድምፄን፡ይሰማል፡አለው። 38፤ጲላጦስ፦እውነት፡ምንድር፡ነው፧አለው።ይህንም፡ብሎ፡ዳግመኛ፡ወደ፡አይሁድ፡ወጥቶ፦እኔስ፡ አንዲት፡በደል፡ስንኳ፡አላገኘኹበትም። 39፤ነገር፡ግን፥በፋሲካ፡አንድ፡ልፈታላችኹ፡ልማድ፡አላችኹ፤እንግዲህ፡የአይሁድን፡ንጉሥ፡ልፈታላችኹ፡ ትወዳላችኹን፧አላቸው። 40፤ዅሉም፡ደግመው፦በርባንን፡እንጂ፡ይህን፡አይደለም፡እያሉ፡ጮኹ።በርባን፡ግን፡ወንበዴ፡ነበረ።

ምዕራፍ ፲፱ ለማስተካከል

1፤በዚያን፡ጊዜም፡ጲላጦስ፡ኢየሱስን፡ይዞ፡ገረፈው። 2፤ወታደሮችም፡ከሾኽ፡አክሊል፡ጐንጕነው፡በራሱ፡ላይ፡አኖሩ፡ቀይ፡ልብስም፡አለበሱት፤ 3፤እየቀረቡም፦የአይሁድ፡ንጉሥ፡ሆይ፥ሰላም፡ለአንተ፡ይኹን፡ይሉት፡ነበር፤ 4፤በጥፊም፡ይመቱት፡ነበር።ጲላጦስም፡ደግሞ፡ወደ፡ውጭ፡ወጥቶ፦እንሆ፥አንዲት፡በደል፡ስንኳ፡ እንዳላገኘኹበት፡ታውቁ፡ዘንድ፡ርሱን፡ወደ፡ውጭ፡አወጣላችዃለኹ፡አላቸው። 5፤ኢየሱስም፡የሾኽ፡አክሊል፡ደፍቶ፡ቀይ፡ልብስም፡ለብሶ፡ወደ፡ውጭ፡ወጣ። 6፤ጲላጦስም፦እንሆ፥ሰውዬው፡አላቸው።የካህናት፡አለቃዎችና፡ሎሌዎች፡ባዩትም፡ጊዜ፦ስቀለው፡ስቀለው፡ እያሉ፡ጮኹ።ጲላጦስም፦እኔስ፡አንዲት፡በደል፡ስንኳ፡አላገኘኹበትምና፡እናንተ፡ወስዳችኹ፡ስቀሉት፡ አላቸው። 7፤አይሁድም፡መልሰው፦እኛ፡ሕግ፡አለን፥እንደ፡ሕጋችንም፡ሊሞት፡ይገ፟ባ፟ዋል፥ራሱን፡የእግዚአብሔር፡ ልጅ፡አድርጓልና፥አሉት። 8፤ስለዚህ፥ጲላጦስ፡ይህን፡ነገር፡በሰማ፡ጊዜ፥እጅግ፡ፈራ፤ 9፤ተመልሶም፡ወደገዢው፡ግቢ፡ገባና፡ኢየሱስን፦አንተ፡ከወዴት፡ነኽ፧አለው።ኢየሱስ፡ግን፡አንድ፡እንኳ፡ አልመለሰለትም። 10፤ስለዚህ፥ጲላጦስ፦አትነግረኝምን፧ልሰቅልኽ፡ሥልጣን፡እንዳለኝ፡ወይም፡ልፈታኽ፡ሥልጣን፡እንዳለኝ፡ አታውቅምን፧አለው። 11፤ኢየሱስም፡መልሶ፦ከላይ፡ካልተሰጠኽ፡በቀር፥በእኔ፡ላይ፡ምንም፡ሥልጣን፡ ባልነበረኽም፤ስለዚህ፥ለአንተ፡አሳልፎ፡የሰጠኝ፥ኀጢአቱ፡የባሰ፡ነው፡አለው። 12፤ከዚህ፡በዃላ፡ጲላጦስ፡ሊፈታው፡ፈለገ፤ነገር፡ግን፥አይሁድ፦ይህንስ፡ብትፈታው፡የቄሳር፡ወዳጅ፡አይደለኽም፤ራሱን፡ንጉሥ፡የሚያደርግ፡ዅሉ፡የቄሳር፡ተቃዋሚ፡ነው፡እያሉ፡ጮኹ። 13፤ጲላጦስም፡ይህን፡ነገር፡ሰምቶ፡ኢየሱስን፡ወደ፡ውጭ፡አወጣው፥በዕብራይስጥም፡ገበታ፡በተባለው፡ ጸፍጸፍ፡በሚሉት፡ስፍራ፡በፍርድ፡ወንበር፡ተቀመጠ። 14፤ለፋሲካም፡የማዘጋጀት፡ቀን፡ነበረ፤ስድስት፡ሰዓትም፡የሚያኽል፡ነበረ፤አይሁድንም፦እንሆ፥ንጉሣችኹ፡ አላቸው። 15፤እነርሱ፡ግን፦አስወግደው፥አስወግደው፥ስቀለው፡እያሉ፡ጮኹ።ጲላጦስም፦ንጉሣችኹን፡ ልስቀለውን፧አላቸው።የካህናት፡አለቃዎችም፦ከቄሳር፡በቀር፡ሌላ፡ንጉሥ፡የለንም፡ብለው፡መለሱለት። 16፤ስለዚህ፥በዚያን፡ጊዜ፡እንዲሰቀል፡አሳልፎ፡ሰጣቸው። 17፤ኢየሱስንም፡ይዘው፡ወሰዱት፤መስቀሉንም፡ተሸክሞ፡በዕብራይስጥ፡ጎልጎታ፡ወደተባለው፡የራስ፡ቅል፡ ስፍራ፡ወደሚሉት፡ወጣ። 18፤በዚያም፡ሰቀሉት፥ከርሱም፡ጋራ፡ሌላዎች፡ኹለት፥አንዱን፡በዚህ፡አንዱን፡በዚያ፡ኢየሱስንም፡ በመካከላቸው፡ሰቀሉ። 19፤ጲላጦስም፡ደግሞ፡ጽሕፈት፡ጽፎ፡በመስቀሉ፡ላይ፡አኖረው፤ጽሕፈቱም፦የአይሁድ፡ንጉሥ፡የናዝሬቱ፡ ኢየሱስ፡የሚል፡ነበረ። 20፤ኢየሱስም፡የተሰቀለበት፡ስፍራ፡ለከተማ፡ቅርብ፡ነበረና፡ከአይሁድ፡ብዙዎች፡ይህን፡ጽሕፈት፡ አነበቡት፤በዕብራይስጥና፡በሮማይስጥ፡በግሪክም፡ተጽፎ፡ነበር። 21፤ስለዚህ፥የአይሁድ፡ካህናት፡አለቃዎች፡ጲላጦስን፦ርሱ፦የአይሁድ፡ንጉሥ፡ነኝ፡እንዳለ፡ እንጂ፥የአይሁድ፡ንጉሥ፡ብለኽ፡አትጻፍ፡አሉት። 22፤ጲላጦስም፦የጻፍኹትን፡ጽፌያለኹ፡ብሎ፡መለሰ። 23፤ጭፍራዎችም፡ኢየሱስን፡በሰቀሉት፡ጊዜ፡ልብሶቹን፡ወስደው፡ለያንዳንዱ፡ጭፍራ፡አንድ፡ክፍል፡ኾኖ፡ በአራት፡ከፋፈሉት፤እጀ፡ጠባቡን፡ደግሞ፡ወሰዱ።እጀ፡ጠባቡም፡ከላይ፡ዠምሮ፡ወጥ፟፡ኾኖ፡የተሠራ፡ነበረ፡ እንጂ፡የተሰፋ፡አልነበረም። 24፤ስለዚህ፥ርስ፡በርሳቸው፦ለማን፡እንዲኾን፡በርሱ፡ዕጣ፡እንጣጣልበት፡እንጂ፥አንቅደደው፡ ተባባሉ።ይህም፦ልብሴን፡ርስ፡በርሳቸው፡ተከፋፈሉ፡በእጀ፡ጠባቤም፡ዕጣ፡ተጣጣሉበት፡የሚለው፡የመጽሐፍ፡ ቃል፡ይፈጸም፡ዘንድ፡ነው። 25፤ጭፍራዎችም፡እንዲህ፡አደረጉ።ነገር፡ግን፥በኢየሱስ፡መስቀል፡አጠገብ፡እናቱ፥የእናቱም፡ እኅት፥የቀለዮጳም፡ሚስት፡ማርያም፥መግደላዊትም፡ማርያም፡ቆመው፡ነበር። 26፤ኢየሱስም፡እናቱን፡ይወደ፟ው፡የነበረውንም፡ደቀ፡መዝሙር፡በአጠገቡ፡ቆሞ፡ባየ፡ጊዜ፡እናቱን፦አንቺ፡ ሴት፥እንሆ፥ልጅሽ፡አላት። 27፤ከዚህ፡በዃላ፡ደቀ፡መዝሙሩን፦እናትኽ፡እንሇት፡አለው።ከዚህም፡ሰዓት፡ዠምሮ፡ደቀ፡መዝሙሩ፡ወደ፡ቤቱ፡ወሰዳት። 28፤ከዚህ፡በዃላ፡ኢየሱስ፡አኹን፡ዅሉ፡እንደተፈጸመ፡ዐውቆ፥የመጽሐፉ፡ቃል፡ይፈጸም፡ ዘንድ፦ተጠማኹ፡አለ። 29፤በዚያም፡ሖምጣጤ፡የሞላበት፡ዕቃ፡ተቀምጦ፡ነበር፤እነርሱም፡ሖምጣጤውን፡በሰፍነግ፡ሞልተው፡ በሁሶፕም፡አድርገው፡ወደ፡አፉ፡አቀረቡለት። 30፤ኢየሱስም፡ሖምጣጤውን፡ከተቀበለ፡በዃላ፦ተፈጸመ፡አለ፥ራሱንም፡አዘንብሎ፡ነፍሱን፡አሳልፎ፡ሰጠ። 31፤አይሁድም፡የማዘጋጀት፡ቀን፡ስለ፡ኾነ፡ያ፡ሰንበት፡ትልቅ፡ነበረና፡ሥጋቸው፡በሰንበት፡በመስቀል፡ላይ፡ እንዳይኖር፥ጭናቸውን፡ሰብረው፡እንዲያወርዷቸው፡ጲላጦስን፡ለመኑት። 32፤ጭፍራዎችም፡መጥተው፡የፊተኛውን፡ጭን፡ከርሱም፡ጋራ፡የተሰቀለውን፡የሌላውን፡ጭን፡ሰበሩ፤ 33፤ወደ፡ኢየሱስ፡በመጡ፡ጊዜ፡ግን፡ርሱ፡ፈጽሞ፡እንደ፡ሞተ፡አይተው፡ጭኑን፡አልሰበሩም፤ 34፤ነገር፡ግን፥ከጭፍራዎች፡አንዱ፡ጐኑን፡በጦር፡ወጋው፤ወዲያውም፡ደምና፡ውሃ፡ወጣ። 35፤ያየውም፡መስክሯል፤ምስክሩም፡እውነት፡ነው፤እናንተም፡ደግሞ፡ታምኑ፡ዘንድ፡ርሱ፡እውነት፡ እንዲናገር፡ያውቃል። 36፤ይህ፡የኾነ፦ከርሱ፡ዐጥንት፡አይሰበርም፡የሚል፡የመጽሐፉ፡ቃል፡እንዲፈጸም፡ነው። 37፤ደግሞም፡ሌላው፡መጽሐፍ፦የወጉትን፡ያዩታል፡ይላል። 38፤ከዚህም፡በዃላ፡አይሁድን፡ስለ፡ፈራ፡በስውር፡የኢየሱስ፡ደቀ፡መዝሙር፡የነበረ፡የአርማትያስ፡ዮሴፍ፡ የኢየሱስን፡ሥጋ፡ሊወስድ፡ጲላጦስን፡ለመነ፤ጲላጦስም፡ፈቀደለት።ስለዚህም፡መጥቶ፡የኢየሱስን፡ሥጋ፡ ወሰደ። 39፤ደግሞም፡አስቀድሞ፡በሌሊት፡ወደ፡ኢየሱስ፡መጥቶ፡የነበረ፡ኒቆዲሞስ፡መቶ፡ንጥር፡የሚያኽል፡የከርቤና፡ የሬት፡ቅልቅል፡ይዞ፡መጣ። 40፤የኢየሱስንም፡ሥጋ፡ወስደው፥እንደ፡አይሁድ፡አገናነዝ፡ልማድ፥ከሽቱ፡ጋራ፡በተልባ፡እግር፡ልብስ፡ ከፈኑት። 41፤በተሰቀለበትም፡ስፍራ፡አትክልት፡ነበረ፥በአትክልቱም፡ማንም፡ገና፡ያልተቀበረበት፡ዐዲስ፡መቃብር፡ነበረ። 42፤ስለዚህ፥መቃብሩ፡ቅርብ፡ነበረና፥ስለ፡አይሁድ፡ማዘጋጀት፡ቀን፡ኢየሱስን፡በዚያ፡አኖሩት።

ምዕራፍ ፳ ለማስተካከል

1፤ከሳምንቱም፡በፊተኛው፡ቀን፥መግደላዊት፡ማርያም፥ገና፡ጨለማ፡ሳለ፡ማለዳ፡ወደ፡መቃብር፡ መጣች፤ድንጋዩም፡ከመቃብሩ፡ተፈንቅሎ፡አየች። 2፤እየሮጠችም፡ወደ፡ስምዖን፡ጴጥሮስና፥ኢየሱስ፡ይወደ፟ው፡ወደ፡ነበረው፣ወደ፡ሌላው፡ደቀ፡መዝሙር፡ መጥታ፦ጌታን፡ከመቃብር፡ወስደውታል፥ወዴትም፡እንዳኖሩት፡አናውቅም፡አለቻቸው። 3፤ስለዚህ፥ጴጥሮስና፡ሌላው፡ደቀ፡መዝሙር፡ወጥተው፡ወደ፡መቃብሩ፡ኼዱ። 4፤ኹለቱም፡ዐብረው፡ሮጡ፤ሌላው፡ደቀ፡መዝሙርም፡ከጴጥሮስ፡ይልቅ፡ፈጥኖ፡ወደ፡ፊት፡ሮጠና፡ አስቀድሞ፡ከመቃብሩ፡ደረሰ፤ 5፤ዝቅም፡ብሎ፡ቢመለከት፡የተልባ፡እግሩን፡ልብስ፡ተቀምጦ፡አየ፥ነገር፡ግን፥አልገባም። 6፤ስምዖን፡ጴጥሮስም፡ተከትሎት፡መጣ፡ወደ፡መቃብሩም፡ገባ፤የተልባ፡እግሩን፡ልብስ፡ተቀምጦ፡አየ፥ 7፤ደግሞም፡በራሱ፡የነበረውን፡ጨርቅ፡ለብቻው፡ባንድ፡ስፍራ፡ተጠምጥሞ፡እንደ፡ነበረ፡እንጂ፡ከተልባ፡ እግሩ፡ልብስ፡ጋራ፡ተቀምጦ፡እንዳልነበረ፡አየ። 8፤በዚያን፡ጊዜ፡አስቀድሞ፡ወደ፡መቃብር፡የመጣውም፡ሌላው፡ደቀ፡መዝሙር፡ደግሞ፡ ገባ፥አየም፥አመነም፤ 9፤ከሙታን፡ይነሣ፡ዘንድ፡እንዲገባው፡የሚለውን፡የመጽሐፉን፡ቃል፡ገና፡አላወቁም፡ነበርና። 10፤ደቀ፡መዛሙርቱም፡ወደ፡ቤታቸው፡ደግሞ፡ኼዱ። 11፤ማርያም፡ግን፡እያለቀሰች፡ከመቃብሩ፡በስተውጭ፡ቆማ፡ነበር።ስታለቅስም፡ወደ፡መቃብር፡ዝቅ፡ብላ፡ ተመለከተች፤ 12፤ኹለት፡መላእክትም፡ነጭ፡ልብስ፡ለብሰው፡የኢየሱስ፡ሥጋ፡ተኝቶበት፡በነበረው፡አንዱ፡በራስጌ፡ሌላውም፡በእግርጌ፡ተቀምጠው፡አየች። 13፤እነርሱም፦አንቺ፡ሴት፥ስለ፡ምን፡ታለቅሻለሽ፧አሏት።ርሷም፦ጌታዬን፡ወስደውታል፡ወዴትም፡ እንዳኖሩት፡አላውቅም፡አለቻቸው። 14፤ይህንም፡ብላ፡ወደ፡ዃላ፡ዘወር፡ስትል፡ኢየሱስን፡ቆሞ፡አየችው፤ኢየሱስም፡እንደ፡ኾነ፡አላወቀችም። 15፤ኢየሱስም፦አንቺ፡ሴት፥ስለ፡ምን፡ታለቅሻለሽ፧ማንንስ፡ትፈልጊያለሽ፧አላት።ርሷም፡የአትክልት፡ ጠባቂ፡መስሏት፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡ወስደኸው፡እንደ፡ኾንኽ፡ወዴት፡እንዳኖርኸው፡ንገረኝ፡እኔም፡ እወስደዋለኹ፡አለችው። 16፤ኢየሱስም፦ማርያም፡አላት።ርሷ፡ዘወር፡ብላ፡በዕብራይስጥ፦ረቡኒ፡አለችው፤ትርጓሜውም፦መምህር፡ ሆይ፡ማለት፡ነው። 17፤ኢየሱስም፦ገና፡ወደ፡አባቴ፡አላረግኹምና፡አትንኪኝ፤ነገር፡ግን፥ወደ፡ወንድሞቼ፡ኼደሽ፦እኔ፡ወደ፡ አባቴና፡ወደ፡አባታችኹ፡ወደ፡አምላኬና፡ወደ፡አምላካችኹ፡ዐርጋለኹ፡ብለሽ፡ንገሪያቸው፡አላት። 18፤መግደላዊት፡ማርያም፡መጥታ፡ጌታን፡እንዳየች፡ይህንም፡እንዳላት፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ነገረች። 19፤ያም፡ቀን፡ርሱም፡ከሳምንቱ፡ፊተኛው፡በመሸ፡ጊዜ፥ደቀ፡መዛሙርቱ፡ተሰብስበው፡ በነበሩበት፥አይሁድን፡ስለ፡ፈሩ፡ደጆቹ፡ተዘግተው፡ሳሉ፥ኢየሱስ፡መጣ፤በመካከላቸውም፡ቆሞ፦ሰላም፡ ለእናንተ፡ይኹን፡አላቸው። 20፤ይህንም፡ብሎ፡እጆቹንም፡ጐኑንም፡አሳያቸው።ደቀ፡መዛሙርቱም፡ጌታን፡ባዩ፡ጊዜ፡ደስ፡አላቸው። 21፤ኢየሱስም፡ዳግመኛ፦ሰላም፡ለእናንተ፡ይኹን፤አብ፡እንደ፡ላከኝ፡እኔ፡ደግሞ፡እልካችዃለኹ፡አላቸው። 22፤ይህንም፡ብሎ፡እፍ፡አለባቸውና፦መንፈስ፡ቅዱስን፡ተቀበሉ። 23፤ኀጢአታቸውን፡ይቅር፡ያላችዃቸው፡ዅሉ፡ይቀርላቸዋል፤የያዛችኹባቸው፡ተይዞባቸዋል፡አላቸው። 24፤ነገር፡ግን፥ከዐሥራ፡ኹለቱ፡አንዱ፡ዲዲሞስ፡የሚሉት፡ቶማስ፡ኢየሱስ፡በመጣ፡ጊዜ፡ከነርሱ፡ጋራ፡ አልነበረም። 25፤ሌላዎቹም፡ደቀ፡መዛሙርቱ፦ጌታን፡አይተነዋል፡አሉት።ርሱ፡ግን፦የችንካሩን፡ምልክት፡በእጆቹ፡ ካላየኹ፡ጣቴንም፡በችንካሩ፡ምልክት፡ካላገባኹ፡እጄንም፡በጐኑ፡ካላገባኹ፡አላምንም፡አላቸው። 26፤ከስምንት፡ቀን፡በዃላም፡ደቀ፡መዛሙርቱ፡ደግመው፡በውስጥ፡ነበሩ፥ቶማስም፡ከነርሱ፡ጋራ፡ ነበረ።ደጆች፡ተዘግተው፡ሳሉ፡ኢየሱስ፡መጣ፤በመካከላቸውም፡ቆሞ፦ሰላም፡ለእናንተ፡ይኹን፡አላቸው። 27፤ከዚያም፡በዃላ፡ቶማስን፦ጣትኽን፡ወደዚህ፡አምጣና፡እጆቼን፡እይ፤እጅኽንም፡አምጣና፡በጐኔ፡ አግባው፤ያመንኽ፡እንጂ፡ያላመንኽ፡አትኹን፡አለው። 28፤ቶማስም፦ጌታዬ፡አምላኬም፡ብሎ፡መለሰለት። 29፤ኢየሱስም፦ስላየኸኝ፡አምነኻል፤ሳያዩ፡የሚያምኑ፡ብፁዓን፡ናቸው፡አለው። 30፤ኢየሱስም፡በዚህ፡መጽሐፍ፡ያልተጻፈ፡ሌላ፡ብዙ፡ምልክት፡በደቀ፡መዛሙርቱ፡ፊት፡አደረገ፤ 31፤ነገር፡ግን፥ኢየሱስ፡ርሱ፡ክርስቶስ፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡እንደ፡ኾነ፡ታምኑ፡ዘንድ፥አምናችኹም፡ በስሙ፡ሕይወት፡ይኾንላችኹ፡ዘንድ፡ይህ፡ተጽፏል።

ምዕራፍ ፳፩ ለማስተካከል

1፤ከዚህ፡በዃላ፡ኢየሱስ፡በጥብርያዶስ፡ባሕር፡አጠገብ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡እንደ፡ገና፡ተገለጠላቸው፤ 2፤እንዲህም፡ተገለጠ።ስምዖን፡ጴጥሮስና፡ዲዲሞስ፡የሚባለው፡ቶማስ፡ከገሊላ፡ቃና፡የኾነ፡ናትናኤልም፡ የዘብዴዎስም፡ልጆች፡ከደቀ፡መዛሙርቱም፡ሌላዎች፡ኹለት፡በአንድነት፡ነበሩ። 3፤ስምዖን፡ጴጥሮስ፦ዓሣ፡ላጠምድ፡እኼዳለኹ፡አላቸው።እነርሱም፦እኛም፡ከአንተ፡ጋራ፡እንመጣለን፡ አሉት።ወጥተውም፡ወደ፡ታንኳዪቱ፡ገቡ፡በዚያችም፡ሌሊት፡ምንም፡አላጠመዱም። 4፤በነጋም፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡በባሕር፡ዳር፡ቆመ፤ደቀ፡መዛሙርቱ፡ግን፡ኢየሱስ፡መኾኑን፡አላወቁም። 5፤ኢየሱስም፦ልጆች፡ሆይ፥አንዳች፡የሚበላ፡አላችኹን፧አላቸው።የለንም፡ብለው፡መለሱለት። 6፤ርሱም፦መረቡን፡በታንኳዪቱ፡በስተቀኝ፡ጣሉት፡ታገኙማላችኹ፡አላቸው።ስለዚህ፡ጣሉት፤በዚህም፡ጊዜ፡ ከዓሣው፡ብዛት፡የተነሣ፡ሊጐትቱት፡አቃታቸው። 7፤ኢየሱስ፡ይወደ፟ው፡የነበረውም፡ደቀ፡መዝሙር፡ጴጥሮስን፦ጌታ፡እኮ፡ነው፡አለው።ስለዚህ፡ስምዖን፡ ጴጥሮስ፡ጌታ፡መኾኑን፡በሰማ፡ጊዜ፡ዕራቍቱን፡ነበረና፥ልብሱን፡ታጥቆ፡ወደ፡ባሕር፡ራሱን፡ጣለ። 8፤ሌላዎቹ፡ደቀ፡መዛሙርት፡ግን፡ከምድር፡ኹለት፡መቶ፡ክንድ፡ያኽል፡እንጂ፡እጅግ፡አልራቁም፡ ነበርና፥ዓሣ፡የሞላውን፡መረብ፡እየሳቡ፡በጀልባ፡መጡ። 9፤ወደ፡ምድርም፡በወጡ፡ጊዜ፡ፍምና፡ዓሣ፡በላዩ፡ተቀምጦ፡እንጀራም፡አዩ። 10፤ኢየሱስም፦አኹን፡ካጠመዳችኹት፡ዓሣ፡አምጡ፡አላቸው። 11፤ስምዖን፡ጴጥሮስም፡ወደ፡ጀልባዪቱ፡ገብቶ፡መቶ፡ዐምሳ፡ሦስት፡ታላላቅ፡ዓሣዎች፡ሞልቶ፡የነበረውን፡ መረብ፡ወደ፡ምድር፡ጐተተ፤ይህንም፡ያኽል፡ብዙ፡ሲኾን፡መረቡ፡አልተቀደደም። 12፤ኢየሱስም፦ኑ፥ምሳ፡ብሉ፡አላቸው።ከደቀ፡መዛሙርቱ፡አንድ፡ስንኳ፦አንተ፡ማን፡ነኽ፧ብሎ፡ ሊመረምረው፡የደፈረ፡አልነበረም፤ጌታ፡መኾኑን፡ዐውቀው፡ነበርና። 13፤ኢየሱስም፡መጣና፡እንጀራ፡አንሥቶ፡ሰጣቸው፥እንዲሁም፡ዓሣውን። 14፤ኢየሱስ፡ከሙታን፡ከተነሣ፡በዃላ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ሲገለጥላቸው፡ይህ፡ሦስተኛው፡ጊዜ፡ነበረ። 15፤ምሳ፡ከበሉ፡በዃላም፡ኢየሱስ፡ስምዖን፡ጴጥሮስን፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥ከነዚህ፡ይልቅ፡ ትወደኛለኽን፧አለው፦አዎን፡ጌታ፡ሆይ፥እንድወድኽ፡አንተ፡ታውቃለኽ፡አለው፦ግልገሎቼን፡አሰማራ፡ አለው። 16፤ደግሞ፡ኹለተኛ፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥ትወደኛለኽን፧አለው፦አዎን፡ጌታ፡ሆይ፥እንድወድኽ፡ አንተ፡ታውቃለኽ፡አለው፦ጠቦቶቼን፡ጠብቅ፡አለው። 17፤ሦስተኛ፡ጊዜ፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥ትወደኛለኽን፧አለው።ሦስተኛ፦ትወደኛለኽን፧ስለ፡አለው፡ ጴጥሮስ፡ዐዘነና፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡ዅሉን፡ታውቃለኽ፤እንድወድኽ፡አንተ፡ታውቃለኽ፡ አለው።ኢየሱስም፦በጎቼን፡አሰማራ። 18፤እውነት፡እውነት፡እልኻለኹ፥አንተ፡ጕልማሳ፡ሳለኽ፡ወገብኽን፡በገዛ፡ራስኽ፡ታጥቀኽ፡ወደምትወደ፟ው፡ ትኼድ፡ነበር፤ነገር፡ግን፥በሸመገልኽ፡ጊዜ፡እጆችኽን፡ትዘረጋለኽ፥ሌላውም፡ያስታጥቅኻል፡ ወደማትወደ፟ውም፡ይወስድኻል፡አለው። 19፤በምን፡ዐይነት፡ሞት፡እግዚአብሔርን፡ያከብር፡ዘንድ፡እንዳለው፡ሲያመለክት፡ይህን፡አለ።ይህንም፡ ብሎ፦ተከተለኝ፡አለው። 20፤ጴጥሮስም፡ዘወር፡ብሎ፡ኢየሱስ፡ይወደ፟ው፡የነበረውን፡ደቀ፡መዝሙር፡ሲከተለው፡አየ፤ርሱም፡ደግሞ፡ በእራት፡ጊዜ፡በደረቱ፡ተጠግቶ፦ጌታ፡ሆይ፥አሳልፎ፡የሚሰጥኽ፡ማን፡ነው፧ያለው፡ነበረ። 21፤ጴጥሮስም፡ይህን፡አይቶ፡ኢየሱስን፦ጌታ፡ሆይ፥ይህስ፡እንዴት፡ይኾናል፧አለው። 22፤ኢየሱስም፦እስክመጣ፡ድረስ፡ይኖር፡ዘንድ፡ብወድስ፥ምን፡አግዶኽ፧አንተ፡ተከተለኝ፡አለው። 23፤ስለዚህ፦ያ፡ደቀ፡መዝሙር፡አይሞትም፡የሚለው፡ይህ፡ነገር፡ወደ፡ወንድሞች፡ወጣ፤ነገር፡ ግን፥ኢየሱስ፦እስክመጣ፡ድረስ፡ይኖር፡ዘንድ፡ብወድስ፡ምን፡አግዶኽ፧አለው፡እንጂ፡አይሞትም፡ አላለውም። 24፤ስለ፡እነዚህም፡የመሰከረ፡ይህንንም፡ጽፎ፡ያለ፡ይህ፡ደቀ፡መዝሙር፡ነው፥ምስክሩም፡እውነት፡እንደ፡ ኾነ፡እናውቃለን። 25፤ኢየሱስም፡ያደረገው፡ብዙ፡ሌላ፡ነገር፡ደግሞ፡አለ፤ዅሉ፡በያንዳንዱ፡ቢጻፍ፡ለተጻፉት፡መጻሕፍት፡ ዓለም፡ራሱ፡ባልበቃቸውም፡ይመስለኛል፨

  1. ^ ወንጌል አንድምታ Archived ጃንዩዌሪ 8, 2019 at the Wayback Machine ይመልከቱ
  2. ^ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ወንጌል አንድምታን Archived ጃንዩዌሪ 8, 2019 at the Wayback Machineደበሎ ድህረገፅ ላይ ይመልከቱ