የሸክላ ማጫወቻ በቀድሞው ክፍለ ዘመን አይነተኛ የሙዚቃ ወይም ድምጽ ማጫወቻ ዘዴ ነበር።

የ1960ዎች ሸክላ ማጫወቻ እና ራዲዮን
ኤዲሶን እና አዲስ ፍጥረቱ ፎኖግራፉ በ1870 ዓም

መጀመርያ በ1870 ዓም በአሜሪካዊቶማስ ኤዲሶን ተፈጥሮ «ፎኖግራፍ» ሲባል ድምጹ የተቀረጸበት በሰም ወረቀት ላይ ነበር። በጊዜ ላይ አሠራሩ በጣም ተሻሽሎ ድምጾች በሙዚቃ ሸክላ ላይ ይቀረጹ ነበር።

1980ዎቹ ጀምሮ ግን አዳዲስ ፈጠራዎች እንደ ካሴት ወይም ሲዲ ተገኝተው የሸክላ ማጫወቻ ጥቅም በአሁኑ ሰዓት እጅግ ተቀንሷል።