የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፭

ዘቅዱስ ሕርያቆስ

የማርያም ቅዳሴ ገፅ ፭

ዘቅዱስ ሕርያቆስ


፳፬ ፤ እናስተውል ።
፳፭ ፤ አንቺን የወደደ እግዚአብሔር አብ ቅዱስነው ፣ በመኀፀንሽ ያደረ ወልድ ዋህድም ቅዱስ ነው ፣ ያጸናሽም የጽድቅ መንፈስ ጰራቅሊጦስ ቅዱስ ነው ።
፳፮ ፤ ተሰጥዎውን መልሱ ።
፳፯ ፤ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ፍጹም አሸናፊ እግዚአብሔር የጌትነትህ ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው ።
፳፰ ፤ ምስጋናን የተመላሽ ድንግል ሆይ በማንና በማንስ ምሳሌ እንመስልሻለን ። አማኑኤልየማይተረጎም የሥጋን ልብስነት ከአንቺ የለበሳት መሣሪያ ነሽ ። ዝሐውን ከአዳም ጥንተ ሥጋ አደረገ ማጉም ያንቺ ሥጋ ነው ። መወርወሪያውም ቃል እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። መሕኑም ከልዕልና የወረደ የልዑል እግዚአብሔር አምሳል ነው ሠሪውም መንፈስ ቅዱስ ነው ።
፳፱ ፤ ወዮ ይህ ነገር ዕፁብ ድንቅ ነው የቀደሙ አባቶች ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገሩብሽ ድልድይ ሆይ ከምድር እስከ ሰማይ የምትደርሽ መሰላል ሆይ የፍጥረት ሁሉ መጀመሪያ ባንቺ ታደሰ ።
፴ ፤ ከገነት በተሰደደ ጊዜ ለአዳም ተስፋው አንቺ ነሽ ። በግፍ የተገደለ የአቤል የውሃቱ አንቺ ነሽ ። የሴት ቸርነት አንቺ ነሽ ። የሄኖክም ሥራዎቹ ከክፉ ጥፋት የዳነባት ። የኖህ መርከብ ፣ የሴም ቡራኬ ዕድል ፈንታውም አንቺ ነሽ ።
፴፩ ፤ የአብርሃም እንግድነት የያዕቆብ መሰላል አንቺ ነሽ ። ዮሴፍን የምታረጋጊው አንቺ ነሽ ።