ዋጊኖስ ወይም የደጋ አባሎ ባለጠጕር፣ ሥሩና ፍሬው ለደም ተቅማጥ መድኀኒት ይኾናል። ቅጠሉም ቀጥቅጦ በውሃ ዘፍዝፎ ብልትንና ዐይንን ፡ እንዳይነካ ተጠንቅቆ ገላን ቢቀቡት ከዕከክ ያድናል ። ሌላ ስሙ ጉፋ ይባላል ። [ነገር ስም] ትንሽ ቍጥቋጦ ዕንጨት የይፋት አባሎ ፍሬው ለቍስል የሚኾን።

ዋጊኖስ

የተክሉ ሳይንሳዊ ጸባይ ለማስተካከል

ቊጥቋጡ ወይም ዛፉ እስከ ፯ ሜትር ድረስ ይበቅላል።

አስተዳደግ ለማስተካከል

በብዛት የሚገኝበት መልክዓ ምድር ለማስተካከል

በከፊል እርጥበት ባላቸው ጫካዎች ወይም በወይና ደጋ በተፈጁ መስኮች ላይ በጣም ተራ ቊጥቋጥ ነው።

የተክሉ ጥቅም ለማስተካከል

ጸጉሩ ተመልጦ አላድግ ላለ ለራሰ በረሀ የኑግና የዋጊኖስ ቅጠል በአንድነት ወቅጦ ጨምቆ ጠዋት ጠዋት ለሰባት ቀን ሳያቋርጡ መቀባት ተመልሶ ጸጉር እንዲበቅል ያደርጋል፡፡ ቅድመ ጥንቃቄ የዋጊኖሱን ቅጠል ነክቶ አይን መንካት የተከለከለ ነዉ፡፡ከጥንቷዊዉ የአባቶቻችን የህክምና መጽሐፍ ከዕፀ ደብዳቤ የተገኘ፡፡

የቆዳ ችግሮችንና፣ ቁምጥናን፣ ቁስሎችንም ለማከም፣ የተደቀቁት ቅጠሎች ወይም ዘሮች ከቅቤ ጋር ይቀላቀላል።

የሥሮቹና የፍሬዎቹ የተፈላ ልጥ በተቅማጥወባ ላይ ያክማል።

ቢጫ-ቀይ ፍሬዎቹ በከብት በተለይም በበግ ቢበላ ገዳይ መርዝ እንደ ሆነ ተብሏል።

የተክሉ መረቅ የከብቶችን ማበጥ ለማከም እንደ ጠቀመ ተብሏል።[1]

ዕከክን ለማከም፣ የዋጊኖስና የሽነት ቅጠል እና የጌሾ ዘር ተደቅቆ በቅቤ ለጥፍ ይለጠፋል።

የአባለዘር በሽቶችን ለማከም፣ የዋጊኖስ ዘርና የጤፍ ዘር በውሃ ተጋግሮ በለጥፍ ይለጠፋል።[2]

ፍቼ ወረዳ እንደ ተዘገበ፣ ለእከክ ወይም ለችፌ፣ ቅጠሉ ተደቅቆ ለ፫ ቀን በውሃ ውስጥ ከቆየ በኋላ እንደ መታጠቢያ ይጠቀማል። ለውሻ በሽታ ቅጠሉ በቀጥታ ይበላል፤ ለማስታወክ፣ የደረቀው ቅጠል እንደ ጢስ በአፍንጫ ይናፈሳል።[3]

ዘጌ እንደ ተዘገበ፦ ለ«ቡላድ»፦ የፍሬ ዱቄት በማር ፩ ሳምንት ተቡኮ ይበላል። ለችፌ፦ የልጥና የቅቤ ለጥፍ ይቀባል። ለተቅማጥ፦ የቅጠል ጭማቂ በጧት ይጠጣል። ለ«አህያ ኪንታሮት»፦ የፍሬው ዱቄት በወተት ለ፫ ቀን ይጠጣል። ለ«ሙሽሮ»፦ የሥሩ ዱቄት በማር ይጠጣል።።[4]

ማጣቀሻ ለማስተካከል

  • "Brucea antidysentrica". Encyclopaedia of the History of Science, Technology, and Medicine in Non-Western Cultures፣ Helaine Selin፣ እ.ኤ.አ ፳፻፰ ዓ.ም፣ ገጽ ፰፻፴፯
  1. ^ አማረ ጌታሁን - SOME COMMON MEDICINAL AND POISONOUS PLANTS USED IN ETHIOPIAN FOLK MEDICINE Archived ጁላይ 31, 2017 at the Wayback Machine March 1976 እ.ኤ.አ.
  2. ^ በደብረ ሊባኖስ ዙሪያ ያለው ሕዝብ መድሃኒታዊ እጾች እውቀናና ጥቅም 1998 ዓም ከጥላሁን ተክለሃይማኖት፣ ሚሩጸ ጊዳይ፣ ግርማይ መድኅን፣ ያለም መኮነን፣ አዲስ አበባ ዩኒቬርሲቴ፣ አክሊሉ ለማ ተቋም
  3. ^ የፍቼ፣ ኦሮሚያ ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 2006 ዓም ከዓቢዩ እኒየው እና ሌሎች፣ ጎንደርና አዲስ አበባ ኡኒቨርሲቲዎች ሥነ ፍጥረት ኮሌጆች
  4. ^ የዘጌ ልሳነ ምድር ባህላዊ መድሃኒት ጥናት 1999 ዓም ከጥላሁን ተክለሃይማኖት፣ ሚሩጸ ጊዳይ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ