ወደ ሮማውያን በአዲስ ኪዳን የመጀመሪያው መልዕክት ሲሆን ቅዱስ ጳውሎስ በቆሮንጦስ እያለ በ፶ ዎቹ ዓ.ም. የጻፈው መልዕክት ነው ። ይህ ምዕራፍ ፲፭ ሲሆን በ፴፫ ንዑስ ክፍሎች ይከፈላል ። ጳውሎስ በዚህ መልዕክቱ በምዕራፍ ፲፬ ያለውን መልክት በመቀጠል የእግዚአብሔርን ቃል እንደ ምግብ በየዕለቱ መቀለብ በመንፈስ ቅዱስ መሞላትንና በእምነት ጠንካራ እደሚያደርግ ያስተምራል።

ወደ ሮማውያን ፲፭
በ፫ኛው ክፍለ ዘመን የተጻፈ ወደ ሮማውያን ፲፭:፳፮-፳፯ ወደ ሮማውያን ፲፭:፴፪-፴፫ በኮዴክስ ካሮሊነስ
አጭር መግለጫ
ፀሐፊ ጳውሎስ
የመጽሐፍ ዐርስት ወደ ሮማውያን
የሚገኘው በአዲስ ኪዳን ፮ኛው መጽሐፍ
መደብ የጳውሎስ መልዕክት


ቅዱስ ጳውሎስ ለሮማውያን መልዕክቱን የጻፈበት ምክኒያት አይሁዳውያንና ሮማውያን በሰላም አንድላይ በሮም ለብዙ ዘመን ሲኖሩ ቆይተው ክርስትና በተመሠረተበት ወቅት ፣ አይሁዳውያን ክርስቶስ እኛን ነው የመረጠን ለመንግሥቱ እናንተን አይደለም... ሲሊ ሮማውያን ደግሞ እናንተ ሰቀላችሁት እንጂ ምን አረጋቹህለት... እየተባባሉ እርስበርሳቸው ጥል ስለፈጠሩ እነሱን ለማስታረቅ ጻፈው ።

የጳውሎስ መልዕክት ወደ ሮማውያን ምዕራፍ ፲፭

ቁጥር ፩ - ፲ ለማስተካከል

1፤እኛም፡ኀይለኛዎች፡የኾን፟፡የደካማዎችን፡ድካም፡እንድንሸከም፡ራሳችንንም፡ደስ፡እንዳናሠኝ፡ይገ፟ባ፟ናል። 2፤እያንዳንዳችን፡እንድናንጸው፡ርሱን፡ለመጥቀም፡ባልንጀራችንን፡ደስ፡እናሠኝ። 3፤ክርስቶስ፡ራሱን፡ደስ፡አላሠኘምና፤ነገር፡ግን፦አንተን፡የነቀፉበት፡ነቀፋ፡ወደቀብኝ፡ተብሎ፡እንደ፡ ተጻፈ፡ኾነበት። 4፤በመጽናትና፡መጻሕፍት፡በሚሰጡት፡መጽናናት፡ተስፋ፡ይኾንልን፡ዘንድ፡አስቀድሞ፡የተጻፈው፡ዅሉ፡ለትምህርታችን፡ተጽፏልና። 5-6፤ባንድ፡ልብ፡ኾናችኹ፡ባንድ፡አፍ፡እግዚአብሔርን፥ርሱም፡የጌታችን፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ አባት፥ታከብሩ፡ዘንድ፥የትዕግሥትና፡የመጽናናት፡አምላክ፡እንደክርስቶስ፡ኢየሱስ፡ፈቃድ፡ርስ፡በርሳችኹ፡ ባንድ፡ዐሳብ፡መኾንን፡ይስጣችኹ። 7፤ስለዚህ፥ክርስቶስ፡ለእግዚአብሔር፡ክብር፡እንደ፡ተቀበላችኹ፡እንዲሁ፡ርስ፡በርሳችኹ፡ተቀባበሉ። 8-9፤ለአባቶች፡የተሰጠውን፡የተስፋ፡ቃል፡ያጸና፡ዘንድ፡ደግሞም፦ስለዚህ፡በአሕዛብ፡መካከል፡ አመሰግንኻለኹ፡ለስምኽም፡እዘምራለኹ፡ተብሎ፡እንደ፡ተጻፈ፥አሕዛብ፡ስለ፡ምሕረቱ፡እግዚአብሔርን፡ ያከብሩ፡ዘንድ፥ክርስቶስ፡ስለእግዚአብሔር፡እውነት፡የመገረዝ፡አገልጋይ፡ኾነ፡እላለኹ። 10፤ደግሞም፦አሕዛብ፡ሆይ፥ከሕዝቡ፡ጋራ፡ደስ፡ይበላችኹ፡ይላል።

ቁጥር ፲ - ፳ ለማስተካከል

11፤ደግሞም፦እናንተ፡አሕዛብ፡ዅላችኹ፥ጌታን፡አመስግኑ፡ሕዝቦቹም፡ዅሉ፡ይወድሱት፡ይላል። 12፤ደግሞም፡ኢሳይያስ፦የእሴይ፡ሥር፡አሕዛብንም፡ሊገዛ፡የሚነሣው፡ይኾናል፤በርሱ፡አሕዛብ፡ተስፋ፡ ያደርጋሉ፡ይላል። 13፤የተስፋ፡አምላክም፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ኀይል፡በተስፋ፡እንድትበዙ፡በማመናችኹ፡ደስታንና፡ሰላምን፡ዅሉ፡ ይሙላባችኹ። 14፤እኔም፡ራሴ፡ደግሞ፥ወንድሞቼ፡ሆይ፥በበጎነት፡ራሳችኹ፡እንደ፡ተሞላችኹ፥ዕውቀትም፡ዅሉ፡እንደ፡ ሞላባችኹ፥ርስ፡በርሳችኹም፡ደግሞ፡ልትገሠጹ፡እንዲቻላችኹ፡ስለ፡እናንተ፡ተረድቻለኹ። 15-16፤ነገር፡ግን፥አሕዛብ፡በመንፈስ፡ቅዱስ፡ተቀድሰው፡የተወደደ፡መሥዋዕት፡ሊኾኑ፥ለእግዚአብሔር፡ ወንጌል፡እንደ፡ካህን፡እያገለገልኹ፥ለአሕዛብ፡የክርስቶስ፡ኢየሱስ፡አገልጋይ፡እኾን፡ዘንድ፡ከእግዚአብሔር፡በተሰጠኝ፡ጸጋ፡ምክንያት፡ተመልሼ፡ላሳስባችኹ፡ብዬ፡በአንዳንድ፡ቦታ፡በድፍረት፡ጻፍኹላችኹ። 17፤እንግዲህ፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡በሚኾን፡ነገር፡በክርስቶስ፡ኢየሱስ፡ትምክሕት፡አለኝ። 18-19፤አሕዛብ፡እንዲታዘዙ፡ክርስቶስ፡በቃልና፡በሥራ፥በምልክትና፡በድንቅ፡ነገር፡ኀይል፥በመንፈስ፡ ቅዱስም፡ኀይል፡በእኔ፡አድርጎ፡ከሠራው፡በቀር፡ምንም፡ልናገር፡አልደፍርም፤ስለዚህ፥ከኢየሩሳሌም፡ዠምሬ፡ እስከ፡እልዋሪቆን፡ድረስ፡እየዞርኹ፡የክርስቶስን፡ወንጌል፡ፈጽሜ፤ሰብኬያለኹ። 20፤እንዲሁም፡በሌላው፡ሰው፡መሠረት፡ላይ፡እንዳልሠራ፡የክርስቶስ፡ስም፡በተጠራበት፡ስፍራ፡ሳይኾን፡ ወንጌልን፡ለመስበክ፡ተጣጣርኹ፤

ቁጥር ፳፩ - ፴፫ ለማስተካከል

21፤ነገር፡ግን፦ስለ፡ርሱ፡ያልተወራላቸው፡ያያሉ፥ያልሰሙም፡ያስተውላሉ፡ተብሎ፡እንደ፡ተጻፈ፡ነው። 22፤ስለዚህ፡ደግሞ፡ወደ፡እናንተ፡እንዳልመጣ፡ብዙ፡ጊዜ፡ተከለከልኹ። 23፤አኹን፡ግን፡በዚህ፡አገር፡ስፍራ፡ወደ፡ፊት፡ስለሌለኝ፥ከብዙ፡ዓመትም፡ዠምሬ፡ወደ፡እናንተ፡ልመጣ፡ ናፍቆት፡ስለ፡አለኝ፥ 24፤ወደ፡እስጳንያ፡በኼድኹ፡ጊዜ፡ሳልፍ፡እናንተን፡እንዳይ፥አስቀድሜም፡ጥቂት፡ብጠግባችኹ፡ወደዚያ፡ በጕዞዬ፡እንድትረዱኝ፡ተስፋ፡አደርጋለኹ። 25፤አኹን፡ግን፡ቅዱሳንን፡ለማገልገል፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡እኼዳለኹ። 26፤መቄዶንያና፡አካይያ፡በኢየሩሳሌም፡ቅዱሳን፡መካከል፡ያሉትን፡ድኻዎች፡ይረዱ፡ዘንድ፡ወደዋልና። 27፤ወደዋልና፥የእነርሱም፡ባለዕዳዎች፡ናቸው፤አሕዛብ፡በእነርሱ፡መንፈሳዊ፡ነገርን፡ተካፋዮች፡ከኾኑ፡ በሥጋዊ፡ነገር፡ደግሞ፡ያገለግሏቸው፡ዘንድ፡ይገ፟ባ፟ቸዋልና። 28፤እንግዲህ፡ይህን፡ፈጽሜ፡ይህን፡ፍሬ፡ካተምኹላቸው፡በዃላ፡በእናንተ፡በኩል፡ዐልፌ፡ወደ፡እስጳንያ፡ እኼዳለኹ፤ 29፤ወደ፡እናንተም፡ስመጣ፡በክርስቶስ፡በረከት፡ሙላት፡እንድመጣ፡ዐውቃለኹ። 30፤ወንድሞች፡ሆይ፥ስለ፡እኔ፡ወደ፡እግዚአብሔር፡እየጸለያችኹ፡ከእኔ፡ጋራ፡ትጋደሉ፡ዘንድ፡በጌታችን፡ በኢየሱስ፡ክርስቶስና፡በመንፈስ፡ፍቅር፡እለምናችዃለኹ፤ 31-32፤በእግዚአብሔር፡ፈቃድ፡በደስታ፡ወደ፡እናንተ፡መጥቼ፡ከእናንተ፡ጋራ፡እንዳርፍ፥በይሁዳ፡ካሉት፡ ከማይታዘዙ፡እድን፡ዘንድ፥ለኢየሩሳሌምም፡ያለኝ፡አገልግሎቴ፡ቅዱሳንን፡ደስ፡የሚያሠኝ፡ይኾን፡ዘንድ፡ ጸልዩ። 33፤የሰላምም፡አምላክ፡ከኹላችኹ፡ጋራ፡ይኹን፤አሜን።