ወረኢሉአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች አንዱ ነው። ከተማው የተቆረቆረው በአጼ ምኒልክ ዘመነ መንግስት ሲሆን የቆረቆሩትም ራሳቸው ንጉሱ እንደሆኑ ይነገራል። ለአድዋ ጦርነት የክተት አዋጅ በታወጀበት ወቅት ንጉሱ ሰራዊታቸውን የሰበሰቡት በዚህ ከተማ ነው። ከተማው ከደሴ 91 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገናል።