እንዳ ማርያም (ቅድስት ማርያም) በቀደመው አርባዕተ አሥመራ ተብሎ በሚታውቀው መንደር አማካይ ቦታ ላይ የተሰራ ቤተክርስቲያን ነው። አርባዕተ አሥመራ በተራው የድሮውም ሆነ የአሁኑ አስመራ አማካይ ቦታ ነው።

እንዳ ማርያም -- በአሁኑ ዘመን

የቀደመው እንዳ ማርያም የሂድሞ ቅርጽ የያዘ የነበር ሲሆን ግድግዳውም የደብረ ዳሞን አሰራር በሚያስታውስ-መልኩ ከድንጋይና እንጨት ንብብር የታነጸ ነበር። ይህ የጥንቱ ቤተክርስቲያን ሁለት ጊዜ የተቃጠለ ሲሆን በሁለተኛው ጊዜ ያቃጠለው ግራኝ አህመድ ነበር።

በዚህ በድሮው ቤተክርስቲያን ፈንታ አዲስ ቤተክርስቲያን በጣሊያኑ አርክቴክት ኢ ጋሎ አቅድ መሰረት 1920 ላይ ተሰራ። 1938 ላይ ከእንደገና በመታነጽ ቤተክርስቲያኑ አሁን የያዘውን ቅርጽ አገኘ።