አበየጊሪ ቪሃረአኑራደፑረስሪ ላንካ የሚገኝ ጥንታዊ የቡዲስም ትልቅ ገዳምቤተ መቅደስ ነበር። በ80 ዓክልበ. በንጉስ ቨለገምባ (ቨጠጋሚኒ አበየ) ተመሠረተ። እስከ 1157 ዓም ድረስ ቆመ።

ቤተ መቅደሱ (አሁን እንደ ታደሰ)

የ«ቪሃረ» ትርጉም ከፓሊኛ «ገዳም» ሲሆን ከቡዲስት ገዳም በላይ ለቡዲስም ኅብረተሠብ ተከታዮች እንደ ከፍተኛ ትምህርት ቤት አገልግሎ ነበር። ከእርሱ በፊት ትልቁ የጤራቫዳ ቡዲስም ተቋም አኑራደፑረ መሃቪሃረ ከ244 ዓክልበ. ጀምሮ ይኖር ነበር፤ በ80 ዓክልበ. ግን 300 መኖክሶች ከመሃቪሃረ ተገንጥለው ወደ አዲሱ አበየጊረ ተዛውረው አዲስ የቡዲስም ወገን ጀመሩ። የአበየጊሪ ጤራቫዳ ወገን ግን ከመሃያነ ቡዲስም ወገን ትምህርቶች ጋራ ተቀላቀለ።

የአኑራደፑረ መንግሥት ነገሥታት አደልዎን ለአበየጊሪ ወገን ያሳዩ ነበር። እንዲሁም በ270 ዓም ግድም የነበረው ንጉሥ መሃሴነ መሃቪሃረውን አጥፍቶ አዲስ ሦስተኛ ተቋም ጄተቨና በአኑራደፑረ ከተማ መሠረተ። ከዚህ ትንሽ በኋላ ግን ያው ንጉሥ ዳግመኛ መሃቪሃረውን አሠራ። ሦስተኛው ተቋም ጄተቨና ደግሞ ከ270 እስከ 1157 ዓም ድረስ ቆመ።

ቻይና ተጓዥ ፋሥየን ተቋሙን በ398 ዓም በጎበኘው ጊዜ 5,000 ተማሮች መኖኩሶች (ቢኩዎች) እንደ ተገኙ ጻፈ። በዚያውም ወቅት፣ ከአለም ዋና ዩኒቨርስቲዎች አንድ ነበረ።

በ1157 ዓም የአበየጊሪና የጄተቨና ተቋማት ሃራ ጤቆች ተብለው ያው ቪሃረ በንጉሥ ፩ ፐራክረመባሁ ትዕዛዝ ተዘጋና ሌሎቹ ሁለት ተቋማት ወደ መሃቪሃረ ተጨመሩ። ከ1157 ዓም ጀምሮ ጤራቫዳ ብቻ ተደገፈ።

ተቋሙ ያስተማረው በተለይ ለቡዲስም ተከታዮች የሚገቡት ጽሁፎችና ኑሮ ዘዴዎች በተመለከተ ነበር።

2008 ዓም ፍርስራሹ በሙሉ ታድሶ ተገለጸ።