«አልወለድም» በደራሲ አቤ ጉበኛ ብዕር ተከሽኖ የቀረበና በ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ለሕትመት የበቃ ልብ ወለድ መጽሐፍ ነው። በ ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ዳግም ለኅትመት የበቃው እና አብዮቱ በሀገሪቱ ሲቀጣጠል በኅብረተሰቡ ዘንድ በከፍተኛ ሁኔታ የተነበበው ‘አልወለድም’ ማንንም ሰው ከእናቱ ማሕጸን ጀምሮ ምኞትና ጥንቃቄ ሊለየው እንደማይገባ የሚያትት ሲሆን በመታየት ላይ ያለው እውነታ ግን አዳጋች የሆነና የሰው ዘር በድህነት ተወልዶ፣ አድጎ እና ኑሮው በድህነት እንደሚያልፍ ያሳያል። እንዲህ ያለው ሁኔታ አግባብ አለመሆኑንም ይቃወማል። [1] መጽሐፉ የሰው ልጅ የሚደርስበትን መከራ በመቃወም ይሞግታል። የሰው ልጅ መብት በአግባቡ መጠበቅ እንዳለበት ያስረዳል።

ማጣቀሻ ለማስተካከል

  1. ^ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር ለ’ሚሌኒዬም’ ካሳተመው አጀንዳ፤ http://www.ethioreaders.com/index.php