አልበኒኒው ዮርክ ክፍላገር መቀመጫ ከተማ ነው።

አውሮፓውያን ከደረሱ አስቀድሞ ጥንታዊ ኗሪዎቹ የመሂከን ወገን ነበሩ። የነሱ ሠፈር ፐምፖቶወቱት-መሂከኔው ተባለ። የፈረንሳይ ቆዳ ነጋዴዎች በ1532 ዓም በዚያ ትንሽ አምባ ለጊዜው ጀምረው እንደነበር ይታመናል። በ1601 ዓ.ም. ኸንሪ ሀድሰን የሚባል የእንግላንድ ተጓዥ ደረሰ። መርከቡ በሆላንድ መንግሥት ስም ስለሆነ የሆላንድ ይግባኝ ጣለበት። የሆላንድ ነጋዴዎች በ1606 ዓ.ም. አምባውን አድሰው ፎርት ናሣው አሉት፤ በ1610 ዓም ግን በጐርፍ ጠፋ። ዳግመኛ አምባ ፎርት ኦራንጅ (ኦራኘ) በዙሪያው በ1616 ዓ.ም. ተሠራ። በ1622 ዓም ቦታው ረንሠለርስዊክ፣ በ1644 ዓም ቤቨርስዊክ ተባለ። በ1657 ዓ.ም. እንግሊዞች ያዙትና ስሙን ወደ አልበኒ ቀየሩት። ሆኖም የሆላንድ ሰዎች እንደገና በ1666 ዓም ለስድስት ወር ይዘውት ለጊዜው ስሙን ውለምስታት አሉት።